አሰፋ ማሩ – ልክ የዛሬ 18 ዓመት ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ

ልክ የዛሬ 18 ዓመት ሚያዝያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አሰፋ ማሩ ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ
የኢመማ ጀግኖች ሰማእታትን እናስብ።

የዛሬ 18 ዓመት ሚያዚያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አስፋ ማሩ ከቤቱ በሰላም ወጥቶ ወደ ሥራ በመሔድ ላይ እያለ በአዲስ አበባ ሐምሌ19 የሕዝብ መነፈሸ አካባቢ በጠራራ ጸሐይ በወያኔ/ኢህአዴግ ነፍሰ ገዳይ ፖሊሶች የጥይት እሩምታ ሰለባ የሆነ ጀግና ኢትዮጵያዊ ነው።
አቶ አሰፋ ማሩ በጊዜው በወሎ ክፍለሀገር በላስታ አውራጃ መቄት ወረዳ በ1951ዓ.ም ተወለደ። በመምህርነት ሙያ ከማገልገሉም ባሻገር በሙያ ማህበሩ የአመራር አባል በመሆንም የመምህራንን መብትና ጥቅም ለማስከበር ፣ የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅ በሚደረገው ትግል በግምባር ቀደምትነት ከሚታገሉት አንዱ ሆኖ ሕይወቱ በግፈኞች እስካለፈበት ዕለት በጽናት ቆሞ ቆይቷል። በወቅቱ በነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤም በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት የላቀ ድርሻ አበርክቷል።

No comments:

| Copyright © 2013 Lomiy Blog