ማክሰኞ ምሽት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ኢቲቪ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አስመልክቶ ያቀረበው ዜናን ብዙዎች በተቀላቀለ ስሜት ነበር የተከታተሉት፡፡
ዜናው የአቶ አንዳርጋቸውን ንግግር ለአፍታ ያቀረበ ሲሆን ይዘቱ ግን ግራ ያጋባቸው በርካቶች ናቸው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ‹‹እኔ አሁን ከራሴ ጋር ታርቄ ሰላም አግኝቻለሁ፡፡ እውነቴን ነው የምልህ እኔ እንደ ምርቃት ነው የተቀበልኩት፡፡ አሁን የሚያስቸኩለኝ ነገር የለም፡፡ ጥሩ ዕረፍት ማድረግ እፈልጋለሁ፡፡ ምክንያቱም በጣም በጣም ደክሞኛል … ሰልችቶኛል፡፡ እውነቴን ነው የምልህ ተረጋግቼ ያለሁበት ሁኔታ ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጥላቻ በውስጤ የለም፡፡ ምንም ዓይነት ብስጭት የለኝም፡፡ ምንም ዓይነት መጥፎ ስሜት አይሰማኝም፡፡ በቃ … የመጨረሻ እርጋታና ዕረፍት ውስጥ ነው ያለሁት፤›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ከአንዴም ሁለቴ በፍርድ ቤት በሽብርተኝነት ከሶ የሞት ፍርድ ባስፈረደ መንግሥት ቁጥጥር ሥር የዋለ ሰው በጤናው ደስተኛነቱን አይናገርም የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች፣ የንግግሩን አንድምታ በተመለከተ የተራራቀ መላምታቸውን ማቅረባቸውን ቀጥለዋል፡፡ ለአንዳንዶች የአቶ አንዳርጋቸው ንግግር ባልተጠበቀ መንገድ በጠላቶቹ እጅ የወደቀ ሰው ያለበትን ሁኔታ ባለመቀበል የሰጡት ነው፡፡ ለሌሎች ደግሞ በአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ ሁኔታ ላይ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እያሰማ ላለው ሥጋት ምላሽ ለመስጠት መንግሥት አስገድዷቸው የሰጡት ቃል ነው፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልገሎትና የፌዴራል ፖሊስ የጋራ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሰንዓ በኩል ወደ ኤርትራ ሊገቡ ሲል ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለው፣ በዚያው ዕለት ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠታ
ቸውን አስታውቋል፡፡ ይህ ከሁለት ሳምንት በላይ የዘለቀውን የአቶ አንዳርጋቸውን መገኛ ቦታ ጥያቄና መላምት የሚያስቆም ቢሆንም፣ በመንግሥት በአሸባሪነት የተፈረጀው የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ በኢትዮጵያ መያዝ ግለሰቡ ካላቸው የእንግሊዝ ዜግነት አኳያ የሚያስከትለው የሕግና የፖለቲካ አንድምታ ግን አሁንም የመወያያ አጀንዳ መሆኑ አልቀረም፡፡ በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ የሆኑት የየመን፣ የኢትዮጵያና የእንግሊዝ መንግሥታት ሚና፣ ወቅታዊ ሁኔታና የመጪ ጊዜ ግንኙነት ግልጽ አይደለም፡፡ አንዳንዶቹ የመን አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፋ የሰጠችበት መንገድ ዓለም አቀፍ ሕግ የሚጠይቃቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ያሟላ አይደለም በማለት እየተቿት ይገኛሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ግንቦት 7 ለኢትዮጵያውያን መብትና ነፃነት እታገላለሁ እያለ በአመራሩ እርከን ከሊቀመንበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በመቀጠል የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው እንግሊዛዊ መሆናቸው ስሜት አልሰጣቸውም፡፡ በአንድ በኩል እንግሊዝ ዜጋዋ የሆነውን የአቶ አንዳርጋቸውን መብት ለማስጠበቅ ከየመንም ጋር ሆነ ከኢትዮጵያ ጋር የሚጠበቅባትን አላደረገችም በሚል እየተተቸች ነው፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵያን መንግሥት በኃይል ለመገልበጥ ለሚሠራው ግንቦት 7 አመራር ዜግነት የሰጠችው እንግሊዝ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍንና ሽብርተኝነት እንዲጠፋ ከኢትዮጵያ ጋር በጥምረት መሥራቷ የተቃርኖ ስሜት የፈጠረባቸው በርካቶች ናቸው፡፡ ጥቂቶቹ ደግሞ የአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ በአንፃራዊነት ጥሩ የሚባለውን የእንግሊዝና የኢትዮጵያ ግንኙነት አይጐዳውም ወይ ሲሉ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የእንግሊዝን ፓስፖርት የያዙ ግለሰብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ምን ጥልቅ ያደርጋቸዋል? ዜግነታቸውን ጥለው ከሄዱ በኋላ ማንን ነው ነፃ የሚያወጡት? ይህ ዓይነቱ ድርጊትስ አንድን ሉዓላዊ አገር መዳፈር አይደለም ወይ? ሲሉ ይከራከራሉ፡፡
አቶ አንዳርጋቸው በዋና ጸሐፊነት ያገለግሉት የነበረው ግንቦት 7 በ2000 ዓ.ም. በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አማካይነት የተቋቋመ ሲሆን፣ አወዛጋቢው ምርጫ 97 የተካሄደበትን ቀን ለማስታወስ ስሙን እንደመረጠው ንቅናቄው ይገልጻል፡፡ በ1997 ዓ.ም. ተካሂዶ በነበረው አገር አቀፍ ምርጫ ወቅት የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ኢሕአዴግን በከፍተኛ ሁኔታ የተፎካከረው ሲሆን፣ በተለይ በአዲስ አበባ ፍፁም የበላይነት ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡ ቅንጅት በኋላ ላይ የአዲስ አበባን አስተዳደርና የፓርላማ መቀመጫውን አልረከብም ቢልም ዶ/ር ብርሃኑ የዋና ከተማዋ ከንቲባ እንዲሆኑ መርጧቸው ነበር፡፡ ኢሕአዴግ ምርጫውን አጭበርብሯል በሚል ለተቃውሞና ለአመፅ የወጡ አካላት ከመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ጋር በፈጠሩት ግጭት ወደ 200 የሚደርሱ ሰዎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ተከትሎ፣ ዶ/ር ብርሃኑን ጨምሮ የቅንጅት አመራሮች ታስረው የነበረ ሲሆን ዶ/ር ብርሃኑ ግንቦት 7ን የመሠረቱት ከእስር ቤት እንደተለቀቁ ከአገር ቤት ከወጡ በኋላ ነው፡፡
ግንቦት 7 በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን እታገላለሁ የሚል ቢሆንም፣ በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት ለማስወገድ የትጥቅ ትግልን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት መንገድ እንደሚጠቀም ይገልጻል፡፡ ከተቋቋመ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2002 ዓ.ም. የመጀመሪያው ወራት በግንቦት 7 መሪነት የኢትዮጵያ የመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ የግድያ ወንጀል ለመፈጸም ሙከራ ሲያደርጉ ነበር ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን መንግሥት አስታውቆ ነበር፡፡ ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ካቀረበ በኋላ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በወቅቱ በአምስት ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ ሲወስን፣ በሌሎች 33 ግለሰቦች ደግሞ የዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ወስኖ ነበር፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በሌሉበት የሞት ቅጣት ከተላለፈባቸው መካከል አንዱ ነበሩ፡፡
በወቅቱ በሌሉበት የሞት ቅጣት የተላለፈባቸው አቶ አንዳርጋቸው ከቅጣቱ በኋላ ለቢቢሲ ‘ፎከስ ኦን አፍሪካ’ ፕሮግራም በሰጡት አስተያየት ቅጣቱን ጠብቀውት እንደነበር ገልጸው ነበር፡፡ ‹‹ይኼ ውሳኔ ለእኛም ሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስገራሚ አይደለም፡፡ የነፃነትን ዋጋ እናውቃለን፡፡ መብቶቻችንን ለማስጠበቅ ሁሌም ቢሆን መስዋዕትነት ለመክፈል እንገደዳለን፡፡ ይኼ መስዋዕትነት የሞት ቅጣት ከሆነ እሱን በፀጋ እቀበላለሁ፤›› ብለው ነበር፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በዚያ ቃለ ምልልስ ንቅናቄው የሚፈልገውን ውጤት ለማምጣት የትጥቅ ትግልን ጭምር እንደ አማራጭነት እንደሚጠቀም አስታውቀው ነበር፡፡ ‹‹ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ሊሰማ እስካልፈቀደ ድረስ እንዲሰማንና ከሥልጣንም እንዲለቅ ለማድረግ የምናስገድደው ይሆናል፤›› ብለው ነበር፡፡
በ2003 ዓ.ም. ፓርላማው በሽብርተኝነት ከፈረጃቸው ቡድኖች መካከል አንዱ ግንቦት 7 ሲሆን ሌሎቹ ኦብነግ፣ ኦነግ፣ አልቃይዳና አልሸባብ ናቸው፡፡ በ2004 ዓ.ም. በፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ በድጋሚ ተከሰው የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው በሌሉበት በድጋሚ የሞት ቅጣት ተላልፎባቸው ነበር፡፡
አቶ አንዳርጋቸው ኢሕአዴግ ሥልጣን በያዘባቸው የመጀመሪያ ዓመት አካባቢ የኢሕአዴግ መሥራች ከሆኑት ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) አባል እንደነበሩ በጻፉት መጽሐፍ ገልጸዋል፡፡ በ1985 ዓ.ም. በገዛ ፈቃዳቸው ከኢሕአዴግ እንደለቀቁ ‹‹ነፃነትን የማያውቅ ‹‹ነፃ አውጪ››” በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሐፍ መግቢያ ላይ አትተዋል፡፡ በስደት ይኖሩበት ከነበረው እንግሊዝ በ1983 ዓ.ም. ተመልሰው የብአዴን አባልና በአዲስ አበባ ኢሕአዴግ ኮሚቴ አባል በመሆን እስከ 1985 ዓ.ም. ድረስ ማገልገላቸውን አስፍረዋል፡፡ በተለያዩ የአመለካከት ልዩነቶች ከኢሕአዴግ ጋር መለያየታቸውን የገለጹት አቶ አንዳርጋቸው ከእነዚህ መካከል ኢሕአዴግ በማርክሲስት ርዕዮተ ዓለም ላይ ያለው አቋም፣ የኤርትራ ሪፈረንደም፣ የመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን አስተዳደር፣ የኢሕአዴግ ዲሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን መሠረት ያደረገ ውሳኔ አሰጣጥ፣ የሙስና መበራከት፣ አቅምን መሠረት ያላደረገ የአባላትና የአመራር ምልመላና ዕድገት፣ በኢሕአዴግ ላይ ከማንም ነፃ በሆኑ ኦዲተሮች ዓመታዊ የሒሳብ ቁጥጥር አለመደረጉ የሚሉት ይገኙበታል፡፡ ነገር ግን ኢሳት በተባለው ቴሌቪዥን ጣቢያ የኢሕአዴግ አባል እንዳልነበሩ ደግሞ አስተባብለዋል፡፡ 
የየመን አወዛጋቢ አሳልፎ የመስጠት ውሳኔ 
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል የመን በቁጥጥር ሥር አቶ አንዳርጋቸውን እንዳዋለች ወዲያው ለኢትዮጵያ መስጠቷን ያረጋገጠ ሲሆን የመን በቁጥጥር ሥር ማዋሏን ለእንግሊዝ ሳታስታውቅ በሚስጥር ለኢትዮጵያ አሳልፋ መስጠቷ ከዓለም አቀፍ ሕግ መርህ ውጪ እንደሆነ በመጥቀስ ትችት የሚያቀርቡባት አሉ፡፡ ነገር ግን የመን አቶ አንዳርጋቸውን ለኢትዮጵያ አሳልፋ የሰጠችው በ1991 ዓ.ም. በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና በቀድሞ የየመን ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳላህ መካከል በሁለቱ አገሮች የሚፈለጉ ወንጀለኞችን አሳልፈው ለመስጠት ባደረጉት ስምምነት መሠረት እንደሆነ በመግለጽ ራሷን ትከላከላለች፡፡ 
‘ዘ ኢኮኖሚስት’ መጽሔት እንደዘገበው ከሆነ ግን የመን አሳልፎ መስጠቱን ለመፈጸም የሚያስፈልጉ ተገቢነት ያላቸው ሥነ ሥርዓቶችን አልፈጸመችም፡፡ ለእንግሊዝ ባለሥልጣናት ቀድማ ሳታሳውቅ አሳልፋ መስጠቷ አንዱ ጥሰት እንደሆነም ጠቅሷል፡፡ መጽሔቱ ያነጋገራቸው አናንድ ዱባይ የተሰኙ ወንጀለኛን አሳልፎ የመስጠት ሕግ ኤክስፐርት ቅድሚያ የማሳወቅ ሥነ ሥርዓት በቪዬና የኮንሱላር ግንኙነቶች ኮንቬንሽን የተረጋገጠ በመሆኑ፣ የመን ለእንግሊዝ ኤምባሲ ሳታሳውቅ አሳልፋ መስጠቷ ሕጉን እንድትጥስ እንዳደረጋት አስረድተዋል፡፡
የሒዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት ሌስሊ ሌፍኮ በበኩላቸው የየመንና የኢትዮጵያ ድርጊት ሕጋዊነት ላይ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን፣ በተለይ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ሕግ በሚጥልባት ግዴታ መሠረት አቶ አንዳርጋቸው በጠበቃቸው፣ በቤተሰባቸውና በእንግሊዝ ኮንሱላር ኃላፊዎች እንዲጐበኙ ማድረግ እንዳለባት ጠይቀዋል፡፡ የመንም ምንም ዓይነት የቅድመ አሳልፎ መስጠት ሥነ ሥርዓቶችን ሳትጠብቅ ወዲያውኑ ለኢትዮጵያ አሳልፋ መስጠቷ የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰት እንደሆነ ተከራክረዋል፡፡
ሌፍኮ የመን ግርፋትን ለማስቀረት የተፈረመው ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን አፅዳቂ መሆኗን አስታውሰው፣ በኮንቬንሽኑ ተላልፎ የሚሰጠው ወንጀለኛ ለግርፋት የሚጋለጥ ስለመሆኑ በቂ ምክንያት ካለ አሳልፎ የመስጠት ውሳኔው ሊቀር እንደሚገባ የተደነገገ ቢሆንም፣ የመን ይህን ችላ በማለት አሳልፋ መስጠቷም ሌላ ጥሰት እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ሌፍኮ የኮንቬንሽኑ ድንጋጌ ኢትዮጵያና የመን ወንጀለኛን አሳልፎ ለመስጠት ከፈጸሙት ስምምነት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባም ተከራክረዋል፡፡
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ባወጣው መግለጫ የየመን ባለሥልጣናት መረጃ እንዲሰጡት በተደጋጋሚ ጠይቆ ምላሽ እንዳጣ በመግለጽ ሥጋት እንደገባው አስታውቆ ነበር፡፡ ድርጊቱም ከቪዬና ኮንቬንሽን ተፃራሪ እንደሆነ አመልክቶ ነበር፡፡ የውጭ ጉዳይ ቢሮው አቶ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ አስቀድሞ የሞት ፍርድ እንደተወሰነባቸው አስታወሶ እንግሊዝ በመርህ ደረጃ የሞት ቅጣትን ስለምትቃወም ኢትዮጵያ ቅጣቱን ተግባራዊ እንዳታደርግ ጠይቋል፡፡ 
ሪፖርተር በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡት ያነጋገራቸውና ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የዓለም አቀፍ ሕግ ኤክስፐርት የየመን ድርጊት ዓለም አቀፍ ሕግን ስለመጣሱና አለመጣሱ ለመግለጽ የአገሪቱን ብሔራዊ ሕግና በኢትዮጵያና በየመን መካከል ወንጀለኞችን አሳልፎ ለመስጠት የተፈራረሙትን ስምምነት በቅድሚያ ማጤን እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የመንና ኤርትራ በሃኒሽ ደሴቶች ጉዳይ ግጭት ውስጥ ስለሆኑ ኤርትራን ለመጉዳት አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፋ መስጠቷን በመግለጽ የመን ሕጋዊ ግዴታዋን ለመወጣት አለመሞከሯን የሚተቹም አሉ፡፡ 
‹‹ለኢትዮጵያውያን የሚታገል እንግሊዛዊ›› 
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ቢሆኑም በዜግነታቸው ግን እንግሊዛዊ ናቸው፡፡ ምርጫ 97ን ተከትሎ አባል የነበሩበት ቅንጅት ከገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ጋር የነበረውን አተካሮ ተከትለው አስቀድሞ ይኖሩበት በነበረው እንግሊዝ ጥገኝነት ከጠየቁ በኋላ፣ ዜግነት እንደተሰጣቸው የተለያዩ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የጋራ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል አቶ አንዳርጋቸው ባለፉት አምስት ዓመታት ኑሯቸውን በኤርትራ አድርገው ከኤርትራ መንግሥት ጋር በመተባበርና ከሌሎች ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በመሥራት ኢትዮጵያን ለመበጥበጥ ሲጥሩ እንደነበር አስታውቋል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በኤርትራ ለሽብርተኞች ሥልጠና ሲሰጡ እንደነበር መረጃ እንዳለውም ተቋሙ አመልክቷል፡፡
ለበርካታ ኢትዮጵያዊያን እንቆቅልሽ የሆነው ጥያቄ አቶ አንዳርጋቸው እንግሊዛዊ ከሆኑ ሉዓላዊ አገር የሆነችውን የኢትዮጵያን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚታገል ንቅናቄን ለምን ይመራሉ የሚል ነው፡፡ ይህን ጥያቄ ከሕግ አንፃር ሳይሆን የፖለቲካ እንቅስቃሴን ለማሳለጥ ከሚያስፈልግ የሞራል አቋም ጋር የሚያያዙት የፖለቲካ ተንታኞች አሉ፡፡ የትውልድ አገር በተለይ ከፖለቲካ ጋር በተገናኙ ምክንያቶች ዜግነትን በምትከለክልበት ወቅት፣ ለፖለቲካ ሥራ እንዲመች ሲባል የሌላ አገር ፓስፖርት መያዝና የሚቆሙለት ዓላማ ግን ዜግነት የከለከለችውን አገር ሕዝብ ማገልገል መሆኑ የተለመደ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ እንደ ምሳሌም የቀደሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የትጥቅ ትግል ያካሂድ የነበረውን ሕወሓትን እየመሩ የነበራቸው የሶማሊያ ፓስፖርት እንደነበር ይጠቅሳሉ፡፡ 
ሪፖርተር ያነጋገራቸው ኤክስፐርት ግን የአቶ አንዳርጋቸው የእንግሊዝ ፓስፖርት ከአገር አልባነት ዓውድ መታየት እንዳለበት ያስገነዝባሉ፡፡ ‹‹እርግጠኛ ነኝ እንግሊዝ የአቶ አንዳርጋቸው የጥገኝነት ጥያቄ ላይ ከመወሰኗና ፓስፖርት ከመስጠቷ በፊት የግል ሁኔታውን መርምራለች፡፡ ለምሳሌ አቶ አንዳርጋቸው በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀልንና የመሳሰሉ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ የተቀበላቸውን ወንጀሎች የትም ቢሆን ስለመፈጸማቸው የሚጠቁም ማንኛውም ዓይነት መረጃ እንዳለ ካወቀች ጥያቄውን ልትቀበለው አትችልም፡፡ እንዲህ ዓይነት ምክንያቶች በሌሉበት ሁኔታ ግን ጥያቄ ካቀረቡለት አገር ጋር ትክክለኛ የሆነ ግንኙነት እንዳላቸው ጠያቂዎቹ ካረጋገጡ ዓለም አቀፍ ሕግ አገር አልባነትን ለማስወገድ ዜግነት እንዲሰጥ ያበረታታል፤›› ሲሉ ኤክስፐርቱ ገልጸዋል፡፡ ኤክስፐርቱ በተጨማሪም የዜግነት ጥያቄው በዘፈቀደ ተከልክሏል ብሎ ያሰበ አመልካች በጉዳዩ ላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ መከራከር መብት እንዳለው ዓለም አቀፍ ሕግ ማረጋገጡንም ጠቁመዋል፡፡
ኤክስፐርቱ አገር አልባነትን ለማስወገድ በተመድ ሥር የተፈረሙት ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽኖችን በርካታ አገሮች ባያፀድቋቸውም ግለሰቦች ዜግነት ሲያጡ ሌሎች አገሮች እንዲሰጡ የሚያበረታቱ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ ዜግነት ሊጠፋ የሚችለው ወይ ዜጋው በፈቃደኝነት ዜግነቱ ይቅርብኝ ሲል አልያም ደግሞ ተገዶ ዜግነቱን ሲያጣ እንደሆነ የጠቆሙት ኤክስፐርቱ፣ ተገዶ ዜግነቱን የሚያጣ ግለሰብ ማመልከቻ ካስገባበት አገር ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ለማረጋገጥ ይበልጥ እንደሚቸገር አመልክተዋል፡፡ በውጭ አገር ለረዥም ጊዜ መኖር ትክክለኛ ግንኙነት ለማረጋገጥ ጠቃሚ ቢሆንም፣ በተመሳሳይ ግን ዜግነትን ለማጣትም ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሕግ ከኢትዮጵያ ውጪ ተደራቢ የሌላ አገር ዜግነትን ይከለክላል፡፡ ይኼም ማለት አንድ ሰው የሌላ አገር ዜግነትን ሲያገኝ የኢትዮጵያ ዜግነቱ እንደተሰረዘ ይቆጠራል፡፡ ነገር ግን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነትና የፌዴራል ፖሊስ ፀረ ሽብር ግብረ ኃይል አገልግሎት በመግለጫው፣ ‹‹ጥምር ዜግነት መያዝ ማንንም ከተጠያቂነት አይከላከለውም፤›› ሲል አስታውቋል፡፡ 
ኤክስፐርቱ በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያ የምትወስዳቸው ውሳኔዎች በሁለት ምክንያት ተቀባይነት ሊኖራቸው እንደሚችል ይጠቅሳሉ፡፡ አንደኛው ግለሰቡ ከኢትዮጵያ ጋር ጠላት ከሆነችውና በጦርነት ውስጥ እንዳለች ከምትወሰደው ኤርትራ ጋር መሥራታቸው እንደ ወንጀል የሚወሰድ መሆኑ ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በየመን ሰነዓ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ወደ ኤርትራ በመጓዝ ላይ እያሉ ነው፡፡ ኤርትራ በ1985 ዓ.ም. በሪፈረንደም ከኢትዮጵያ ከተገነጠለች በኋላ የአፍሪካ ቀንድ እየተባለ የሚጠራውን አካባቢ በማበጣበጥ የምትታወቅ ናት፡፡ በቅርቡም ተመድ በይፋ በሶማሊያ ከመሸገው አልሸባብ ጋር በመሥራት ሽብር እያስፋፋች ለመሆኗ ሪፖርት ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ኤርትራ ግንቦት 7ን ጨምሮ የኢትዮጵያን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚሠሩ ኃይሎች መቀመጫ ናት በሚል በኢትዮጵያ ሁሌም ትወቀሳለች፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ግለሰቡ ከዚህ ቀደም በፍርድ ቤት የሞት ቅጣት የተወሰነባቸው መሆኑን ኤክስፐርቱ ያስረዳሉ፡፡ 
የእንግሊዝ አቋም
ታዋቂው ጋዜጠኛ ማርቲን ፕላውትን ጨምሮ በርካታ ተንታኞች በጉዳዩ ላይ የእንግሊዝ ድምፅ በጉልህ አለመሰማቱን ተችተዋል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ዜጋው ቢሆኑም ለኢትዮጵያ ተላልፈው እንዳይሰጡ የውጭ ጉዳይ ቢሮው ተጨባጭ እንቅስቃሴ አለማድረጉን በመኮነን በርካታ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡ 
አቶ አንዳርጋቸው አስቀድሞ የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው በመሆናቸው ኢትዮጵያ ቅጣቱን ተግባራዊ ልታደርግ ትችላለች በሚል ሥጋት የገባቸው አሉ፡፡ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ቢሮም ኢትዮጵያ ቅጣቱን ተግባራዊ እንዳታደርግ ጠይቋል፡፡
የግንቦት 7 ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ማደቦ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ የምሥራች ኃይለ ማርያምና በ1997 ዓ.ም. ምርጫ ወቅት የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች ልዑካን በመምራት መጥተው የነበሩትና አሁንም የአውሮፓ ፓርላማ አባል የሆኑት አና ጎሜዝ፣ በተለያዩ ሚዲያዎች የእንግሊዝ መንግሥት ለጉዳዩ የሰጠውን አነስተኛ ትኩረት አውግዘዋል፡፡ አንዳንድ የእንግሊዝ ሚዲያዎች እንግሊዝ አቶ አንዳርጋቸውን ለማነጋገር ያደረገችው ጥረት ሳይሳካ መቅረቱን ዘግበዋል፡፡ 
እንግሊዝና ኢትዮጵያ አብረው ከሚሠሯቸው ነገሮች መካከል ዋነኛው በአፍሪካ ቀንድ ሽብርተኝነትን መዋጋት መሆኑን በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያን መንግሥት በኃይል ለመገልበጥ ከሚያሴረውና በሽብርተኝነት ከተፈረጀው ግንቦት 7 አመራሮች መካከል አንዱ ለሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ዜግነት መስጠቱ ያልተዋጠላቸው አካላት፣ ጉዳዩ የሁለቱን አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳያበላሽ ሥጋት ገብቷቸዋል፡፡ እንግሊዝ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከርም የአቶ አንዳርጋቸውን ዜግነት መሰረዝ እንዳለባትም የጠየቁ አሉ፡፡
እንደ ቀደመው ጊዜ ሌላው አገር ለሚያራምደው ፖሊሲ ተቃውሞ ለማሳየት ሳይሆን ዓለም አቀፍ ግዴታዋን ለመወጣት ዜግነቱን ለአቶ አንዳርጋቸው እንግሊዝ የሰጠች እንደሚመስላቸው የገለጹት ኤክስፐርቱ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ዜግነት የሁለቱን አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይጐዳል ብለው እንደማያስቡ አስረድተዋል፡፡ አሁን የአቶ አንዳርጋቸውን ዜግነት መሰረዝ ለእንግሊዝ ቀላል እንደማይሆንም አመልክተዋል፡፡ ‹‹የግለሰቡ ፖለቲካዊ ባህርይ በተለይም ዜግነት የሰጠውን አገር የሚጐዳ ተግባር መፈጸሙ ዜግነቱን ለመሰረዝ በቂ ምክንያት ነው፡፡ ነገር ግን ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር በተያያዘ መጠየቅ ያለበት ወሳኝ ጥያቄ እንግሊዝ ግንቦት 7 እንዴት ነው የምትወስደው የሚለው ነው፡፡ ዜግነት ጥቅም ብቻ ሳሆን ግዴታም አለው፡፡ ዜግነት ለሰጠህ አገር ታማኝ መሆን አለብህ፡፡ የግለሰቡ እንቅስቃሴ ከዚያ አገር ብሔራዊ ጥቅም ጋር ሊፃረር አይገባም፡፡ ይኼ የግንቦት 7 ድርጊት ከእንግሊዝ ብሔራዊ ጥቅም ጋር የሚጋጭ ነው ወይ ብለን መጠየቅ አለብን፡፡ ለምሳሌ አቶ አንዳርጋቸው በሽብርተኛነት ተፈርዶባቸዋል፡፡ ነገር ግን እንግሊዝ የኢትዮጵያ የፀረ ሽብርተኝነት ሕግ ለሽብርተኝነት የሰጠው ትርጉም በጣም ሰፋ ብሎ መተርጐሙ ላይ ተቃውሞ እንዳላት በግልጽ የሚታወቅ ነገር ነው፡፡ ስለዚህ ይኼ ጉዳይ ድንገት ያለመግባበት ምክንያት ሊሆን አይችልም፤›› ሲሉም ኤክስፐርቱ ይደመድማሉ፡፡ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎችም ፖለቲካው ከዓለም አቀፍ ሕግ የበለጠ የሚመዝን በመሆኑ፣ በእንግሊዝና በኢትዮጵያ ግንኙነት ዙሪያ የአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደማይኖረው አመልክተዋል፡፡  
ለዚህም እንደ ምሳሌ የሚያነሱት በቅርቡ አዲስ አበባ መጥተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተነጋገሩትን የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር ሊኔ ፊዘርስቶንን ነው፡፡ ሚኒስትሯ የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ ጨምሮ በበርካታ ጉዳዮች ጋር ከተነጋገሩ በኋላ አገራቸው በየዓመቱ የምትሰጠውን 300 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ የልማት ድጋፍ አጠናክራ መቀጠልዋን ማስታወቃቸው፣ የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ከምንም ነገር በላይ እንደሆነ ያሳያል ይላሉ፡፡ 
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ዓርብ ምሽት ከቢቢሲ ‹‹ፎከስ ኦን አፍሪካ›› ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ የሞት ፍርዱ ተፈፃሚ ይሆናል ወይ ተብለው ሲጠየቁ ‹‹አሁን መናገር አልችልም›› በማለት ከማረጋገጥ የተቆጠቡ ሲሆን፣ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያን የኤርትራ መልዕክተኛ ሆነው የመበጥበጥ ሥራ እስከሠሩ ድረስ የእንግሊዝ ዜጋ መሆናቸው እሳቸውን በቁጥጥር ለማዋል ኢትዮጵያ ያለባትን የሞራልና የሕግ ግዴታ እንደማያስተጓጉለው ገልጸዋል፡፡ በሌሉበት ስለተፈረደባቸው በድጋሚ ጉዳያቸው እንዲታይ ይደረጋል ወይ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄም ሲመልሱ  ‹‹በአገር ከሌሉ ምን ማድረግ እንችላለን›› ያሉ ሲሆን ጉዳዩ በድጋሚ ሊታይ እንደማይችል ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ 
Source: Reporter

አበሻና ቀጥታ መስመር አይተዋወቁም፤ ቀጥታ መስመር መጀመሪያ አለው፣ መጨረሻም አለው፤ አበሻ እንዲህ ተጀምሮ የሚያልቅ ነገር አይወድም፤ እልቅ ሲል ጭር ይልበታል፤ አበሻ የባህርዩ የሆነውና የሚስማማው ክብ መስመር ነው፣ ክብ መስመር መጀመሪያ የለው፣ ማለቂያ የለው፣ ሲዞሩ መዋል ነው፤ አበሻ ነገሩ ሁሉ ክብ ነው፤ ቤቱ ክብ ነው፣ እንጀራው ክብ ነው፣ ዳቦው ክብ ነው፣ ድስቱ ክብ ነው፣ ጋኑም ክብ ነው፤ ክብ ያልሆነ
ነገር አበሻ ምን አለው?
አበሻ ነገሩ ሁሉ ክብ ነው፣ አዙሪት ነው፣ ታሪኩም አዙሪት ነው፣ ሄደ የተባለው ሁሉ ተመልሶ ይመጣል። አበሻ ማለት አዙሪት ነው፣ አዙሪት ማለትም አበሻ ነው። የእንግሊዝ ወይም የሩስያ ወታደሮችን ሰልፍ ስታዩ ቀጥታ መስመር ምን እንደሆነ ተገነዘባላችሁ። የአበሻ ወታደሮችስ? ተለያይቶ የተገጣጠመ ክብ መስመር?
አበሻ በመስመር መሄድም ሆነ መቆም አይሆንለትም። አበሻ ቀጥታ መሰመር ሲያጋጥመው የሚታየው ተለምጦ ነው፣ ክብ ሆኖ ነው፣ መጀመሪያ የሌለው፤ መጨረሻም የሌለው በፈለገበት በኩል ሊገባበትና በፈለገበት በኩል ሊወጣበት የሚያስችለው ክብ ሲሆን ነው፤ ሰዎች ተራ ይዘው በመስመር እንዲጠብቁ በሚደረግበት ግዜ አበሻ ጭንቀቱ ነው፤ እንዴት ብሎ ጀርባውን ለማያውቀው ሰጥቶ ከፊቱ ደግሞ አንድ የማያውቀው ሰው ተደንቅሮ በሰላም መቆም ይችላል? አንዱ ደፋር ከኋላው መጥቶ ቀድሞት ቢሄድ ግድ የለውም፤ ለነገሩ ራሱም ቢሆን ፈርቶ ነው እንጂ ያደርገው ነበር! የድሮዎቹን ሰዎች ጭንቀታቸውን ለመቀነስ አንተ ቅደም አንተ ቅደም እየተባባሉ የተራውን ቀጥታ መስመር ይቆለምሙት ነበር፤ የዛሬው የሰለጠነው ትውልድ አንተ ቅደም ብሎ ነገር አያውቅም፣ ሁሉም በየፊናው ለመቅደም ሲሞክር መተራመስ ነው፤ መተራመስ ቀጥታ መስመርን ድራሹን ማጥፋት ነው።

አበሻ ለቀጥታ መስመር ያለውን ኃይለኛ ጥላቻ ለመረዳት አምስት ደቂቃ ያህል በአዲስ አበባ መንገዶች ዳር በተለይ መስቀልያ በሆኑት ላይ ቆም ብሎ ማየት ነው። የትራፊክ ፅሕፈት ቤት በፈረንጅ አገር ሲደረግ አይቶ በየመንገዶቹ ላይ ሁሉ ነጭ መስመር ይለቀልቃል፣ ልፋ ያለው በህልሙ ዳውላ ይሸከማል እንደሚባለው ሆኖ ነው እንጂ መኪና የሚነዳው አበሻ መቼ ስራ አጥቶ ነው ያንን ቀጥታ መስመር የሚያየው? እያንዳንዱ ነጂ በፊናው በራሱ በውስጡ ያለውን ክቡን እየተከተለ በኩራት የትርምስ ትርኢት ያሳያል፤ ተመልካቾቹ የትራፊክ ፖሊሶች ናቸው። የትራፊክ ፖሊሶቹ አራትም አምስትም እየሆኑ የትርምሱን ቲያትር በመደነቅ ይመለከታሉ፣ በመንገዶቹ ላይ ቀጥታ መስመሮች የተሰመሩት ለመኪናዎቹ እንደአጥር ሆነው ቀጥታ እንዲሄዱ ለማድረግ ነበር፣ አበሻ ምኑ ቂል ነው? መኪናውን በመስመሩ ላይ አንፈራጥጦ እየነዳ ይሸፍነውና መስመሩን ከነኖራው ጋር ከህልውና ውጭ ያደርገዋል። መስመሩ ሲጠፋ ለትርምሱ ይበጃል፤ ለሁለት መኪናዎች የተቀየሰውን መንገድ አንዱ ብቻውን ይዞት ወሬውን እያወራ ይንፈላሰሳል።
ትርምስ ፈጣሪዎች ባለመኪናዎች ብቻ አይደሉም፣ እግረኞችም ናቸው፣ ለእግረኞቹ ማቋረጫ ተብሎ የተሰራ መንገድ አለ፣ እግረኞች ሁሉ በዚያ ለእግረኞች በተሰመረው መንገድ ገብተው ለማቋረጥ ይፈራሉ፤ መፍራታቸው አያስደንቅም። መስመሮቹ ለእግረኞቹም ሆነ ለመኪና ነጂዎቹ አይታዩም፤ የሚያስደንቀው ግን እግረኞቹ በባቡር መንገዱ መሃል ገብተው በሙሉl ልብ ሲያተራምሱ ነው!  የሚተራመሱት የትራፊክ ፖሊሶችም ቢሆኑ መስመሮቹን አያዩም፤ እግረኞቹንም አያዩም፤ መኪናዎቹን አያዩም፣ ለወጉ ለብሰው የሚተራመሰውን እያዩ እነሱም ይተራመሳሉ!
አበሻ በሩጫ በዓለም የታወቀ ሆኖአል፤ ግን በመቶ ሜትር የሩጫ ውድድር ስስጥ አበሻ የለበትም፣ የመቶ ሜትር ውድድር ውስጥ ትርምስ የለም፣ መስመር ይዞ መሮጥ ያስፈልጋል፣ ታዲያ አበሻ በሩጫ የተደነቀ ጎበዝ ቢሆንም በመስመር ውስጥ ገብተህ ሩጥ ሲሉት ግራ ይገባዋል፤ አበሻ ንጉስ እንደኀይሌ ንግሥት እንደ ጥሩነሽ የሚሆነው በርቀት ሩጫ ትርምስ ውስጥ ብቻ ነው፤ በመኪናም የርቀት ውድድር ቢኖር አበሻን ማን ይቀድመው ነበር!  ለሽቅድድም የወጣውን መኪና ሁሉ በትርምስ እያጣበቀ ቀጥ ያደርገው ነበር፤ ለመሆኑ ባቡሩ ተሰርቶ ሲያልቅ አበሻ ምን ይበጀዋል? ችግር ነው ጌትነት!
የአበሻ የመስመርና የወረፋ ጥላቻ ከምን የመነጨ ይመስላችኋል  ከጌታና ሎሌ ስርዓት አይመስላችሁም?  ከጨዋነት ነው የሚሉም አይጠፉም ይሆናል፣ በመተሳሰብ አንተ ቅደም አንተ ቅደም እየተባባለ ግዜን ሲያቃጥል ኖረና አሁን ደግሞ በትርምስ ጊዜን ያቆመዋል!
ደጉ ዘመን አንተ ቅደም የሚባልበት ዛሬ ከቻለ ገፍትሮ መቅደም፣ጨዋው ሲገፈትሩት አንገቱን ደፍቶ ዝም ማለት፣ በደርግ ዘመን ቤንዚን በሰልፍ በሚቀዳበት ግዜ መኪናዬ ውስጥ ሆኜ ተራዬን እጠብቃለሁ። አንዱ ጮሌ መስመሩን ስቶ መጣና ከእኔ መኪና ፊት ለመግባት ቆልመም አድርጎ አቆመ፤ መኪናዬን አስነሳሁና ገጨሁበት። ከመኪናው ወርዶ የተገጨውን ሲመለከት « እኔ ወፍ የምጠብቅ ይመስልሃል?» አልሁት፤ እሱም አግድም እያየኝ «እኔ ምን አውቃለሁ» ሲል መለሰልኝ።


87 በመቶ የማሊ ሴቶች ድብደባ ተገቢ ነው ይላሉ:: 

የጊኒና የኢትዮጵያ ሴቶችም ድብደባ ተገቢ ነው ብለው ያስባሉ:: 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተለያዩ ተቋማት በቤት ውስጥ ጥቃት ዙሪያ ያወጧቸውን ሪፖርቶች መነሻ በማድረግ በቅርቡ በ37 የአፍሪካ አገራት ላይ የተሰራ አንድ ጥናት፣ ኢትዮጵያውያን ባሎች ሚስቶቻቸውን አዘውትረው በመደብድብ 3ኛ መሆናቸውን አረጋገጠ።
‘አፍሪካ ሄልዝ፣ ሂዩማን ኤንድ ሶሻል ዲቨሎፕመንት ሰርቪስ’ የተባለው አህጉራዊ ድርጅትና በሴቶች ጥቃት ዙሪያ የሚሰሩ ሌሎች ተቋማት በጋራ የሰሩት ጥናት እንደሚለው፣ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ባሎች የትዳር አጋሮቻቸውን መደብደብ አግባብ ነው ብለው የሚያስቡና በተለያዩ ምክንያቶች ሚስቶቻቸውን የሚደበድቡ ናቸው፡፡ 
ጥናቱ ከተሰራባቸው የአፍሪካ አገራት የበለጠ ተደባዳቢ ባሎች ያሉባት አገር ናት ተብላ በቀዳሚነት የተቀመጠችው ኡጋንዳን ስትሆን፣ ሴራሊዮን ሁለተኛ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ ሶስተኛ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
60 በመቶ ያህሉ ኡጋንዳውያን ባሎች በትዳር ውስጥ የሚከሰቱ ግጭቶችን ለመፍታት ሚስቶቻቸውን መደብደብ ሁነኛ መላ ነው ብለው እንደሚያስቡ የጠቆመው የጥናቱ ውጤት፣ ለድብደባ ምክንያት ከሚያደርጓቸው ነገሮች መካከልም፤ ‘እዚህ ሄድኩ ሳትይኝ ከቤት ወጥተሸ ሄድሽ’፣ ‘የምልሽን አትሰሚኝም’፣ ‘ከእከሌ ጋር ያለሽ ነገር ምንድን ነው?’፣ ‘ልጆቼን በወጉ አልተንከባከብሽም’ እና ሌሎች ከወሲብና ከቅናት ጋር ተያያዙ ጉዳዮች እንደሚገኙበት አመልክቷል፡፡
ጥናቱ በተሰራባቸው አገራት የሚገኙ አብዛኞቹ ባሎች የድብደባን አስፈላጊነት የሚያምኑበት ሲሆን፤ በአንዳንዶቹ አገራት የጥቃቱ ሰለባ የሆኑት ሚስቶችም ተመሳሳይ አመለካከት እንዳላቸው ተጠቁሟል፡፡ መሰል አመለካከት ከሚንጸባረቁባቸው አገራት መካከል ጥናቱ በቀዳሚነት ያስቀመጠው ማሊን ሲሆን፣ ከ15 እስከ 49 የዕድሜ ክልል ውስጥ ከሚገኙ የአገሪቱ ሴቶች 87 በመቶ ያህሉ፣ ባሎች ሰበብ አስባብ እየፈጠሩ ሚስቶቻቸውን መደብደባቸው ተገቢ ነው ብለው እንደሚያስቡ አረጋግጧል፡፡ የማሊን ሴቶች ተከትለው የጊኒና የኢትዮጵያ ሴቶችም ድብደባ ይገባል ብለው ያስባሉ ብሏል ጥናቱ፡፡
የኡጋንዳ መንግስት ቃል አቀባይ ኦፎኖ ኦፖንዶ ለ “ኒውስ ቪዥን” ጋዜጣ በሰነዘሩት አስተያየት፤ የጥናቱ ውጤት ትክክለኛ መሆኑን ገልጸው፣ በአብዛኞቹ የአገሪቱ የገጠር አካባቢዎች የቤት ውስጥ ጥቃት እንደሚፈጸምና ተገቢ ነው ተብሎ እንደሚታመን እማኝነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
“አብዛኞቹ ባሎች የቤተሰቡ የገቢ ምንጭ በመሆናቸው በሚስቶቻቸው ላይ የፈለጋቸውን ጥቃት ቢሰነዝሩ ሃይ ባይ የለባቸውም፡፡ አንዳንዴ ደግሞ፣ ባሎች ሌላ ሚስት ወደቤታቸው ለማስገባት ሲሞክሩ ሚስቶች ነገሩን በመቃወም ከቤታቸው ለመውጣት ይሞክሩና በባሎቻቸው ድብደባና ግርፋት ይደርስባቸዋል፡፡” ብለዋል ቃል አቀባዩ፡፡

Source: Addis Addmass

ዳንኤል ክብረት: -
ሰሞኑን ከአንድ ሰው ‹የማጭበርበር› ነገር ጋር በተያያዝ ከዚህም ከዚያም አስተያየት ይሰጣል፡፡ አብዛኞቹ የመገናኛ ብዙኃንም ትኩረታቸውን በሰውዬው ላይ አድርገው እንዴት እንዲህ ሊያደርግ ቻለ? ለምን እንዲህ አደረገ? ምን ነክቶት ነው? እያሉ ጉዳዩን ከማኅበረሰብ ሳይንስ፣ ከሥነ ልቡና፣ ከእምነትና ከባሕል አንጻር እየተነተኑ ይገኛሉ፡፡
እኔ ግን ይህን ጉዳይ ስከታተል ትዝ የሚለኝ አንድ የሀገራችን ተረት ነው፡፡ ሰውዬው መንገድ ላይ ሲሄድ በሩ ወለል ብሎ የተከፈተ ቤት ያገኛል፡፡ ለጥቂት ቆም ብሎ ሁኔታውን ሲያይ ማንም በአካባቢው ዝር የሚል አልነበረም፡፡ ነገሩ የተከፈተ በር ብቻ ሳይሆን ‹የተከፈተ ዕድልም› የሆነለት ሰውዬ የተከፈተው ቤት ውስጥ ዘው ብሎ ይገባል፡፡ማንም አልነበረም፡፡ ወዲያና ወዲህ እየተንጎራደደ ቤቱን ቃኘና ዓይኑ ያረፈበትን ዕቃ ይዞ ላጥ አለ፡፡ መንገድ ላይ ያዩት ሰዎች የሚያውቁትን ዕቃ አንድ ሰው ይዞ ሲሸመጥጥ በማየታቸው ይጠራጠሩና ያስቆሙታል፡፡ ፖሊስም በነገሩ ይገባበታል፡፡ ሰውም ከዚህም ከዚያም ይወርድበታል፡፡
      ግርግሩ በዚህ መልክ እየቀጠለ ዕቃቸው የተሰረቀባቸው ሰዎች ኡኡ እያሉ ይደርሳሉ፡፡ ሲደርሱም የቤት ዕቃቸው በአንድ በማያውቁት ሰው ትከሻ ላይ ያገኛሉ፡፡ ግርግሩን ሰንጥቀው ይገቡና ‹‹ሞላጫ ሌባ›› እያሉ ሌባውን በጥፊ ሲመቱት ሌባው ተናድዶ ዕቃውን ያወርድና ጥፊውን በጥፊ ይመልሳል፡፡ ፖሊስ በድርጊቱ ተገርሞ ከዚያ ሁሉ ሰው ይልቅ ለባለቤቶቹ ጥፊ ለምን መልስ እንደሰጠ ሲጠይቀው ‹‹ቤታቸውን ከፍተው እየሄዱ ሰው ሌባ ያደርጋሉ›› አለ ይባላል፡፡
የሰሞኑ ሁኔታም ይህን ነገር እንድናየው የሚያደርግ ነው፡፡ ለመጭበርበርና ለመታለል የሚችል አሠራር፣ አካሄድና አፈጻጸም የዘረጋነው እኛው ነን፡፡ ነገሮችን በመረጃና በማስረጃ ላይ ተመርኩዘን ከመወሰን ይልቅ በሚወራ ወሬ፣ በሚገነባ ገጽታና ከሚዲያ በምንሰማው ነገር ላይ ብቻ የመመራትን አሠራር ያሰፈንነው እኛው ነን፡፡ ዛሬ ቀን ጥሎት የተጋለጠው ሰው ላይ በወደቀ ዛፍ ላይ የሚበዛውን ምሣር ሁሉ እናዘንብበታለን እንጂ ሌሎች ወደፊት እንዳይከሰቱ የሚያደርግ አደረጃጀት፣ አሠራርና አስተሳሰብ ግን አልዘረጋንም፡፡  
እንዲያውም የዚህን ሰው በዚህ መልኩ መምጣት ለሀገራችን ተቋማትና ኃላፊዎች ‹በረከተ መርገም› የሚሆን ይመስለኛል፡፡ ‹ዓመት ባል ካልመጣ ሁሉ ሴት፣ ክረምት ካልመጣ ሁሉ ቤት› የሚባል አባባል አለ፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዎች ባይኖሩ የኃላፊዎቻችንን፣የምሁሮቻችንንና የመሥሪያ ቤቶቻችንን የተዝረከረከ አሠራር እንድናይ ማን ያደርገን ነበር፡፡ እዚህ ሀገር ምን ዓይነት ሰዎች ምን ዓይነት ቦታ እንደሚይዙ አሳይቶናል፤ ሴትዮዋ ‹አፍ ያለው ያግባሽ ከብት ያለው› ስትባል ‹‹አፍ ያለው ያግባኝ፣ አፍ ያለው ከብቱን ያመጣዋልና›› ያለችው እውነቷን ነው እንድንል አስችሎናል፡፡ አፍ ካለ፣ መናገር ከተቻለ፣ መስጠት ከተቻለ፣ እዚህ ሀገር ውስጥ ዕድሉም መንገዱም ወለል ብሎ እንደሚከፈት አይተናል፡፡ ሚዲያዎቻችንም የማጣረት፣ የመመርመርና ከግራ ቀኝ የማየት ዐቅማቸው የት ድረስ እንደሆነ አሳይቶናል፡፡ ‹ማን ምን አለ› እንጂ ‹ያለው ልክ ነው ወይ?› ብሎ ለማረጋገጥ ጥቂት እርምጃዎች መሄድ የሚችሉ ሚዲያዎች እንደዋልያ ‹ብርቅዬ ድንቅየ›› መሆናቸውን ተምረንበታል፡፡
እንዲህ ያለ ሰውማ ይምጣ፡፡ እዚህ ሀገር ድፍረት እንጂ ዕውቀት፣ ትውውቅ እንጂ ዕውውቅ፣ ዘመድ እንጂ ችሎታ፣ ቅልጥፍና እንጂ ጉብዝና ዋጋ እንደሌላቸው እናይ ዘንድ፡፡
እኔን ምን አገባኝ የሚሉት አጉል ወግ
እርሱ ነው ሀገሬን ያረዳት እንደ በግ
የሚል ግጥም ልጽፍ ተነሣሁኝና
ምን አገባኝ ብዬ ተውኩት እንደገና
ብሎ የጻፈውን ባለ ቅኔ እውነት እንድናየው አድርጎናልና እንዲህ ያለ ሰውማ ይኑር፡፡
ምሁሮቻችን ያላስተማሩት ተማሪ ከፊታቸው ቆሞ አስተምራችሁኛል ሲላቸው፣ ተማሪዎቹ ብቃት አንሷችሁ እኔን ማየት ሳትችሉ ቀርታችሁ ነው እንጂ አብሬያችሁ ተምሬ ነበር ሲላቸው፣ የዩኒቨርሲቲዎች አስተዳደሮች ረስታችሁኝ ነው እንጂ ሸልማችሁኝ ነበር ሲላቸው፣ በቅቼ ተሠውሬ ነው እንጂ አብሬያችሁኮ ነው የምሠራው ሲላቸው፤ የቤተ መንግሥት ሰዎች በእሳት ሠረገላ ገብቼ አላያችሁኝም እንጂ ከአቶ መለስ ጋር አብሬ ነበርኩኮ ሲላቸው ዝም ያሉት ‹ዝምታ ወርቅ ነው›› ብለው አይደል፡፡ የዝምታችን ነገር የት ድረስ እንደሚደርስ፣ ስሕተትን የመቻል ዐቅማችን የት ድረስ እንደሆነ፣ የተበላሸን ነገር የመሸከም ችሎታችን ምን ያህል እንዳደገ፣ ውሸትን የመቀበል ብቃታችን ጨምሮ ጨምሮ እዚህ መድረሱን በሚገባ አሳይቶናል፡፡ ኑርልን ባክህ፡፡
ባለፈው ጊዜ በዓለም ዋንጫ ጉዟችን አንድ ተጨዋች ሁለት ቢጫ ካየ በኋላ እንደገና ተሰልፎ በመጨዋቱ ፊፋ ቀጣን፡፡ ይህ ቅጣት ብዙ ሰዎችን አሳዘነ፡፡ ያ ቅጣት ግን ብናውቅበት ኖሮ በረከተ መርገም ነበር፡፡ የፌዴሬሽናችንን አሠራር ቁልጭ አድርጎ በአደባባይ ያሳየን፡፡ እንኳንም ተጨዋቹ ተቀጣ፣ እንኳን ፌዴሬሽኑም ተዝረከረከ፡፡ ያንን ዝርክርክነት እንዴት አድርገን እናየው ነበር፡፡ ከዚያ በፊትምኮ ከዚያ የባሱ ዝርክርክ አሠራሮች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በድብብቁ አሠራራችን ምክንያት ‹ሽል ሆነው ከመግፋት ይልቅ ቂጣ ሆነው እየጠፉ› ሳናያቸው ኖርን፡፡ ያንን አጋጣሚ ማለፍ ግን አልተቻለም፡፡ ዓለም ያወቀው፣ ዓለም ሊያውቀውም ግድ የሚለው ጥፋት ነበረና፡፡
የሚገርመው ነገር እንዲያ ዓይነት አገርን አንገት ያስደፋን ጥፋት ሲሆን እንዳይፈጸም፣ ካልሆነም እንዲታረም የሚያደርግ አሠራር ባለመዘርጋታችንና አመለካከታችንንም ባለማስተካከላችን በሴቶች እግር ኳስ ላይ ተደገመና የፓስፖርት መጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባትን ተጨዋች ለማሰለፍ ሜዳ ውስጥ እስከማስገባት ደረስን፡፡ ይኼኛውን ዝርክርክነት ለማወቅ የቻልነው ለማወቅና ለመታወቅ የግድ የሚለው ዓለም አቀፋዊ አሠራር በመኖሩ የተነሣ ነው፡፡
ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ(ገሞራው) ‹በረከተ መርገም› በሚለው ግጥሙ ላይ ‹ድኻው ምን አረገ ሊቆቹን ነው መርገም› ይላል፡፡ አሁን መረገም ያለበት ተቋማዊ አሠራራችን፣ አስተሳሰባችን፣ የመረጃ አያያዛችን፣ ነገሮችን በንሥር ዓይን ከማየት ይልቅ በተወራውና በተባለው ብቻ መመራታችን፣ የዘመድ አዝማድ አካሄዳችን፣ የተጠጋጋውን ሁሉ የሚያምነው አሠራራችን ነው፡፡ መረገም ያለበት ለመታለል፣ ለመሞኘት፣ ለመሸወድ፣ ለመጭበርበር እጅግ ቀላልና እጅግም ዝግጁ የሆነው ቢሮክራሲያችን ነው፡፡
ይህን መሰል ሰዎች መምጣታቸው በሀገራችን እጅግ ተወዳጁ ምግብ ‹ምላስና ሰንበር› መሆኑን እንድናውቅ አድርጎናል፡፡ ምላስና ሰንበር ካለህ የፈለግከውን ተናገር - ትሰማለህ፤ ምላስና ሰንበር ካለህ የፈለግከውን ነኝ በል - ትታመናለህ፤ ምላስና ሰንበር ካለህ የፈለግከው ቦታ ደርሻለሁ በል - ትደነቃለህ፤ ምላስና ሰንበር ካለህ እንደ ኢዲ አሚን ሁሉንም መዓርግ ለራስህ ስጥ - ትሞገሳለህ፤ ምላስና ሰንበር ካለህ ዐዋቄ ኩሉ ነኝ በል - ተከታይ ታገኛለህ፡፡ የዚህን መሰል ሰዎች መነሣት ይህንን አሳይቶናል፡፡ እንኳንም ተነሣችሁ፡፡
ደግሞስ እነርሱ ባይኖሩ ይህንን መሰሉን የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ የተወካዮች ምክር ቤት፣ ዋናው ኦዲተር፣ ያልደረሰባቸውን የተበላሹ አሠራሮች እንዴት እናያቸው ነበር? ኧረ እንኳን ኖራችሁ፤ ለኛ በረከተ መርገም ናችሁ፡፡ 
 © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው
Source: www.danielkibret.com

By: David Smith:- 
  It's 30 years since Ethiopia's famine came to attention in the UK. Now, a farmer plans to sue Britain for human rights abuses, claiming its aid has funded a government programme of torture and beatings as villagers have been removed from their homes. 

   "Life was good because the land was the land of our ancestors. The village was along the riverside, where you could get drinking water, go fishing and plant mango, banana and papaya. The temperature there was good and we could feed ourselves."
This is how Mr O – his name is protected for his safety – remembers the home he shared with his family in the Gambella region of Ethiopia. The fertile land had been farmed for generations, relatively safe from wars, revolutions and famines. Then, one day, near the end of 2011, everything changed. Ethiopian troops arrived at the village and ordered everyone to leave. The harvest was ripe, but there was no time to gather it. When Mr O showed defiance, he says, he was jailed, beaten and tortured. Women were raped and some of his neighbours murdered during the forced relocation.


Using strongarm tactics reminiscent of apartheid South Africa, tens of thousands of people in Ethiopia have been moved against their will to purpose-built communes that have inadequate food and lack health and education facilities, according to human rights watchdogs, to make way for commercial agriculture. With Orwellian clinicalness, the Ethiopian government calls this programme "villagisation". The citizens describe it as victimisation.
And this mass purge was part bankrolled, it is claimed, by the UK. Ethiopia is one of the biggest recipients of UK development aid, receiving around £300m a year. Some of the money, Mr O argues, was used to systematically destroy his community and its way of life. Now this lone subsistence farmer is taking on the might of Whitehall in a legal action; a hearing took place in the high court in London last Thursday, but judgment on whether the case can go ahead has been reserved. Mr O and his legal team now await a decision on permission from the judge, who will declare whether there is an arguable case that can go forward to a full hearing.
"The British government is supporting a dictatorship in Ethiopia," says Mr O, speaking through an interpreter from a safe location that cannot be disclosed for legal reasons. "It should stop funding Ethiopia because people in the remote areas are suffering. I'm ready to fight a case against the British government." The dispute comes ahead of the 30th anniversary of famine in Ethiopia capturing the world's gaze, most famously in Michael Buerk's reports for the BBC that sparked the phenomena of Band Aid and Live Aid. Now, in an era when difficult questions are being asked about the principle and practice of western aid, it is again Ethiopia – widely criticised as authoritarian and repressive – that highlights the law of unintended consequences.
Mr O is now 34. He completed a secondary-school education, cultivated a modest patch of land and studied part-time at agricultural college. He married and had six children. That old life in the Gambella region now seems like a distant mirage. "I was very happy and successful in my farming," he recalls. "I enjoyed being able to take the surplus crops to market and buy other commodities. Life was good in the village. It was a very green and fertile land, a beautiful place." So it had always been as the seasons rolled by. But in November 2011 came a man-made Pompeii, not with molten lava but soldiers with guns. A meeting was called by local officials and the people were told that they had been selected for villagisation, a development programme the government claims is designed to bring "socioeconomic and cultural transformation of the people".
Mr O says: "In the meeting the government informed the community, 'You will go to a new village.' The community reacted and said, 'How can you take us from our ancestral land? This is the land we are meant for. When a father or grandfather dies, this is where we bury them.'"
The community also objected to the move because they feared ethnic persecution in their proposed home and because the land would not be fertile enough to farm. "Villagisation is bad because people were taken to an area which will not help them. It's a well-designed plan by the government to weaken indigenous people."
    The army used brutal means to force the villagers to resettle. Mr O says he witnessed several beatings and one rape, and he knows of several women who contracted HIV as a result. Some people simply disappeared. He claims to have witnessed soldiers, police and local officials perpetrating the abuses. The  villagers, including Mr O and his family, found themselves in a new location in Gambella. He says there was no food and water, no farmland, no schools and no healthcare facility. Jobs, and hope, were scarce.
So in 2012 he dared to return to his old village and tried to farm his land. It was a doomed enterprise. In around April, he claims, he was caught and punished for encouraging disobedience among the villagers. Soldiers dragged him to military barracks where he was gagged, kicked and beaten with rifle-butts, causing serious injuries. He was repeatedly interrogated as to why he had come back. "I went to the farm and was taken by soldiers to military barracks and locked in a room," Mr O recalls. "I was alone and beaten and tortured using a gun. They put a rolled sock in my mouth. The soldiers were saying: 'You are the one who mobilised the families not to go to the new village. You are also inciting the people to revolution.' Other people were in different rooms being tortured, some even killed. Some women were raped. By now they have delivered children: even now if you go to Gambella, you will meet them." He reflects: "I felt very sad. I had become like a refugee in my homeland. They did not consider us like a citizen of the country. They were beating us, torturing us, doing whatever they want."
In fear for his life, Mr O fled the country. The separation from his wife and children is painful. He communicated indirectly with them last year through a messenger. "I am sad. The family has no one supporting them. I am also sad because I don't have my family."
But such is the terror that awaits that, asked if if he wants to return home, he replies bluntly: "There's nothing good in the country so there is nothing that will take me back."
Modern Ethiopia is a paradox. A generation after the famine, it is hailed by pundits as an "African lion" because of stellar economic growth and a burgeoning middle class. One study found it is creating millionaires at a faster rate than any other country on the continent. Construction is booming in the capital, Addis Ababa, home of the Chinese-built African Union headquarters. Yet the national parliament has only one opposition MP. Last month the government was criticised for violently crushing student demonstrations. Ethiopia is also regarded as one of the most repressive media environments in the world. Numerous journalists are in prison or have gone into exile, while independent media outlets are regularly closed down.
Gambella, which is the size of Belgium, has a population of more than 300,000, mainly indigenous Anuak and Nuer. Its fertile soil has attracted foreign and domestic investors who have leased large tracts of land at favourable prices. The three-year villagisation programme in Gambella is now complete. A 2012 investigation by Human Rights Watch, entitledWaiting Here for Death, highlighted the plight of thousands like Mr O robbed of their ancestral lands, wiping out their livelihoods. London law firm Leigh Day took up the case and secured legal aid to represent Mr O in litigation against Britain's international development secretary, whom it accuses of part-funding the human rights abuses.
Mr O explains: "The Ethiopian government is immoral: it is collecting money on behalf of poor people from foreign donors, but then directing it to programmes that kill people. At the meeting, the officials said: 'The British government is helping us.' Of all the donors to Ethiopia, the British government has been sending the most funds to the villagisation programme. "I'm not happy with that because we are expecting them to give donations to support indigenous people and poor people in their lands, not to create difficult conditions for them. They should stop funding Ethiopia because most of the remote areas are suffering. The funds given to villagisation should be stopped." Mr O did not attend last week's court hearing at which Leigh Day argued that British aid is provided on condition that the recipient government is not "in significant violation of human rights". It asserted that the UK has failed to put in place any sufficient process to assess Ethiopia's compliance with the conditions and has refused to make its assessment public, in breach of its stated policy.
    "There are credible allegations of UK aid money contributing to serious human rights violations," states Leigh Day's summary argument. "In particular, there is evidence that the 'villagisation' programme is partly funded by the defendant's payments into the promotion of basic services programme." The concerns have led to a full investigation by the World Bank, it adds.
Rosa Curling, a solicitor in the human rights department at Leigh Day, says: "It's about making sure the money is traced. When you're handing over millions of pounds you have a legal responsibility to make sure the money is being used appropriately. The experience of the village is absolutely appalling. We're saying to the Department for International Development (DfID), please look at this issue properly, please follow the procedure you said you would follow, please talk to the people who've been affected. Look at what happened to Mr O and his village. They haven't done that."
Mr O offered to meet British officials, she adds, but they decided his refugee camp was too dangerous. He offered to meet them in a major city, but still they refused. "They haven't met anybody directly affected by villagisation." Curling urges: "If you've got money, trace it and put conditions on it so it's not being used like this. It completely defeats the point of aid if it's being used in this way. We're talking about millions of British pounds."
The view is echoed by Human Rights Watch. Felix Horne, its Ethiopia and Eritrea researcher, says: "Given that aid is fungible, DfID does not have any mechanism to determine how their well-meaning support to local government officials is being used in Ethiopia. They have no idea how their money is being spent. And when they are provided [with] evidence of how that money is in fact being used, they conduct seriously flawed assessments to dismiss the allegations, and it's business as usual.
"While they have conducted several 'on the ground' assessments in Gambella to ascertain the extent of the abuses, they have refused to visit the refugee camps where many of the victims are housed. The camps are safe, easy to access, and the victims of this abusive programme are eager to speak with DfID, and yet DfID and other donors have refused to speak with them, raising the suspicion that they aren't interested in hearing about abuses that have been facilitated with their funding."
DfID is set to contest the court action, denying that any of its aid was directly used to uproot Mr O or others affected by villagisation. A spokesman says: "We will not comment on ongoing legal action. The UK has never funded Ethiopia's resettlement programmes. Our support to the Protection of Basic Services Programme is only used to provide essential services like healthcare, schooling and clean water." Shimeles Kemal, the Ethiopian government's state minister of communications, was unavailable for comment.
    Source: The Guardian

-አና ጎሜዝ ወደ እንግሊዝ መመለስ አለባቸው እያሉ ናቸው:: 
ከዱባይ ወደ አስመራ ለመሄድ የመን ሰንዓ ላይ በየመን የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ታስረዋል የተባሉት በሽብርተኝነት የተፈረጀው የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ለኢትዮጵያ ተላልፈው ተሰጥተዋል መባሉን እንደ ሰማ የእንግሊዝ መንግሥት አስታወቀ፡፡
ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ማረጋገጫ እንደሚፈልግ ገልጿል፡፡ 
በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ የፖለቲካ ጉዳዮች ምክትል ጸሐፊ ሚስተር ኢያን ኮክስ አቶ አንዳርጋቸውን በሚመለከት ለሪፖርተር በላኩት መግለጫ እንዳስረዱት፣ የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው አቶ አንዳርጋቸው  ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰነዓ ውስጥ መጥፋታቸው ተገልጾላቸዋል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የእንግሊዝ ባለሥልጣናት አቶ አንዳርጋቸው ያሉበትን ሁኔታና ሥፍራ ለማወቅ የየመን ከፍተኛ ባለሥልጣናትንና በእንግሊዝ የሚገኙትን የየመን አምባሳደርን ማነጋገራቸውን አስረድተዋል፡፡
ኢያን ኮክስ አንዳንድ ከሚወጡ መረጃዎች ለመረዳት እንደቻሉት፣ አቶ አንዳርጋቸው ምናልባትም ኢትዮጵያ ውስጥ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ በመሆኑም ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በአስቸኳይ ማረጋገጫ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባለፈው ዓርብ ባወጣው መግለጫ፣ አቶ አንዳርጋቸው በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ እንደሚገኙ ከሪፖርቶች መረዳት መቻሉን ገልጾ፣ ከሚመለከታቸው አካላት ማረጋገጫ በአስቸኳይ እንዲሰጠው መጠየቁን አስታውቋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የእንግሊዝ ባለሥልጣናት በእንግሊዝ የየመን አምባሳደርን አነጋግረዋቸው፣ አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው መሰጠታቸውን ለቤተሰቦቻቸው መንገራቸውን ለቢቢሲ አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባል የሆኑትና የኢትዮጵያን መንግሥት በመንቀፍ የሚታወቁት ሚስስ አና ጎሜዝ፣ አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠታቸውን ማረጋገጣቸውን ለእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዊልያም ሔግ በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡
ሚስስ ጎሜዝ በይፋዊ ድረ ገጻቸው ባሰፈሩት ደብዳቤ አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው እንደተሰጡ መረጃ ማግኘቻቸውን ገልጸው፣ በዚህም መደንገጣቸውንና የእንግሊዝ መንግሥት ምንም ዓይነት ዕምርጃ ባለመውሰዱ መናደዳቸውንም አስረድተዋል፡፡
ሚስ ጎሜዝ  በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የሕይወትና የአካል አደጋ ሊደርስባቸው እንደሚችል፣  እንዲሁም ባላመኑበትና ባልፈጸሙት ወንጀል ክስ ሊቀርብባቸው እንደማይገባ ገልጸው፣ በተቻለ መጠን ወደ እንግሊዝ የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻችም ጠይቀዋል፡፡
በ1997 ዓ.ም. ብሔራዊ ምርጫ የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የነበሩት ሚስስ ጎሜዝ፣ የእንግሊዝ መንግሥት የኢትዮጵያ ዋነኛው ለጋሽና የፖለቲካ ደጋፊ በመሆኑና ተፅዕኖውም ከማንም አገር የላቀ በመሆኑ፣ አቶ አንዳርጋቸውን ማስፈታት አለበት ሲሉ ለቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ፕሮግራም መናገራቸው ተዘግቧል፡፡
አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው ተሰጥተዋል መባሉን በተመለከተ፣  የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናትም ምንም ዓይነት መረጃ አልሰጡም፡፡ ነገር ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በሕግ የሚፈለጉ በመሆናቸው ተላልፈው መሰጠት እንዳለባቸው ለውጭ ሚዲያ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
ኢትዮጵያና የመን በ1991 ዓ.ም. በተፈራረሙት የፀጥታና የደኅንነት ስምምነት መሠረት፣ የመን አቶ አንዳርጋቸውን ለኢትዮጵያ አሳልፋ እንደምትሰጥ ይነገራል፡፡ በሌላ በኩል የእንግሊዝ ዜግነት ስላላቸው ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠት የለባቸውም የሚሉ ሲኖሩ፣ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እስከገቡ ድረስ ተጠያቂነት እንዳለባቸው የሚከራከሩ አሉ፡፡
Source: Reporter

መነሻቸውና መድረሻቸው ከየትና ወዴት እንደሆነ ያልተገለጸው የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የመን ሰንዓ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በየመን የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውለው መታሰራቸው ተሰማ፡፡ 
አቶ አንዳርጋቸው በየመን የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ታስረዋል የተባለው ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ሲሆን፣ ሰንዓ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከመያዛቸው ውጪ ከየት ተነስተው ወዴት እንደሚሄዱ አልታወቀም፡፡
    በኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጁት አልቃይዳ፣ አልሸባብ፣ ኦነግና ኦብነግ ጋር በአሸባሪነት የተፈረጀው ግንቦት 7 ዋና ጸሐፊውን በሚመለከት ያወጣው መግለጫ እንደሚያስረዳው፣ አቶ አንዳርጋቸው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ካወቀ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች ለማስለቀቅ ውስጥ ለውስጥ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካለትም፡፡ 
አቶ አንዳርጋቸው በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከአስመራ በየመኒያ አየር መንገድ ተሳፍረው፣ በየመን ሰንዓ ትራንዚት በማድረግ ወደ ኳታር ዶሃ ለመጓዝ ሲሞክሩ ሳይሆን እንደማይቀር የተለያዩ ድረ ገጾች ዘግበዋል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ደርግ የንጉሡን ሥርዓት በኃይል ከተቆጣጠረበት ሁለት ዓመታት በኋላ በ1969 ዓ.ም. ይከታተሉት የነበረውን የምህንድስና ትምህርት አቋርጠው ወደ ትግል መግባታቸውን በቅርብ የሚያውቋቸው ይናገራሉ፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲን (ኢሕአፓ) በመቀላቀል ትግል የጀመሩት አቶ አንዳርጋቸው፣ የበረሃ ትግላቸውንም ከተወሰኑ ጊዜያት በላይ እንዳልገፉበት የሚናገሩት ጓደኞቻቸው፣ ከኢሕአፓ አመራሮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግባባት ባለመቻላቸው ወደ እንግሊዝ አገር መሄዳቸውንም ይናገራሉ፡፡ በእንግሊዝ የስደት ዘመናቸው የደርግ መንግሥትን ይታገሉ ለነበሩት የኢሕአዴግ ታጋዮች የተለያዩ ዕርዳታዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውም ተጠቁሟል፡፡ ኢሕአዴግ የደርግ ሥርዓትን አስወግዶ ሥልጣን ሲይዝ በተደረገላቸው ጥሪ በ1983 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት አቶ አንዳርጋቸው፣ ከኢሕአዴግ ጋር የነበራቸው ቆይታ ከሁለት ዓመታት በላይ አልዘለቀም፡፡
በሽግግሩ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ጸሐፊ በመሆን የሠሩት አቶ አንዳርጋቸው፣ በ1985 ዓ.ም. መጨረሻ አካባቢ መልቀቂያ አስገብተው የተመደቡበትን ኃላፊነትና የኢሕአዴግ አባልነታቸውን በመተው በስደት ወደኖሩበት እንግሊዝ መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ 
አቶ አንዳርጋቸው በድጋሜ ወደ አገር ቤት የተመለሱት በ1997 ዓ.ም. መጀመሪያ አካባቢ ሲሆን፣ ወዲያውኑ የቅንጅት አባል በመሆን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ለመሆንም ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ በ1997 ዓ.ም. የነበረውን አገራዊ ምርጫን ተከትሎ ተፈጥሮ በነበረው የኢሕአዴግና የቅንጅት አለመግባባት የቅንጅት አመራሮችና የተወሰኑ አባላት ሲታሰሩ እሳቸው ባይታሰሩም፣ ቀደም ብሎ በተለያዩ ምክንያቶች ታስረው እንደነበርም ይታወሳል፡፡ 
የተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የፈረጀው የግንቦት 7 ድርጅት አመራር አባል የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው፣ አገር ውስጥ በህቡዕ ተደራጅተው መንግሥትንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመገርሰስ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል በሚል ክስ ተመሥርቶባቸው ከነበሩት እነብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞና አቶ አሳምነው ጽጌ (ማዕረጋቸው ተገፎ ነው)፣ እንዲሁም የግንቦት 7 ድርጅት አመራር ከሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር መከሰሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ጉዳዩን ሲመረምር የነበረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እነጄኔራል ተፈራ ማሞ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ሲወስን፣ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሞት እንዲቀጡ መወሰኑ ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያና የመን ባደረጉት እስረኛን አሳልፎ የመሰጣጠት ስምምነት መሠረት የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል የሚል ግምት እንዳላቸው፣ አንዳንድ በጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች እየተናገሩ ነው፡፡ 
ከዚህ ቀደም አንድ ነጋዴ ከባንኮች ብድር ወስደው ካገር ከወጡ በኋላ የመን በመያዛቸው፣ የየመን መንግሥት አሳልፎ መስጠቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 
የአቶ አንዳርጋቸውን በየመን ቁጥጥር ሥር መዋል አስመልክቶ ለሚመለከታቸው የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጥያቄ ቢቀርብላቸውም፣ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም፡፡ 
Source: Reporter

የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አባልና በአስመራ የሚገኘውን የግንቦት 7 ትግል ይመሩታል የሚባሉት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታሰራቸውን ግንቦት 7 ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
እንደ ግንቦት 7 ንቅናቄ መግለጫ ከሆነ አቶ አንዳርጋቸው ላለፉት አንድ ሳምንታት በየመን ታግተው የሚገኙ ሲሆን ለማስለቀቅ የተደረገው ጥረትም አልተሳካም። አቶ አንዳርጋቸው ወደ የመን የተጓዙት ለትራንዚት እንደሆነ የገለጸው የንቅናቄው መግለጫ የየመን መንግስት እኚህን የትግል ሰው ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፎ እንዳይሰጥ ስጋት እንዳለበት አስታውቋል።
በአቶ አንዳርጋቸው መታሰር ጉዳይ በሶሻል ሚዲያዎች ላይ መነጋጋሪያ የሆነ ሲሆን የፖለቲካ ተንታኙ ጃዋር መሀመድ የሚከተለውን በፌስቡክ አስፍሯል።
Jawar Mohammed On Facebook:
“Despite our difference in political opinion, I am shocked with news of
Andargachew Tsige’s arrest in Yemen. This development should not be seen from partisan perspective. When added to the recent arrest and extradition of Okello Akoay, the leader of the Gambela Movement, its signals that neighboring states starting to work for the regime. Mind you Andargachew was only using Yemen as transit. This is an alarming situation for opposition political leaders and human rights advocates who have taken refuge or travel to these countries. Its to the best interest of all to exert collective pressure on the surrounding governments.”
Source: Ze-Habesha 


    Andargatchew Tsige, secretary of Ginbot 7, a rebel group based in Eritrea, arrived in the Yemeni capital aboard Yemenia Airlines. He was waiting for his flight when Yemeni security men whisked him away into detention. Fears are mounting he might be extradited to Ethiopia.

The countries in the region, Ethiopia, Eritrea, Yemen, Sudan, and Djibouti are rogue states they don't really need 'extradition treaties' to hand over political opponents as 'convicted criminals.'
"Yemen should understand that any harm befalling the human rights, democracy and justice activist Andargatchew Tsige would painfully hurt the interests of the Ethiopian people who are struggling for freedom from life under the brutal TPLF regime," the rebel group Ginbot 7 said in a statement.
"We call for his immediate release; any attempt to hand over Andargachew to the regime in Addis Ababa would irrevocably damage the age-old relations between Ethiopia and Yemen," the rebel group said in its press release.
Andargachew's life was checkered by arrests, tortures, and exiled life before he helped found Ginbot 7, an Eritrea-based armed group vowing to overthrow the regime in Addis by all means possible.

In June 2012, Andargachew, and other top leaders of Ginbot 7, including Ginbot 7 chairman Dr Berhanu Nega, were tried on trumped-up terrorism charges and sentenced to life in absentia.
Source: Ethiomedia

አፍሪካን ፕሬስ ኤጀንሲ እንደዘገበው 10 የሱዳን ወታደሮች በኢትዮ -ሱዳን ድንበር አካባቢ ከተገደሉ በሁዋላ በድንበር አካባቢ ውጥረት ሰፍሯል። እሁድ እለት ደግሞ ተጨማሪ 13 የሱዳን ወታደሮች መቁሰላቸው የተዘገበ ሲሆን፣ ጥቃቱም በኢትዮጵያ ሚሊሺያዎች ሳይፈጸም እንዳልቀረ ተዘግቧል።
የሱዳን ኮማንዶ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ሃይሉን እያሰባሰበ መሆኑን የገለጸው ዘገባው፣ በአንድ ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መካሄዱን ጠቅሷል። ሱዳንና ኢትዮጵያ የድንበር ከተሞቻቸውን ከታጣቂዎች ጥቃት ለመከላከል በሚል  አንዱ በሌላው አገር ድንበር ጥሶ በመግባት እርምጃ እንዲወስድ መስማማታቸው ይታወቃል።
የሱዳን መንግስት ወታደሮቹ መገደላቸውን አምኖ፣ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ የሚለውን እንደማይቀበለው አስታውቋል። የሱዳን መንግስት ጦር ቃል አቀባይ ኮሌኔል አልስዋርሚ ካሊድ ሳድ እንደተናገሩት ወታደሮቻቸው የተገደሉት
ማንነታቸው ካልታወቁ የኢትዮጵያ ወታደሮች ጋር ሲዋጉ መሆኑን ተናግረዋል። ግጭቱ የተነሳው ባሶንዳ እየተባለ በሚጠራው በሁለቱ ድንበር አካባቢዎች መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ታጣቂዎቹ ባሶንዳ የሚገኘውንና በሱዳን መከላከያ ሰራዊት ስር የሚገኘውን የእርሻ ቦታ መልሰው ለመውሰድ አላማ ነበራቸው ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ባላስልጣናትም ስለጉዳዩ እንደተነገራቸው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል። ይሁን እንጅ የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን የተናገረው አንድም ነገር የለም።
በሱዳን ወታደሮች ላይ ለደረሰው ጥቃት ሃላፊነቱን እወስዳለሁ ያለ  ሃይልም እስካሁን አልቀረበም።
Source: www.geeskaafrika.com 
| Copyright © 2013 Lomiy Blog