ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ?
የግብፅ ጦር ዘመን ባፈራዉ ዘመናይ ጦር መሳሪያ መግደል፣ መደብደብ ማሰሩን፣ ሙስሊም ወንድማማቾች እምነት፣ቁጭት ና እልሕ በወለደዉ ፅናት መፋለሙን እንደቀጠሉ ነዉ።የዘመኑ ፈርዖኖች ፍሊሚያ የፈረዕኖቹን ዉልድ እየፈጀ፣ የፈርዖኖቹን ታሪካዊ፣ ሥልታዊት ሐገርን እያወደመ-ቁል ቁል ያንደረድራታል።የጥፋት ዉድመቱ ሒደት፣ ዉጤት መዘዝ አረብ አይሁድን፣ አፍሪቃ እስያን፣ ከሁሉም በላይ አዉሮጳ አሜሪካን እያሳሰበ ግን አቋማቸዉን እያዋዠቀ ነዉ።የግብፅ እልቂት-ዉድመት መነሻ የሁለቱ ፈርዖኖች ደምሳሳ ቅኝት ማጣቀሻ፣ የተቀረዉ ዓለም አቋም መድረሻችን ነዉ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።

ግብፃዊዉ ታዳጊ መሐመድ ገማል አይ ፒ ኤስ በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ ዜና አገልግሎት እንደዘገበዉ ዘንድሮ አስረኛ ዓመቱ ነዉ።ሲወለድ ጀምሮ አይነ-ስዉር ነዉ።እናት ዲና ገማል ግን «ልጄ አካለ ጎደሎ አይደለም።» ይላሉ።«ልጄ አይደለም በጨለማ ዉስጥ የሚኖረዉ።የግብፅ ማሕበረሰብ አንጂ።ዓይን አላቸዉ ግን ከልጄ እኩል ማስተዋል አይችሉም።» እያሉ ቀጠሉ የአይነ-ሥዉሩ ልጅ እናት።

አብደል በድሪም ግብፃዊ ናቸዉ።አሳ አጥማጅ።የሐምሳ-ዓመት ጎልማሳ።ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ እንዳሉት ለሳቸዉ እና በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የካይሮና ያካባቢዉ ነዋሪዎች በተለይ ካለፈዉ ሮብ ወዲሕ «እየዬም ሲዳላ ነዉ።» አይነት በግብፅ ጦር የተገደለ ዉላጅ-ተወዳጅ፥ ዘመድ፥ወዳጅን አስከሬንን አግኝቶ አልቅሶ መቅበር በርግጥ መታደል ነዉ።

«የቅርብ ጓደኛዬ እዚያ (ራባ-አል አደዊጃ) ተገደለ።አስከሬኑን በእሳት አጋዩት።ሞኖፊያ አዉራጅ የምትገኝ የአዲት ትንሽ መንደር ተወላጅ ነኝ።ከኛ ቀበሌ እና ከያንዳዱ አጎራባቾቻችን ቀበሌዎች ቢያንስ ሁለት ሠዉ ተገድሏል።»

ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ? ጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል ሲሲ፥ ወይስ መሐመድ ባድይ።መሐመድ ሙርሲ ወይስ ዓድሊ መንሱር? አናዉቅም።

ያዩ ግን ያዩ የሚያዉቁትን-ይነግሩናል።ሮይተር ዜና አገልግሎት እንደዘገበዉ ግን የካይሮ ሆስፒታሎች የአስከሬን ማስቀመጫዎች ከአፍ እስከ ገደፋቸዉ ሥለሞሉ ከየአየደባባዩ የሚለቀመዉ የሰዉ አካል ቁርጥራጭ፥ እና አስከሬን በየመሳጂዱ ታጭቋል።እና ለገሚስ ግብፆች የሟች አስከሬን አግኝቶ፥ አልቅሶ መቅበር ዛሬ መታደል ነዉ።

የአስር ዓመቱ አይነ-ሥር ወጣት የሐገሩን ምሥቅልቅል ለማወቅ ዓይኑ ሳይሆን ዕድሜዉ በርግጥ አይፈቅድለትም።ሙዚቃ ይወዳል።በልዩ ኮምፒተሩ እየታገዘ ድረ-ገፆችን ማገላበጥ ይችላል። ፊደላት እየደረደረ ቃላት፥ ቃላት እየገጣጠመ ዓረፍተ-ነገራት ይሠራል።እንደማንኛዉም ሕፃን «ስታድግ ምንድ ነዉ መሆን የምትፈልገዉ?» ተብሎ ሲጠየቅ ፈጥኖ ይመልሳል።«ጋዜጠኛ ብሎ።»

የጋዜጠኞቹ ታሪክ።ቅዳሜ ነዉ።ወደ አስከሬን ማከማቻነት ያልተቀየሩት መስጊዶች ወደ መሸሸጊያነት ተለወጡ።የአልጀዚራዉ ጋዜጠኛ ካይሮ መስጊድ ዉስጥ የነበረች ረዳቱን ወይም መረጃ አቀባዩን በሥልክ ጠየቃት።ምን እየሆነ ነዉ-የመጀመሪያዉ ጥያቄ ነበር።

«ባሁኑ ጊዜ ወደ መስጊዱ ዉስጥ እየተኮሱ ነዉ።»

«ከኛ ጋር ለመነጋገር-እንዴዉ ለመሆኑ ደሕና ቦታ ነሽ?»

«በጭራሽ፥ በጭራሽ እዚሕ መስጊድ ዉስጥ ማንም ሰዉ ዋስትና የለዉም። እየተኮሱብን ነዉ።ተኮሱ።-----»

የዋሁ አይነሥዉር ሕፃን-እናቱ «ዓይን እያለዉ የታወረ ባለችዉ ሐገር ጋዜጠኛ መሆን ይፈልጋል።

የፆም ፀሎት ማዘዉትሪያ ቅዱሳን መስጊዶች፥ከቅድሱ ኢድ አልፈጢር በሕዋላ፥ ከሸዋል ኢድ ዋዜማ ጀምሮ አንድም ወደ አስከሬን ማከማቻነት፥ አለያም ወደ ሰዎች መግደያ ቄራነት ተለዉጠዋል። ለወትሮዉ በፍልሰታ ጷሚዎች የሚጨናነቁት፥ የፈጣሪ መማፀኛ ቅዱስ አቢያተ-ክርስቲያናት ይጋያሉ። አደበባዮች፥ የሰላማዊ ሠልፍ ማዕከላት የነበሩ አደባባዮች በተቦጫጨቀ፥ የሰዉ አካል፥ በሰዉ ደም ጎድፈዋል።በንዳጅ ቀርንተዋል።

የቀድሞዉ ፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲና መንግሥታቸዉ የሚጠበቅባቸዉን ያሕል አለመስራታቸዉ፥ ባለመስራታቸዉ የሕዝብ ተቃዉሞ የገጠማቸዉ መሆኑ ይታወቅ ነበር።ሙርሲ እና የሙርሲን የፖለቲካ ማሕበር የነፃነት እና የፍትሕ ፓርቲን የወከሉት የምክር ቤት አባላት በታሪካዊቱ ሐገር የምዕተ-ዓመታት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ ድምፅ መመረጣቸዉ ግልፅ ነዉ።

የነፃነት እና የፍትሕ ፓርቲ-የሙስሊም ወንድማማቾች ማሕበረሰብ የፖለቲካ ክንፍ መሆኑም እርግጥ ነዉ።የሙስሊም ወንድማማቾች ማሕበረሰብ ወይም የነፃነትና የፍትሕ ፓርቲ አባላት ሥልጣን ላይ በነበሩበት አንድ ዓመት ጊዜ ተቃዋሚዎቻቸዉ የሚተቹ፥ የሚወቅሷቸዉን ያክል በሕዝብ ድምፅ የተመረጡ የግብፅ መሪዎች ነበሩ።
ኮሎኔል ገማል አብድናስር የመሯቸዉ የግብፅ የጦር መኮንኖች ንጉስ ፋሩቅን ከሥልጣን አስወግደዉ ሥልጣን ከያዙበት ከ1952 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) ጀምሮ ሙርሲ እስከተመረጡበት ጊዜ ድረስ የግብፅ ጦር ከስልጣን ተለይቶ አያዉቅም።የግብፅ ሁለንተናዊ ሒደት በያኝም ነዉ። አንድ የፖለቲካ ተንታኝ ጦሩን የተቋማት ሁሉ የበላይ ተቋም ይሉታል።
ጀርመናዊዉ የፖለቲካ ተንታኝ ሽታይንባሕ እንደሚሉት ደግሞ ፕሬዝዳት ሆስኒ ሙባረክ በተወገዱ ማስግሥት ሥልጣኑን የወረሱት ፊልድ ማርሻል ተንታዊ እና ጄኔራል አልሲሲን የመሳሰሉ ተከታዮቻቸዉ ጦሩ የፖለቲካ ሥልጣኑን ቢያጣ እንኳን ምጣኔ ሐብቱን እንደያዘ ግብፅን እንደተቆጣጠረ ይቀጥላል የሚል ተስፋ-እምነትም ነበራቸዉ።
«ጦሩ ምጣኔ ሐብቱን እና ማሕበራዊዉን መስክ እንደተቆጣጠረ ለመቀጠል ትልቅ ፍላጎት ነበረዉ ማለት ይቻላል።ጦሩ በሐገሪቱ ምጣኔ ሐብት ትልቅ ተሳትፎ ካላቸዉ ሐይላት ግንባር ቀደሙ ነዉ።ይሕንን አጡት።ሙርሲ የያኔዉን ማርሻል ታንታዊን ስልጣን ሲያስለቅቁ ጦሩ የሚፈልገዉን አጣ።»
በናስር እምነት፥ አላማ ከተቀረፁት አዳዲሶቹ ናስሮች ወይም ፈርዖኖች ጄኔራል አብዱል ፈታሕ አል ሲሲ ብቸኛዉ ፈርዓንነታቸዉን ለማረጋገጥ አስር ወር ጠብቀዉ፥ ተቃዉሞን ተተግነዉ ፕሬዝዳት መሐመድ ሙርሲን በሐይል ከስሥልጣን አስወገዱ።ነሐሴ-ሰወስት።አል-ሲሲ ሕገ-መንግሥት ሽረዉ፥ ምክር ቤት ዘግተዉ፥ ሌላ መሪ ሲሾሙ እኒያ በግብፅ ሕዝብ ተመርጠዉ ግብፅን ሲመሩ የነበሩት ወገኖች በሕዝብ የተጠሉ፥ ግብፅን ለዉድቀት የዳረጉ ሙስሊም ፅንፈኞች ተብለዉ ተወነጀሉ።ታሠሩ። ተገደሉም።
ለሙስሊም ወድማማቾች ግን አዲስ ነገር አይደለም።ሼኽ ሐሰን አሕመድ አብዱረሕማን መሐመድ አል-ባና በ1928 ሲመሠርቱት የብሪታንያ ቅኝ ገዢዎችን የሚቃወም፥ የሙስሊሞችን ሐይማኖት፥ የአረቦችን ባሕል የሚጠብቅ፥ ድሆችን የሚረዳ ማሕበረሰብ ነበር።ባጭር ጊዜ ዉስጥ በርካታ አባላት አሰባስቦ፥ በ1936 የፍልስጤሞችን የነፃነት ጥያቄ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደአደባባይ ሠልፍ ለዓለም ሲያሳዉቅ ሠልፈኛዉ በብሪታንያ ቅኝ ገዢዎች ጦር ተደፈለቀ።

በ1948ቱ የአረብ እስራኤሎች ጦርነት ወቅት አባላቱን አዝምቶ እሲኪዋጋ ድረስ ከግብፁ ንጉስ ፋርቁ መንግሥት ጋር ወዳጅ ባይሆኑ ጠላት አልነበሩም።የጦርነቱ ሽንፈት ያስቆጣዉ ግብፃዊ የንጉሱን ሥርዓት እየተቸ ሙስሊም ወድማማቾች ማሕበረሰብን ማሞጋገስ ሲጀምር ፋሩቅ ማሕበረሰቡን አገዱ።ንብረቶቹን ወረሱ።አብዛኛ መሪዎቹን አሠሩ።

የፋሩቅን አገዛዝ በተለይም በሙስሊም ወድማማቾች ላይ የተወሰደዉን የሐይል እርምጃ የሚቃወም አንድ ተማሪ ጠቅላይ ሚንስትር መሐመድ አን ኑክራሺ ፓሻን በጥይት ደብድቦ ገደላቸዉ።ወዲያዉ የሙስሊም ወንድማማቾች መስሯችና የመጀመሪያዉ መሪ አል-ባና ባደባባይ ተረሸኑ።

ሙስሊም ወድማማቾች በድፍን የዓረብ አለም ተዘርቷል።ግን ንጉስ ለሚጠሉት በተለይ የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎችን ለሚያወግዙት ለቀድሞዉ የሊቢያ መሪ ለኮለኔል ሙዓመር ቃዛፊም፥ ለንጉስ ፈሕድ ወይም ለንጉስ አብደላሕም እኩል ጠላት ነዉ።ናስር እና ተከታዮቻቸዉ የፋሩቅን መንግሥት ማስወገዳቸዉን ደግፎ ነበር።ናስር ሥልጣናቸዉን ካደላደሉ በሕዋላ የሙስሊም ወድማማቾች መሪ-አባላትን የሚገድሉትን ገድለዉ ሌላዉን በየእስር ቤቱ አጎሩ።

የአል-ቃኢዳ መስራች ኦስማ ቢላን የሙስሊም ወድማማቾችን መርሕ ያወግዝ ነበር ይባላል።የኦስማ ቢን ላንደን ቀንደኛ ጠላቶችን ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤልም ሙስሊም ወድማማቾችን ይቃወማሉ። በዚሕም ይሁን በሌላ ምክንያት ጄኔራል አል ሲሲ የመሩትን መፈንቅለ መንግሥት ያወገዘ ቀርቶ «መፈንቅለ መንግሥት» ለማለት እንኳን የደፈረዉ አፍሪቃ ሕብረት ብቻ ነዉ።

የግብፅ ጦር መፈንቅለ መንግሥቱን የተቃወሙ የሙስሊም ወንድማማቾችን አባላትና ደጋፊዎችን በጅምላ ሲያስር፥ አምስት፥ አስር፥ ሃያ፥ ሠላሳ እያለ ሲገድል ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች መጮኸቸዉ አልቀረም።አንዳድ የሐያሉ ዓለም ፖለቲከኞች ጥንቃቄ እንዲደረግ መጠይቃቸዉ ካይሮ እየደረሱ መመለሳቸዉም እዉነት ነዉ።የጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ጊዶ ቬስተርቬለ ባለፈዉ ሳምንት ያሉትን ከሳምንታት በፊት ብለዉት ነበር።

ከዚሕ ባለፍ በገዳዮች ላይ ቆንጣጭ እርምጃ ለመዉሰድ የሞከረ፥እንዲወሰድ የጠየቀ ሐያል መንግሥት የለም።ጋዜጣኛዉ አዉቆም፥ የሚያዉቁ በትክክል ያሉት እየመሰለዉም «ኢስላሚስት ወይም እስላማዉያን፥ ሙስሊማዉያን» የሚላቸዉ ሙስሊም ወንድማማቾች ከሥልጣን በመወገዳቸዉ የሙስሊሞች የበላይ ጠባቂ ከሚባሉት ከሳዑዲ አረቢያ ገዢዎች እኩል የተደሰተ የለም።

የሳዑዲ አረቢያ፥ የባሕሬን፥ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ነገስታት፥ አሚሮች ወይም ሱልጣናት የሕዝብ አመፅ፥ ተቃዉሞንም፥ በሕዝብ የተመረጠ መንግሥትንም፥ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዘ-የጦ መኮንኖችንም እኩል ይፈራሉ፥ ይጠላሉም።ጄኔራል አል-ሲሲ የሙስሊም ወድማማቾቹን መንግሥት በሐይል በማስወገዳቸዉ ግን ለግብፅ ጦር የአስራ-ሁለት ቢሊዮን ዶላር ርዳታ አስታቅፈዉታል።

የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎችና ተባባሪዎቻቸዉ፥ ምናልባት ምዕራባዉያን ለግብፅ የሚሰጡትን ድጋፍ ቢያቋርጡ በሚጎድለዉ ለመሙላት ዛሬ ቃል ገብተዋል። ሐያሉ ዓለም ይሕን ያዉቃል። አልተቃወመዉም። አል-ሲሲ የሚያዙት ጦር ከአየር በሔሊኮብተር፥ ከፎቅ ባነጣጥሮ ተኳሽ፥ ከመሬት በታክ መትረየስ ሠላማዊ ሠልፈኞችን መግደሉን ፕሬዝዳት ባራክ ኦቦባ አዉግዘዋል።ዩናይትድ ስቴትስ በየዓመቱ ለግብፅ ጦር የምታስታጥቀዉን የአንድ ነጥብ ሰወስት ቢሊዮን ዶላር ጦር መሳሪያ ለማቆም ግን አልቃጡም።

ከመራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል እስከ ፍራንሷ ኦሎንድ፥ ከጠቅላይ ሚንስትር ቶኒ ብሌር እስከ ካትሪን አሽተን የሚገኙ የአዉሮጳ መሪዎች ግድያዉን ተቃዉመዋል።በግብፅ ጦር ላይ ማዕቀብ ለመጣል ግን እስካሁን አንዳቸዉም አልደፈሩም።የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ገና በጉዳዩ ላይ ለመምከር ለሮብ ቀጠሮ አላቸዉ።ግብፅ በርግጥ ዚምባቡዌ አይደለችም።

የእስራኤል ሠላም በካይሮ ደሕንነት ላይ የተመሠረተ ነዉ።ከአራት ከመቶ የሚበልጠዉ የዓለም ሸቀጣሸቀጥ፥ ከስምንት ከመቶ የሚበልጠዉ የዓለም ነዳጅ ዘይት የሚተላለፈዉ በሲዊስ ቦይ ነዉ።ሐያሉ ዓለም «ከመርሕ ወይም ከሞራል» ይልቅ «ጥቅም»ን አስቀድሞ ሲያለምጥ ያቺ ለጥቅሙ የሚጓጓላት ሐገር፥ የሚሳሳለትን ጥቅም ጨርሶ ወደሚያጣበት አዘቅት እንዳትደፋ በርግጥ ያሰጋል።

የግብፅ ገዢዎች ግን «ያበጠዉ-ይፈንዳ» አይነት እልሕ የተጋቡ ይመስላሉ።ዛሬ ከወደ ካይሮ እንደተሰማዉ በሕዝብ አመፅ ከሥልጣን የተወገዱት እና ፍርድ ቤት የተበየነባቸዉ ሆስኒ ሙባረክ እንደሚፈቱ ተዝግቧል። ጠመንጃ የታጠቁት ፈርዖኖች፥ እልሕና ፅናት ከሰነቁት ተቃዋሚዎቻቸዉ ጋር የገጠሙት ፍልሚያ እንደቀጠለ ነዉ።

ባለፈዉ ሮብ ናሕላ አደባባይ የጀመረዉ ግድያ መሳጂዶችን፥ አብያተ-ክርስቲያናትን፥ ወሕኒ ቤቶችን በደም፥ አካል፥ በእሳት ከሰል አልብሶ ድፍን ካይሮን አዳርሶ፥ አሌክሳንደሪያን፥ ኢስማኢሊያን፥ እያለ ዛሬ ሲና በረሐ-ወርዷል።ግብፅ ታዉራለች፥ ወይስ አብዳለች? ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ
Source: http://www.dw.de/
 Addis Admass 
*ግብረሰዶማዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ “ሬንቦ” የተባለ ማህበር አቋቁመዋል
*በግብረሰዶማውያን ዙርያ የተካሄዱ ጥናቶች አዳዲስ መረጃዎችን ይፋ አድርገዋል
*ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥቃት ሰለባ ሆነዋል
*ኢትዮጵያውያን ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ለገበያ ቀርበዋል
            ከወራት በፊት እዚህ አዲስ አበባ ከተማችን ውስጥ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመው በአንድ ስመ-ጥር የወንዶች ልብስ መሸጫ ቡቲክ ውስጥ ነው፡፡ ወጣቱ በቡቲኩ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት ከጀመረ ቆየት ብሏል፡፡ በአለባበሱ ሽቅርቅርና ዘመናዊ ነው፡፡ ወደ ቡቲኩ የሚመጡትን ደንበኞች በፈገግታና በትህትና እየተቀበለ ያስተናግዳል፡፡ ደንበኞች የፈለጉትን ልብስ አስወርደው ለመለካት ወደ መልበሻ ክፍል ሲገቡ በዓይኑ ይከተላቸዋል፡፡ በገቡበት የመልበሻ ክፍል መጋረጃ ላይ አይኖቹን
ተክሎ ለደቂቃዎች እንደሚቆይ የቡቲኩ ባለቤት ብዙ ጊዜ ታዝቦታል፡፡ ሆኖም ደንበኞቹ አዲሱን ልብስ ለብሰው ሲወጡ ለማየት ከመጓጓት የተነሳ እየመሰለው በዝምታ ያልፈዋል፡፡ “ለምን እንዲህ ታያለህ?” ብሎ ጠይቆት አያውቅም
፡፡
አብዛኛዎቹ የቡቲኩ ደንበኞች ወንዶች ናቸው፡፡ እጅግ ጥቂት ሴቶች፤ ለፍቅረኞቻቸው፣ ለባሎቻቸውና ለወንድሞቻቸው ልብስ ለመግዛት አሊያም ለማጋዛት ካልመጡ በቀር የሴት ዘር ወደ ስፍራው ዝር አይልም፡፡
የቡቲኩ ባለቤት አብዛኛውን ጊዜ ከቡቲኩ አይጠፋም፡፡ አልፎ አልፎ ከውጪ የመጡ ዕቃዎችን ለመረከብ፣ ክፍያ ለመፈፀምና መሰል ለሆኑ ጉዳዮች ወጣ ማለቱ ግን አይቀርም፡፡ የቡቲኩ ባለቤት ከወራት በፊት ተመሳሳይ ጉዳይ ገጥሞት ነው ቡቲኩን ለሰራተኛው ትቶለት የሄደው፡፡ ባለቤቱ ከሄደ በኋላ ዕድሜው በሃያዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚገመት አንድ ወጣት ልብስ ለመግዛት ወደ ቡቲኩ ገባ፡፡ የቡቲኩ ሰራተኛ አይኑን ወጣቱ ላይ ተከለ፡፡ ወጣቱ ረዘም፣ ቀጠን ያለና ያለ ዕድሜው የተንቀዋለለ አይነት ነው፡፡ የሚፈልገውን ጅንስ መረጠና ወደ መለኪያ ክፍሉ ገባ፡፡ የቡቲኩ ሰራተኛ ጊዜ አላጠፋም፡፡ የቡቲኩን በር ከውስጥ ቆልፎ ወደ መለኪያው ስፍራ ሄደና መጋረጃውን ገለጠው፡፡ ወጣቱ ከለበሰው የውስጥ ሱሪ በስተቀር ከወገቡ በታች እርቃኑን ነበር፡፡ ሊለካው በያዘው ጅንስ ሱሪ አፉን አፈነው፡፡ ያላሰበው ነገር የገጠመው ወጣት፤ ለመጮህ፣ ለመታገልም ሆነ ለማምለጥና ለመከላከል አቅም አልነበረውም፡፡ እንደ ብረት ጠንክሮ ከያዘው እጅ ለማምለጥ በሞት ሽረት ትግል ቢፍጨረጨርም አልሆነለትም፡፡ እዛው የልብስ መለኪያ ክፍል ውስጥ አስገድዶ ደፈረው፡፡
የቡቲኩ ባለቤት ከጉዳዩ ተመልሶ ሱቁ ሲደርስ ቡቲኩ ያለወትሮው ተዘግቷል፡፡ ሁኔታው ያልተለመደ በመሆኑ ቡቲኩን በራሱ ቁልፍ ከመክፈቱ በፊት ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ፡፡ ፖሊሶች በስፍራው ደርሰው በሩ ሲከፈት ተገድዶ የተደፈረው ወጣት፤ እዛችው የልብስ መለኪያ ክፍል ውስጥ በትውከትና በሰገራ ተጨማልቆ ወድቋል፡፡ ሌላ በቡቲኩ ውስጥ የተገኘ ሰው ግን አልነበረም፡፡ ባለቤቱ በሁኔታው እጅግ ደነገጠ፡፡ ፖሊሶች እሱን በቀጥጥር ስር አዋሉና ወጣቱን ወደ ህክምና ሥፍራ ላኩ፡፡ የቡቲኩ ባለቤት የሠራተኛውን ባህሪና ለደንበኞቹ የነበረውን አቀባበልና ስሜት ቀስ እያለ ማስታወስ ጀመረ፡፡ እንዴት ይህንን ነገር ሳልጠረጥር ቀረሁ ሲልም ተቆጨ፡፡ ግን ሁሉም ነገር ጅብ ከሄደ---- ሆኖበታል፡፡ ለቀናት በፖሊስ ጣቢያ ቆይቶ፣ በዋስ ተለቀቀ፡፡ ወንጀል ፈፃሚው ግለሰብ ግን ዛሬም ድረስ ዱካው አልተገኘም፡፡
እንዲህ ያሉ ታሪኮች ዛሬ በአገራችን በተለይም በመዲናችን የተለመዱ ተግባራት ሆነዋል፡፡ ድርጊቱ ከዕለት ወደ እለት እጅግ በሚዘገንንና በሚያስደነግጥ ሁኔታ እየተስፋፋ ነው፡፡ ህፃናት ልጆች በትምህርት ቤታቸው ውስጥ በሚያስተምሯቸው መምህራን እየተደፈሩ ነው፡፡
ለዚህ ደግሞ በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ሰባተኛ ወንጀል ችሎት እየታየ ያለውና በ“ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ” መምህራን ተፈፀመ የተባለው የግብረሰዶም አስገድዶ የመድፈር ወንጀል የቅርብ ጊዜ አብነት ነው፡፡ ስድስት መምህራን የአስርና የአስራ አንድ አመት ዕድሜ ባላቸው ሁለት ህፃናት ላይ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው፣ ጉዳዩ በክስ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት ድርጊቱ እጅግ እየተስፋፋ ሲሆን በማህበረሰቡም ላይ የስነ ልቦናና የማህበራዊ ግንኙነት እንዲሁም፣ የትምህርት ማቋረጥና የጤና ችግር እያስከተለ እንደሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ሴቶችና ወጣቶች ቢሮ በቅርቡ የተደረገ ጥናት ይጠቁማል፡፡ ጥናቱ በአሁኑ ወቅት ተመሳሳይ ፆታን ለወሲብ ማሰብ እጅግ እየተለመደ መምጣቱንና ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ በመፈፀም ሥራ የሚተዳደሩ ሰዎች መበራከታቸውን ይፋ አድርጓል፡፡ የዚህ ችግር ሰለባዎች በአብዛኛው ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት፣ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እንዲሁም የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች፣ በወሲብ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሰዎችና በማረሚያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ የህግ ታራሚዎች መሆናቸውንም ጥናቱ አረጋግጧል፡፡
የግብረሰዶማዊነት ችግር የምዕራባውያንና የሰለጠኑት አገራት ችግር ብቻ እንደሆነ መቁጠር፣ ህብረተሰቡን ለአስከፊ ጉዳት እንደዳረገው የጥናት ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡ ይሄ ዓይነቱ አዝማሚያ መዘነጋት በመፍጠር ወላጆች ስለ ልጆቻቸው አዋዋል፣ የባህርይ ለውጥና አለባበስ እንዳያስተውሉና ወቅታዊ እርምጃዎች እንዳይወስዱ ያደረገ ሲሆን ልጆችንም እጅግ ለከፋ ጉዳት እያጋለጠ ነው፡፡ ትናንት በሩቁ ስንሰማው የነበረው ግብረሰዶማዊነት፤ ዛሬ የእያንዳንዳችንን ቤት የሚያንኳኳ የሁላችንም ሥጋት ሆኗል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት በ“ሴቭ ዘ ቺልድረን ካናዳ” እና በ“ብራይት ፎር ቺልድረንስ ቮለንተር አሶሴሽን” ትብብር የተካሄደ ጥናት እንዳመለከተው፤ በከተማችን አዲስ አበባ ከሚፈፀሙ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች መካከል 22 በመቶ የሚደርሱት የተፈፀሙት በወንዶች ላይ ነው፡፡ እነዚህ ወንዶች የተደፈሩትም ተመሳሳይ ፆታ ባላቸው ሰዎች ነው፡፡ ጥቃቱ ከተፈፀመባቸው አብዛኛዎቹም ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ናቸው፡፡ ከጥቃቱ ፈፃሚዎቹ መካከል 43.7 በመቶ ያህሉ የጥቃቱ ሰለባዎች የቅርብ ሰዎች እንደሆኑ ጥናቱ አመልክቷል፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ማህበር ከክፍለ ከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የግብረ ሰዶማዊነት መስፋፋትን ለማውገዝ ሰሞኑን አንድ ትልቅ ጉባዔ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በገነት ሆቴል በተዘጋጀውና በሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ የኪነጥበብ ባለሙያዎችና የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት በዚህ ጉባዔ ላይ “ዩናይትድ ፎር ላይፍ ኢትዮጵያ” በተባለ አገር በቀል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቧል፡፡ የድርጅቱ መሥራችና ዳይሬክተር ዶ/ር ሥዩም አንቶኒዮስ በዚሁ ጥናታቸው ላይ እንደገለፁት፣ ግብረሰዶማዊነት በአገሪቱ እጅግ በጣም በሚያስደነግጥ ሁኔታ እየተስፋፋ ነው፡፡
የመጀመሪያና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግብረሰዶማውያን መፈልፈያ ቦታዎች እየሆኑ ነው፡፡ በአንድ መንግስታዊ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ውስጥ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ፣ በሴቶች የመኝታ ክፍሎች (ዶርም) ውስጥ ከ130 በላይ የተለያዩ አርቴፊሻል የወሲብ መሣሪያዎች ተገኝተዋል፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የኮንዶሚኒየም ህንፃ ውስጥ አንድ የአስራ ሰባት አመት ወጣት በርካታ ወንድ ህፃናትን እያባባለና እያስገደደ ደፍሯል፡፡ በከተማውም ሆነ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የግብረሰዶም ተግባር እጅግ በሚያስደነግጥ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ሥዩም፣ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በተለያዩ ጊዜያት በወንዶች ፊንጢጣ ውስጥ ገብተው የቀሩ የለስላሳ ጠርሙስና ሌሎች ባዕድ ነገሮች በቀዶ ጥገና ወጥተዋል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወንዶች ከወንድ ጋር፣ ሴቶች ደግሞ ከሴቶች ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ተሠርተው ገበያ ላይ መዋላቸውንም ጠቁመዋል፡፡
በአገሪቱ የግብረሰዶማዊነት ተግባር እጅግ መስፋፋቱን አመላካች ከሆኑት ተግባራት መካከል ግብረሰዶማውያኑ “ሬይንቦ” የተባለ ማህበር በግልፅ አቋቁመው፣ አባላት ለመመልመልና ድርጊቱን ለማስፋፋት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ዶ/ር ሥዩም ተናግረዋል፡፡ ድርጊቱ በአገሪቱ እንዲበራከትና እንዲስፋፋ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል በSex tourism አማካኝነት ወደ አገራችን የሚገቡ የውጪ ዜጐች፣ ከኢትዮጵያ ውጪ ኖረው የሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ወደተለያዩ አገራት ለንግድና ለሌሎች ሥራዎች የሚንቀሳቀሱ ሰዎች እና የልቅ ወሲብ ፊልሞች መበራከት እንደሆኑ ተጠቁሟል፡፡
አሁን በአገሪቱ ውስጥ ባለው ሁኔታ የሴት ግብረሰዶማዊያን (ሴት ለሴት ግንኙነት የሚፈፅሙ) በቁጥር አነስተኛ መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር ሥዩም፣ የወንድ ግብረሰዶማውያን ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ነው ብለዋል፡፡ በሆነ አጋጣሚ ወይም በመደፈር ወደ ግብረሰዶማዊነት ህይወት የሚገቡ ወጣቶች ወይም ህፃናት ድርጊቱን እንዳያቆሙና ከችግራቸው እንዳይላቀቁ ግብረሰዶማውያኑ ያስፈራሯቸዋል - “አንድ ጊዜ በፊንጢጣ ግንኙነት ማድረግ ከጀመርክ ፊንጢጣ ውስጥ የሚፈጠር እጭ ይኖራል፡፡ እጩ ደግሞ በየጊዜው ስፐርም ማግኘት ይኖርበታል፣ ያለዚያ ግን አንጀትህን ይቦድሰውና ለከባድ የጤና ችግር ትጋለጣለህ” እያሉ፡፡ በዚህ ምክንያትም አንድ ጊዜ የችግሩ ሰለባ የሆኑ ሰዎች ከድርጊቱ ለመላቀቅና ወደ ትክክለኛው ህይወት ለመመለስ አይፈልጉም፡፡ ይህ አባባል ግን ፈፅሞ ከእውነት የራቀና ግብረሰዶማውያኑ የአባላት ቁጥራቸውን ለማበራከት የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ ይህንን እጅግ አደገኛ በሆነ ፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን የግብረሰዶማዊነት ተግባር ለመግታት ከፍተኛ ንቅናቄ ማድረግ እንደሚገባውና እያንዳንዱ ሰው በቤቱ ውስጥ በልጆቹ ላይ የሚታዩ ለውጦችን ትኩረት ሰጥቶ በመከታተል፣ ልጆቹ ወደማይመለሱበት ጥፋት ውስጥ ከመግባታቸው በፊት ሊታደጋቸው ይገባል ሲሉ ዶ/ር ሥዩም ተናግረዋል፡፡
ግብረሰዶማውያን በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች የራሳቸው መገናኛ ሆቴሎች፣ መቀጣጠሪያ ካፌዎች፣ የተመሳሳይ ፆታ ወሲብ መፈፀሚያዎች፣ መዝናኛና ማሣጅ ቤቶች እንዳሏቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ በመፈፀም ሥራ የሚተዳደሩ ግብረሰዶማውያን (ቆሚታዎች ነው የሚባሉት) በአብዛኛው በቦሌ አካባቢ የሚገኙ ሲሆን በተለይ ደግሞ ፍሬንድሺፕ ህንፃ፣ ቦሌ ድልድዩ አጠገብና፣ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አካባቢዎች ይጠቀሳሉ፡፡ ፒያሣ የሚገኙ ጥንታዊ ሆቴሎችና ረዘም ያለ ዕድሜን ያስቆጠረ አንድ ካፌም የግብረሰዶማውያን መገናኛ፣ መቀጣጠሪያና መተዋወቂያ ሥፍራዎች ናቸው፡፡ ከጥናቱ ለመረዳት እንደተቻለው፣ ግብረሰዶማውያኑ አብዛኛውን ጊዜ ከተለመዱት የወንዶች አለባበስና ስታይል ለየት ያሉና በቀላሉ አይን የሚስቡ ነገሮችን ማድረግ የሚያዘወትሩ ሲሆኑ አብዛኛዎቹ በግራ ጆሮአቸው ላይ ሎቲ ያደርጋሉ፡፡ ጠበብ ያሉ (ታይት) ሱሪዎችን፣ ሰውነትን በተለይም ደረትና ክንድን የሚያጋልጡ ልብሶችን መልበስና ሱሪያቸውን ዝቅ በማድረግ ፓንታቸውን እያሣዩ መሄድንም ያዘወትራሉ፡፡ ቅንድባቸውን ለመቀንደብ፣ ጥፍራቸውን ለመሞረድና የእግር ተረከዞቻቸውን ለመሠራት አብዛኛዎቹ ግብረሰዶማውያን የሴቶች የውበት ሳሎኖችን ያጣብባሉ፡፡ ብዙውን ጊዜም ነጣ ያሉ (ድፍን ነጭ) ካልሲዎችን በክፍት ጫማ ማድረግን ያዘወትራሉ፡፡ ሁልጊዜም ንፁህና መልካም ጠረን እንዲኖራቸው ይተጋሉ፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኙ በርካታ ፔኒሲዮኖች ለግብረሰዶማውያን አገልግሎት በመስጠት ተግባር ላይ እንደሚሳተፉም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለግብረሰዶማውያንነት በአብዛኛው ተጋላጭ የሚሆኑት በወላጆቻቸው የተረሱ ህፃናት፣ ከአንድ ወላጅ ጋር ብቻ የሚኖሩ፣ የጐዳና ተዳዳሪዎች፣ ስደተኞች፣ የአዕምሮ ውሱንነት ችግር ያለባቸው ሰዎች፣ የአካል ጉዳተኞችና በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥና በማረሚያ ቤቶች ውስጥ ያሉ ሰዎች መሆናቸው በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡ የግብረሰዶማዊነት ችግር ለኤችአይቪ፣ ለወሲባዊ ግንኙነት ፍላጐት ለማጣት፣ ራስን ለመጥላት፣ ከሰዎች ለመገለልና ለብቸኝነት፣ ለጭንቀትና ፍርሃት እንዲሁም ከአስራ አራት በላይ ለሚሆኑ የጤና ችግሮች እንደሚያጋልጥ ተገልጿል፡፡ ይህ ወቅታዊ ጥሪ ለወላጆች፣ ለመንግስትና ለህብረተሰቡ እንዲሁም ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የቀረበ ሲሆን ጉዳዩ አፋጣኝ የመፍትሔ እርምጃ ካላገኘ እጅግ አደገኛ ለሆነ የማህበረሰባዊ ቀውስ ይዳርጋል፡፡
መታሰቢያ ካሣዬ 
 
የሴትየዋ የፊት ገፅታ የዕድሜያቸውን መግፋት ቢያጋልጥም በተለያዩ ሜካፖችና ቅባቶች እንዲሁም በዘመናዊ አለባበሣቸው ወጣት ለመምሰል ጥረዋል። እንዲህ ያሉ ወይዘሮዎች በአብዛኛው አንቱ መባልን አጥብቀው እንደሚጠሉ ያውቃል። ለዚህም ነው “አንቺ” እያለ ማናገር የጀመረው። አዲሷ የጂም ተማሪ፣ ወጣቱ ላይ ዓይናቸውን ጥለዋል፡፡ ዘንካታነቱና የስፖርተኛ ቁመናው ማርኳቸዋል፡፡
   የተስተካከለ ቁመናውና የስፖርተኛ አቋሙ የብዙ ሴቶችን ዓይን ይስባል፡፡ ጐተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ ጂምናዚየም ውስጥ ተቀጥሮ ደንበኞቹን ስፖርት ያሰራል፡፡ በተግባቢነቱ፣ በተጨዋችነቱና በሰው አክባሪነቱ ሁሉም ይወዱታል፡፡ ከሥራው ቦታ ሳይርቅ ጎተራ ላንቻ አካባቢ ከግለሰብ በተከራየው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ እየኖረ ሳለ ነው ህይወቱን የሚቀይር አንድ አጋጣሚ የተፈጠረው፡፡ ያቺን ዕለት አይረሳትም፡፡ ሴትየዋ ጠና ያሉ ናቸው - ከ50 ዓመት በላይ ይሆናቸዋል፡፡ የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ሁለመናቸው ይናገራል፡፡ የጂም ደንበኛ ሆነው ሲመዘገቡ ምንም የተለየ ነገር ይፈጠራል ብሎ አላሰበም፡፡ እንደ ሁልጊዜው በፈገግታና በትህትና ተቀብሎ አስተናገዳቸው፡፡
የለበሰው ቲ-ሸርትና ቁምጣ በጡንቻዎቹ ተወጣጥሯል፡፡ አይናቸውን ከሱ ላይ መንቀል ተሣናቸው፡፡ በስፖርት ሰበብ መቀራረብና መነካካት መኖሩን ደግሞ ወደውታል፡፡ ከወገብሽ ጎንበስ እግርሽን ከፍ ክንድሽን ዘርጋ ከደረትሽ ገፋ እያለ ---የሚሰሩትን እንቅስቃሴ
ይነግራቸዋል አንድ ሁለት አንድ ሁለት እያለ፡፡ እሳቸው ግን ብዙም አይሰሙትም፡፡ ሁለመናቸው የሚነቃቃው ቀረብ ብሎ ሲያሰራቸው ነው - ወገባቸውን ደገፍ፣ ክንዳቸውን ያዝ፣ እግራቸውን ሳብ እያደረገ ሲያንቀሳቅሳቸው አንዳች የተለየ ዓለም ውስጥ የገቡ ይመስላቸዋል፡፡ የሰራ አካላቸው ይፍታታል። ፊታቸው ይበራል፡፡ ጨዋታቸው ይደራል፡፡ ለመግባባት ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ ሲውል ሲያድር መግባባታቸው እየጠነከረ፣ግንኙነታቸው የተለየ መልክ እየያዘ መጣ፡፡
ወጣቱ አሰልጣኝ የሴትየዋን ስሜት ተረድቶታል፡፡ እሳቸው በቀደዱለት ቦይ መፍሰሱን አልጠላውም - የት እንደሚደርስ ባያውቀውም፡፡ ከልጅነት ጀምሮ ከሚያውቀው የድህነት ህይወት ያላቅቀው እንደሆን ማን ያውቃል? ሴትየዋ የስፖርት ሰዓታቸውን ከቀን ወደ ምሽት ሲያዛውሩትም ለምን ብሎ አልጠየቃቸውም፡፡ ልሸኝህ የሚለው ነገር የመጣውም ይሄኔ ነው፡፡ ቤቴ ቅርብ ነው ብሎ መከራከር አልፈለገም፡፡ ወይዘሮዋ ብልሃተኛ ናቸው፡፡ መንገዱን ማርዘምያ መላ አላጡም፡፡ ይሄ ኮረኮንች ነው፣ያኛው እግረኛ ይበዛዋል እያሉ ጨለማ ጨለማውን ዙሪያ ጥምጥም ይዘውት ይሄዳሉ። እንዲያም ሆኖ መድረስ አይቀርም፡፡ “ደህና እደሪ” ብሎ ከመኪና ሲወርድ፣ ጎተት አድርገው ጉንጩን መሳም አስለምደውታል፡፡ መሳሳሙ ከጉንጭ ወደ ከንፈር ለመዝለል ጊዜ አልፈጀበትም፡፡ መሸኛኘት ብቻ ሳይሆን አብሮ ማምሸትም ተጀምሯል፡፡ እራት ግብዣው ቀልጧል፡፡ ውድ ውድ ስጦታዎች እየጎረፉለት ነው፡፡ ረብጣ ብሮች ሸጎጥ ይደረግለታል።
ወጣቱ እስራው ቦታ ድረስ ሰተት ብሎ የመጣለትን ሲሣይ በደስታና በእልልታ የማይቀበልበት ምክንያት አልታየውም፡፡ መጪውን ያሳምረው እንጂ፡፡ ሴትየዋ በጥቂት ሣምንታት እጃቸው ውስጥ የገባላቸውን ግዳይ፣እያንከበከቡ ወደ መኖርያ ቤታቸው ይወስዱ ጀመር፡፡ አብሮ መዋል አብሮ ማደር መጣ፡፡ የጎመዡበትን ዘንካታ ቁመናና የተደላደለ ሰውነት፣ እንደልባቸው አገኙት፡፡ በፈርጣማ ክንዱ አቅፎ በትኩስ የወጣትነት ትንፋሹ አሞቃቸው፡፡ እርጅና ተባርሮ ወጣትነት ዳግም ተመልሶ የመጣ መሰላቸው፡፡ ዓለማቸውን አዩ፡፡ እሱም የምኞቱን አገኘ፡፡ 300ሺህ ብር አውጥተው የገዙትን አዲስ ሞዴል ያሪስ መኪና በስሙ አዛውረው ሰጡት፡፡ ከኪራይ ቤት አውጥተው በ440ሺህ ብር ኮንዶሚኒየም ገዝተው አስገቡት፡፡ ፍቅራቸው ደራ፡፡
የሴትየዋ ባለቤት ከሁለት አመት በፊት ነው በድንገተኛ ህመም የሞቱት፡፡ ሁለት ልጆቻቸው ያሉት ደግሞ ጣሊያን ነው፡፡ እናም ምንም የሚያሳስባቸውና ነፃነታቸውን የሚጋፋ ነገር አልነበረም፡፡ ወይዘሮዋና ወጣቱ ያለገደብ ደስታቸውን አጣጣሙት፣ አንድም የቀራቸው የመዝናኛ ቦታ የለም - ሁሉንም በየተራ አዳረሱት፡፡ ወጣቱ የጂም አሰልጣኝ ሥራውን ለቆ ወይዘሮዋን መንከባከብ የሙሉ ጊዜ ሥራው አደረገው፡፡ ከእጃቸው የማይለዩት ቦርሳቸው አደረጉት፡፡ በፍቅር ከነፉለት፡፡ የወዳጅ ዘመድ ምክር የሚሰሙበት ጆሮ አልነበራቸውም፡፡ “ኧረ ተይ --- አሁን ይሄ ጎረምሳ ልጅሽ አይሆንም?” የሚሏቸውን ሁሉ ጠሏቸው፡፡ ባስ ሲልም ራቋቸው፡፡ ጓደኞቻቸውንማ ልክ ልካቸውን ይነግሯቸዋል “ምቀኝነት ነው፤ እንዲህ የሚያደርጋችሁ --- ያጣ ወሬ ነው” አፋቸውን ያሲዟቸዋል፡፡
እሱም ታዲያ ከጓደኞቹ የሚያበሽቀው አላጣም “እናትህ ከምትሆን ሴት ጋር ምን ነካህ?” ይሉታል፡፡ እሱም “ምቀኞች! እናንተ ባታገኙ ነው” ይላቸዋል፡፡ የነብርን ጭራ አይዙም ከያዙም አይለቁም እንዲሉ በሴትየዋ ዘንድ ለመወደድና ለመታመን መትጋቱን ቀጥሏል። ብዙም ሳይቆይ የወ/ሮዋን ሱፐር ማርኬት የማስተዳደር ኃላፊነት ተረከበ፡፡ “እሷ የስኬቴ ሰበብ ናት፡፡ ያልኳትን የምታደርግልኝ የጠየኳትን የምትሰጠኝ የፈለኩትን የምታሟላልኝ ዓለሜ ናት፡፡” የሚለው ወጣቱ፤ ከእኔ የሚጠበቀው እሷን መንከባከብና በፍቅር ማጥገብ ብቻ ነው” ይላል፡፡ የቀድሞ ጂም አሰሪ ዛሬ ወጣት አባወራ ሆኗል፡፡ “ሃኒ” እያለ ከሚያቆላምጣቸው ወይዘሮ ጋር በትዳር ተሳስሮ ሲኖር ሁለት ዓመት አስቆጥሯል፡፡
ዛሬ ዛሬ ሹገር ማሚዎች የልጅ ልጆቻቸው የሚሆኑ ለጋ ወጣቶችን በገንዘባቸው አጥምደው፣ የወሲብ እስረኛ የሚያደርጉበት ሁኔታ በከተማችን የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡ ሹገር ማሚዎቹ የኢኮኖሚ አቅማቸው የዳበረ፣ የፈለጉትን ለማድረግ የሚያስችል በቂ ገንዘብ ያላቸው፣ ዕድሜያቸው ከ48-65 ዓመት የሚሆናቸው ሲሆኑ ልጅና ቤት ንብረት ኖሮአቸው ትዳራቸው በሆነ ምክንያት የፈረሰ ወይም ባሎቻቸውን በሞት ያጡ፣ አንዳንድ ጊዜም በትዳር ውስጥ ሆነው ከባሎቻቸው የሚፈልጉትን የወሲብ ደስታ በተለያየ ምክንያት ማግኘት የተሳናቸው ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሹገር ማሚዎች፤ የቡና ቤት ባለቤቶች፣ ልጆቻቸው በውጪ አገር የሚኖሩና የራሳቸው ድርጅት ያላቸው ዘናጭ ሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሴቶች በአብዛኛው የሚያጠምዱት ዕድሜያቸው ከ23-30 ዓመት የሚሆናቸው ጥሩ ቁመናና ደንዳና ሰውነት ያላቸው፣ ተግባቢና ተጫዋች ወጣት ወንዶችን ነው፡፡ ወጣት ወንዶች፤ ሹገር ማሚዎችን የሚቀርቧቸው ለገንዘባቸው ብለው ነው፡፡ ይሄን ደግሞ ራሳቸው ሹገር ማሚዎቹ ቢያውቁም ሌላ አማራጭ ግን የላቸውም፡፡ በርካታ ወጣት ወንዶችም ለጊዜያዊ ችግራቸው መወጫ እነዚህን ሴቶች የሙጢኝ ብለው ሹገር ቤቢነቱን ያሣምሩታል፡፡
“የተወለድኩት ከድሃ ቤተሰብ ነው፤ትምህርቴን እንኳን በአግባቡ መማር እንዳልችል ድህነቴ ትልቅ እንቅፋት ሆኖብኛል፡፡ ከ10ኛ ክፍል ላይ የተቋረጠው ትምህርቴ እዛው ላይ እንደቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ሥራ የለኝም፡፡ ህይወት ለእኔ አስቸጋሪ ነበረች፡፡ ተምሮ ሥራ ይዞ ይጦረናል ለሚሉት ደካማ ወላጆቼ፣ እኔው ራሴ ተጧሪና ሸክም መሆኔ በጣም ያበሳጨኝ ነበር፡፡ በተፈጥሮ የታደልኩት ጥሩ ቁመናና ደንዳናው ሰውነቴ ችግረኛ መሆኔን እየደበቁልኝ በምቾት የምኖር ያስመስሉኛል፡፡ ሰፈር አካባቢ ቆሞ መዋሉ ሲሰለቸኝ አካባቢያችን በሚገኝ አንድ ትልቅ የሴቶች ፀጉር ቤት አጠገብ የሞባይል ማደሻ ሱቅ ከፍቶ ከሚሰራው ጓደኛዬ ጋ እየሄድኩ መዋል ጀመርኩ፡፡ ይህም ከማሚ ጋር የምትዋወቅበትን አጋጣሚ ፈጠረልኝ፡፡
እውነት ለመናገር እኔ ስተዋወቃት በመጀመሪያ ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ አስቤአት ወይንም እሷ አስባኛለች ብዬ አልነበረም፡፡ ፀጉሯን ለመሠራት ወደ ፀጉር ቤቱ በመጣች ጊዜ ሁሉ መኪናዋን የምታቆመው በጓደኛዬ ሞባይል ማደሻ ሱቅ በራፍ ላይ ነበር፡፡ ትውውቃችን እያደገ ሲሄድ ረዘም ላለ ጊዜ አብሮ መጫወትና መነጋገሩን ቀጠልን፡፡ ከፀጉር ቤቱ ተሰርታ ስትወጣ፤ ሻይ እንጠጣ እያለች ይዛኝ መሄድ ሁሉ ጀመረች፡፡ ጓደኛዬ ሁኔታው እንዳላማረውና ሴትየዋ ልታጠምደኝ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አድርጋው ነው፡፡ አብረን ቆይተን ስንለያይ እንደዘበት ጃኬት ኪሴ ውስጥ የምትሸጉጣቸው ረብጣ ብሮች ስንቱን ችግሬን እንደሸፈኑልኝ እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ቤቴን ላሳይህ ብላ ይዛኝ ሄደች፡፡ ሳር ቤት አካባቢ ያለው የሴትየዋ ቤት ዘመናዊ ቪላ ነው፡፡ ቤቱ ከባሏ ጋር ፍቺ ሲፈፅሙ የደረሳት እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ ከባሏ ጋር የተለያየችው ስሜቷን ሊጠብቅላት ባለመቻሉ እንደሆነም አጫወተችኝ፡፡ ታዛዥ ፍቅረኛዋ ሆንኩ፡፡ የእናትና የልጅ ያህል የተራራቀውን ዕድሜያችንን ዘንግተን አብረን ማበዱን ተያያዝነው፡፡ ቤተሰቦቼን ከድህነት አወጣሁ፡፡ ያማረ ለብሼ ጥሩ መኪና ይዤ ወደአደኩበት ሰፈር ስሄድ መንደርተኛው ሁሉ ያከብረኛል፡፡ ለቤተሰቦቼ ሀብታም ሚስት ማግባቴን ነገርኳቸው እንጂ “ሚስቴን” አላሳየኋቸውም፡፡ በኋላ ላይም ከሴትየዋ ጋር የማደርገው ወሲብ አልጥምህ አለኝ፡፡ በዚህ ላይ በድህነት ዘመኔ አፈቅራት የነበረች ጓደኛ ነበረችኝ፡፡
ከሴትየዋ ጋር ከተዋወቅን ጀምሮ የራቅኋት ቢሆንም አልፎ አልፎ ማስታወሴና መናፈቄ አልቀረም፡፡ ጓደኛዬን ፈልጌ አገኘኋትና ጓደኝነታችንን ቀጠልን፡፡ አሁን ኑሮዩ የተደላደለ ሆነ፡፡ ገንዘብና ድሎትን ከማሚ፣ ፍቅርን ከጓደኛዬ ማግኘት ጀመርኩ፡፡ ይህ ሁኔታዬ ግን ብዙ አልቆየም፡፡ ማሚ ከጓደኛዬ ጋር ያለኝን ግንኙነት ደረሰችበት፡፡ ፀባችን እየከረረ ሄደ፡፡ በዚህ ጊዜ እኔ በቂ ገንዘብና ንብረት ይዤ ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ሹገር ማሚዬ እንደማታስፈልገኝ እርግጠኛ ነበርኩና ሆን ብዬ ፀቡ እንዲከር አድርጌ ተለየኋት፡፡ ራቫ ፎር መኪናዋንና በርካታ መጠን ያለው ገንዘቧን ግን በእጄ ለማድረግ ችያለሁ፡፡”
በትዳር ውስጥ ያሉና በዕድሜ የገፉ ባሎች ያሏቸው ሴቶችም በአብዛኛው ሹገር ማሚነቱን ይከውኑታል፡፡ እነዚህ ሴቶች የትላልቅ ቡና ቤቶች፣ ሆቴሎች፣ ሱፐር ማርኬቶችና ድርጅቶች ባለቤቶች ናቸው፡፡ በድርጅቶቻቸው ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ጥሩ ቁመና ያላቸው፣ ተግባቢ ወጣቶች ሹገር ማሚዎቹ አይን ከገቡ አበቃላቸው፡፡ በገንዘባቸው ሃይል አንበርክከው የወሲብ እስረኞቻቸው ማድረጉን ያውቁበታል፡፡ በራሳቸው ቤት፣ ወይም ቤት ገዝተው አሊያም ተከራይተው ፍላጐታቸውን ሁሉ እያሟሉ የሚያስቀምጧቸው ጐረምሶች፤ ሹገር ማሚዎቹን እንደ ኮረዳ እያሽኮረመሙ የወጣትነት ትኩስ ፍላጐትና ስሜት እንዲሰማቸው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
በአብዛኛው በሹገር ማሚዎች የተያዙ ወንዶች፤ ከ“ሚስቶቻቸው” ጋር አብረው በአደባባይ እንደ ልብ መታየትን አይፈልጉም፡፡ ይህ ደግሞ ሹገር ማሚዎቹ እንደ ፍላጐታቸው በየአደባባዩና በየመዝናኛ ቦታው ከ “ጐረምሳቸው” ጋር በፍቅር ለማበድ እንዳይችሉ ያደርጋቸዋል፡፡ አብይ ታሪኩ (ስሙ የተቀየረ) ስለ ሹገር ማሚው ሲናገር፤ በተለየዩ መዝናኛ ቦታዎች ላይ ከእኔ ጋር አብሮ መታየት እንዲሁም በየአደባባዩ በማቀፍና በመሣም ፍቅሬን እንድገልፅላት ትፈልጋለች፡፡ ይህ ደግሞ እኔ ፈፅሞ የማልወደውና የማልፈልገው ጉዳይ ነው” ሲል ገልፆታል፡፡ አብዛኛዎቹ ሹገር ማሚዎች፤ ለፍቅረኞቻቸው ፈፅሞ ነፃነትን አይሰጡም፡፡ ከእኔ ከተለየ ሌላ ሴት (ወጣት) “ይጠብሳል” ብለው ስለሚያስቡ የ “ጐረምሶቻቸውን” ውሎ መከታተል ይፈልጋሉ፡፡ አስር ጊዜ እየደወሉ “የት ነህ?” የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውም የተለመደ ነው፡፡ ከወንድ ጓደኞቻቸዉ ጋር እንኳን ቢሆን ለረዥም ጊዜ እየተዝናኑ እንዲቆዩ አይፈቀድላቸውም፡፡ ከሹገር ማሚዎቻቸው ጋር በጊዜ ሂደት ተስማምተው በፍቅር የወደቁ፣ ተጋብተው ህጋዊ ትዳር የመሰረቱም በርካታ ወጣት ወንዶች አሉ፡፡
“ስንጀምር በዚህ መልኩ ግንኙነታችን ይቀጥላል ወይም ዘላቂነት ይኖረዋል ብዬ አልነበረም፡፡ በሂደት ግን በቃ ተመቸችኝ ፤ስንጀምር የነበሩን በርካታ ልዩነቶች እየጠፉ ፍላጐታችን እየተቀራረበ ሄደ፡፡ ታምኚኛለሽ--- ድብን ያለ ፍቅር ያዘኝ፡፡ የእንጋባ ጥያቄውን ያቀረብኩላት እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ የማግኘት ተስፋ እንደሌለኝ ባውቅም ብዙ ስሜት አልሰጠኝም፡፡ የምትወደድ አይነት ሴት ነች፤ ተመችታኛለች፡፡ አሁን እንኳን ከተጋባን ሶስት ዓመት አልፎናል፡፡ የእውነት ነው የምወዳት” ዘውዱ (ስሙ የተቀየረ) ስለ ሹገር ማሚው የተናገረው ነው፡፡
ሹገር ማሚዎች በአብዛኛው የሚጠሉት ነገር ከሹገር ቤቢዎቻቸው ጋር በመዝናኛ ቦታዎች ሲሄዱ “ልጅሽ ነው?” የሚሉ የጓደኞቻቸውን ጥያቄ ነው፡፡ እንዲህ እየተባሉም ቢሆን ሹገር ቤቢዎቻቸው ተለይተዋቸው እንዲቀሩ አይፈልጉም፡፡ ዛሬ ዛሬ በርካታ ወጣቶች፤ ሹገር ማሚዎችን እያሳደዱ መተዋወቅና ማጥመዳቸው የተለመደ ተግባር እየሆነ ነው፡፡ ከሹገር ማሚዎቻቸው የሚያገኙትን ገንዘብ የዕድሜ እኩያዎቻቸውን (ፍቅረኞቻቸውን) ለማዝናናት ይጠቀሙበታል፡፡ በሹገር ማሚዎቹ ለመመረጥና መስፈርቶቻቸውን ለማሟላት ወጣቶቹ ትግል ይዘዋል፡፡ ሹገር ማሚዎቹ በአብዛኛው ሰውነታቸው ደልደል ያለ ተጫዋችና ተግባቢ ወጣት ወንዶችን ለፍቅረኝነት ይፈልጋሉ፡፡ ሹገር ማሚዎቹ እነሱ የሚፈልጉትን አይነት አገልግሎት እየሰጡ አብረዋቸው የሚዘልቁ ወጣቶች የት እንደሚገኙ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ለዚህ ተግባር ተመራጩ ቦታ ጅምናዚየሞች፣ ማሳጅ ቤቶች፣ ሲኒማ ቤቶችና ናይት ክለቦች ናቸው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ሹገር ማሚዎች በአገናኝ ደላሎች አማካኝነት የፈለጉትን ወጣት ከእጃቸው ለማስገባት አይቸገሩም፡፡ እድሜ ለቴክኖሎጂ! ዛሬ ደግሞ ሹገር ማሚዎች የፈለጉትን አይነት ወጣት የሚያገኙበትና የሚቀጣጠሩበት ድረገፅ ተከፍቶ ሥራውን በስፋት እየሰራ ይገኛል፡፡ Friendfinder:sugermummy tips.com, Adult friend finder seeking arrengment.com የተባሉት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ዛሬ ዛሬ ከታዋቂ አርቲስቶቻችን መካከል በሹገር ማሚ ወጥመድ ተይዘው ተፈላጊውን አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ወጣቶች እንዳሉም ይነገራል፡፡ ከዕድሜ ጋር ግብግብ የተያያዙት ሹገር ማሚዎች፤ የዕድሜያቸው ጀንበር አዘቅዝቃ ይህቺን አለም ከመሰናበታቸው በፊት ያሻቸውን ለማድረግ፤ የፈለጉትን ለመፈፀም ትግል ይዘዋል፡፡ ወጣት ወንዶቹም (ሹገር ቤቢዎቹ) የኢኮኖሚ ችግራቸውን የሚቀርፉላቸውን ሹገር ማሚዎች ለመንከባከብና ለማስደሰት እየተጉ ይገኛሉ፡፡
      Source: Addis Admass


| Copyright © 2013 Lomiy Blog