የአፍሪቃና የአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ ተጠናክሮ የቀጠለው ጥቃት እንዲቆም እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ብራሰል ቤልጂግ ውስጥ ለተካሄደው የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽኖች የሰብዓዊ መብቶች የጋራ መድረክ አሳስቧል ። 

የአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት በአፍሪቃ ለሰብዓዊ መብት መከበር ለሚታገሉና አውሮፓ ውስጥ ለሚገኙ የውጭ ዜጎች የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ በጋራ እንዲሰሩ ተጠየቁ ። የአውሮፓ ህብረትም ለውጭ ዜጎችና ለተገን ጠያቂዎች የተሻለ ጥበቃ እንዲያደርግ ጥሬ ቀርቦለታል ። ሂሩት መለሰየአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት ኮሚስዮኖች ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ካካሄዱት ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት ዋነኛ ትኩረቶች አንዱ አፍሪቃ ውስጥ በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች በጋዜጠኖችና በሲቪል ማህበራት ላይ የሚፈፀመው ጥቃት
እየከፋና እየተወሳሰበ መሄዱ ነው ። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ አውሮፓ የሚሰደዱ ሰዎች መንገድ ላይ እንዲሁም አውሮፓ ከደረሱ በኋላም የሚያጋጥማቸው ችግርም ሌላው የመነጋገሪያ ርዕስ ነበር ። ለነዚህ ሁለት አብይ ችግሮች የሁለቱ ክፍለ ዓለማት ኮሚስዮኖች የጋራ መፍትሄ እንዲፈልጉ ውይይቱ ከመካሄዱ በፊት ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሂዩመን ራይትስ ዋች ጥሪ አቅርቦ ነበር ። ከኮሚስዮኖቹ ስብሰባ አስቀድሞ በተመሳሳይ ርዕስ ላይ በተካሄደው በብራሰልሱ ስብሰባ ላይ የተገኙት በሂዩመን ራይትስ ዋች የአፍሪቃ ክፍል ሃላፊ አቶ ዳንኤል በቀለ በተለይ በብዙ የአፍሪቃ ሃገራት በጋዜጠኞችና በሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በሁለት መንገድ መከላከል ይቻላል ይላሉ ።


ሂዩመን ራይትስ ዋች እንደሚለው ባለፉት 20 ዓመታት በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ቁጥር ማደግና የመገናኛ ብዙሃንም መስፋፋት የሚበረታታ ነው ይሁንና በተለይ ፈላጭ ቆራጭ መንግሥታት ባሉባቸው የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ የሚሰነዘረው ጥቃት ተባብሷል ። ስደትን ከሚያባብሱ ምክንያቶች ውስጥ የሚደመሩትን እነዚህን ድርጊቶች የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ምዕራባውያን መንግሥታት ከማውገዝ ባለፈ በነዚህ ጨቋኝ መንግሥታት ላይ ተጨባጭ እርምጃ ባለመውሰድ ይተቻሉ ። ይህ ጉዳይ የብራሰልሱ የውይይት መድረክ አፅንኦት ሰጥቶት ካነሳቸው ነጥቦች አንዱ ነበር ። አቶ ዳንኤልሰብዓዊ መብትን በመጣስ የተወቀሱት አፍሪቃውያኑ ብቻ አይደሉም ። የአውሮፓ ህብረትም በተለይ ተገን ለሚያሻቸው የውጭ ዜጎች ድንበሩን በመዝጋት ተተችቷል ። ወደ አውሮፓ በባህር ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞች መንገድ ላይ ችግር ሲያጋጥማቸው አይቶ እዳላየ በማለፍ ብዙዎች ለሞት የሚዳረጉባቸው አጋጣሚዎች በምሳሌነትም ተነስተዋል ። ከመካከላቸው ከአንድ ወር በፊት የኢጣልያዋ ደሴት ላምፔዱዛ አቅራቢያ ከ 350 ሰዎች በላይ ህይወት የጠፋበት አደጋ አንዱ ነው ። አቶ ዳንኤል የአውሮፓ ህብረት በዚህ ረገድ የሚያራምደውን መርህ እንዲመረምር መጠየቁን ተናግረዋል ።
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ
Source: www.dw.de

No comments:

| Copyright © 2013 Lomiy Blog