በተለምዶ እሩቅ ምስራቅ ተብሎ በሚታወቀው የኢሲያ ክ/ዓለም ከጃፓን ባህር በስተምስራቅ በሰላማዊ ውቅኖስ፣ በደሴት መልክ የምትገኘው ጃፓን ስያሜዋም እራሱ በእነርሱ ቐቐ አተረጉዋጎም የጸኃይ መነሻ እንደማለት ነው። 
ትላልቆቹን ደሴቶች ማለትም ሆንሹ፣ ሆካይዶ፣ ኪይሹ እና ሺኮኩን ጨምሮ የ 6,852 ደሶቶች ስብስብ የሆነችው ጃፓን በህዝብ ብዛቷም በዓለማችን 10 ኛውን ደረጃ ይዛለች። 126 ሚሊየን ገደማ ህዝብ ኣላት።
ቀድሞ በትልቅነቱ በዓለማችን 2ኛ የሆነውን ግዙፍ ኢኮኖሚ በመገንባት የምትታወቀው ጃፓን በኣገር ውስጥ ጥቅል ምርትም ሆነ በገቢ እና ወጪ ሸቀጦች ደግሞ የ 4ኛነቱን ደረጃ እንደያዘች ትገኛለች። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት የ 2ኛነቱን ደረጃ ለቃ ወደ 3ኛነት ዝቅ ለማለት ተገዳለች። በኣንጻሩ የአንበሳ ድርሻ ከያዘችው US አሜሪካ ለጥቃ በፈጣን እድገት እጅግ ግዙፍ ኢኮኖሚ በመገንባት የ2ኛነቱን ደረጃ የተቆናጠጠችው የጃፓኗ ጎረቤት ታላቐ ቻይና ናት። በኢኮኖሚዋ ግዝፈት 2ኛ ትሁን እንጂ ወደ ውጪ በምትልካቸው ሸቀጦች ግን ግንባር ቀደም ናት ቻይና። በቆዳ
ስፋቷም ከሩሲያ ቀጥላ 2ኛ ስትሆን፣ በህዝብ ብዛቷ ግን ለማነጻጸር በሚቸግር ልዩነት ቀዳሚቱኑን ይዛ ትገኛለች። 1 ቢሊየን 350 ሚሊየን ህዝብ ኣላት። ከኣጠቃላዩ የኣፍሪካ ህዝብ በ 250 ሚሊዮን ይበልጣል።
የባህር ይዞታን ሳይጨምር 20,4 በመቶ የየብስ ስፋት በመያዝ የዓለማችን 2 ኛዋ ስፊ ኣህጉር ኣፍሪካ የህዝብ ብዛቷም 1,1 ቢሊየን ይገመታል። ከኣጠቃላይ ህዝቧ 54 በመቶ የሚሆነው በ19 ዓመት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ በመሆኑ ደግሞ The youngest contnent (ወጣቷ ክ/ዓለም) በመባልም ትታወቃለች። በተለያዩ በርካታ ምክኒያቶች በዓለማችን ለዘመናት ጥልቅ በሆነ ድህነት ብትታወቅም ታዲያ ያንኑ ያህል ደግሞ ይህ ነው የማይባል የተፈጥሮ ሀብትም እንዳላት ግልጽ ነው። ከዚሁ የተነሳ ኣህጉሪቱ በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የከበርቴዎቹን ኣገራት ትኩረት እየሳበች መምጣቷ ሲታወቅ ካሳለፍነው ሳምንት ማገባደጃ ኣንስቶ የጃፓን እና የቻይና ቱባ ቱባ ባለስልጣናት ያውም በተመሳሳይ ጊዜ ኣፍሪካን እየጎበኙ መሆናቸውም ይታወቃል።
የዛሬው የኢኮኖሚ ዝግጅታችንም በዚሁ ጉዳይ ላይ ያተኩራል፣ ከዝግጅቱ ጋር ጃፈር ዓሊ ነኝ መልካም ቆይታ።
የኣፍሪካ ጉብኝታቸውን ባለፈው ሰኞ በአዲስ ኣበባ ያጠናቀቁት የጃፓኑ ጠ/ሚ፣ ሺንዞ ኣቤ፣ ለተመሳሳይ ተልዕኮ ትላንት ወደ ኦማን ማምራታቸው ታውቐል።
በተመሳሳይ መልኩ የቻይናው የው/ጉ/ሚኒስትር ዋንግ ኪዪም ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የኣፍሪካ ኣገሮችን መጎብኘታቸው ሲታወቅ፣ የሁለቱ የኢኮኖሚ ባላንጣዎች ጎን ለጎን ኣፍሪካን መጎብኘታቸው በእርግጥ ለምን? ማሰኘቱ ኣልቀረም። ይህም፤ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚሉት በሁለቱ ኣገሮች መካከል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጋጋለ በመጣው የኢኮኖሚ ፉክክር ብቻም ሳይሆን፤ የሚያመለክተው፤ የኣህጉረ ኣፍሪካም ኣስፈላጊነቷ ያንኑ ያህል እየጎላ መምጣቱንም ጭምር ነው።
የቻይና ፈጣን ግስጋሴ ከጃፓንም ኣልፎ ምዕራባውያኑንም እያሳሰበ መምጣቱ በሚነገርበት በኣሁኑ ወቅት የኣንድ ኣገር እድገት ሌላውን የሚጎዳ ሆኖ ሳይሆን ነገር ግን ቻይና ጃፓንን ከዓለም ገበያ በተለይም ከኣፍሪካ እየገፋች መምጣቷ ነው ኣሳሳቢነቱ። የኣሁኑ የጠ/ሚ ኣቤ ተልዕኮም ከዚሁ የመነጨ ሲሆን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ክስተቱ ለኣፍሪካም የጎላ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።
ቀድሞ በአዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከዚያም ወዲህ እዚህ በጀርመን ኣገር በመምህርነት ያገለገሉት ዶ/ር አለማየሁ ብሩ ሁኔታውን ያብራሩታል።
የጃፓኑ ጠ/ሚ ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ለኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የሚውል የ 10 ቢሊየን የን ብድር የፈቀዱ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ ለሞዛንቢክ 50 ሚሊየን የን ገደማ እና ለኣይቮሪኮስትም እንዲሁ ዳጎስ ያለ ገንዘብ መፍቀዳቸው ታውቐል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ወደ ኣፍሪካ ያመሩት የቻይናው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ኪዪም ኢትዮጵያን፣ ጂቡቲን፣ ጋናን እና ሰኔጋልን ጎብኝቷል። የው/ጉ/ሚ ኪዪ በዚህ ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያው የው/ጉ/ሚ ቴዎድሮስ ኣድኃኖም፣ ከጂቡቲው ኣቻቸው መሀመድ አሊ፣ ከጋናው ሃናህ ቴቴህ እና ከሰኔጋሉ የው/ጉ/ሚ ማንኩዬር ኒዲያዬ በተጨማሪም ከየኣገሮቹ መሪዎች ጋርም መምከራቸው ታውቐል።
የቻይና የው/ጉ/ሚኒስትሮች እኣኣ ከ 1991 ወዲህ በየዓመቱ በዓመቱ መጀመሪያ ኣፍሪካን መጎብኘታቸው የተለመደሲሆን ከሳኃራ በታች ያሉ የኣፍሪካ ኣገሮችን ሲጎበኙ ግን የዋንግ ጉብኝት የመጀመሪያው መሆኑ ነው።
Source: dw.de

በአትላንታ የሚታተመው ድንቅ መጽሔት ተርጉሞ እንዳቀረበው
ዜና ድንቅ፦ ደቡብ አፍሪካዊው ሰባኪ ተከታዮቹ ሣር እንዲበሉ አዘዘ …. (ሜይ ኦንላይን ጥር 2/2006- ጃንዋሪ 10/2014)
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ የሚገኘው የራቢኒ ሴንተር ሚኒስትሪ ቤተክርስቲያን ፓስተር የሆኑት ሌሴጎ ዳንኤል፣ “ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ከፈለጋችሁ ውጡና የግቢውን ሳር ብሉ” ብለው በማዘዛቸው ተከታዮቻቸው ወጥተው ሳሩን ሲበሉ መዋላቸውን ሜል ኦንላይን ዘገበ። እንደዘገባው ከሆነ ፓስተሩ፣ ሥራ መብላት ወደ እግዚአብሔር ያቀርባል ከማለታቸው በተጨማሪ፣ ሰው ምንም ነገር ይሁን ወደ ሆድ የሚገባ እስከሆነ ድረስ መብላት ይችላልም ሲሉ ነግረዋቸዋል። ተከታዮቻቸውም ሳሩን ከበሉ በኋላ አብዛኞቹ
ታመው ሲያስመልሳቸው ታይቷል።
ይህ ድርጊታቸው ግን በርካታ ተቃውሞ እንደቀሰቀሰባቸውም ዜናው አክሎ ገልጿል። (ከታችን በፎቶው ላይ ተክታዮቻቸው ሳሩን ሲበሉ ፣ .. ታመው ሲሯሯጡ እና ፓስተሩ ይታያሉ)

South African Pastor Makes Congregation Eat Grass To Be Closer To God

Pastor Lesego Daniel (pictured) has been at the center of some heated controversy, after it was publicized — via his Rabboni Centre Ministries in Garankuwa, South Africa’s Facebook page — that he had instructed congregation members to eat grass so that they can “be closer to God,” according to Times Live.
SEE ALSO: Basketball Player Fakes Own Kidnapping To Escape School
The minister, who is oftentimes referred to as a “miracle man,” reportedly made his congregation of about 1,000 eat the grass as part of a ritual to show that humans can be controlled by God’s spirit.
When the church members ate the grass, a few claimed they were cured of their ills. One woman, 21-year-old law student Rosemary Phetha claimed she suffered from a sore throat for an entire year. Once the young woman ingested the grass, she swore it healed her malady, telling Times Live, that the preacher “turned me into a sheep and instructed me to eat grass. Yes, we eat grass and we’re proud of it because it demonstrates that, with God’s power, we can do anything.” the young congregant enthused.
Doreen Kgatle, 27, told Times Live that she suffered a stroke two years ago that left her paralyzed and unable to walk; yet, after she obeyed her pastor’s wishes, it resulted in a cure. “I could not walk, but soon after eating the grass, as the pastor had ordered, I started gaining strength, and an hour later, I could walk again,” Kgatle contends.
As the obedient ministry followers ate the grass, Daniels was allegedly witnessed walking on top of his congregants as they were spread out across a lawn.
But not everyone was cured from what ailed them. Instead, many reportedly received more than what they bargained for when they became violently ill after ingesting the grass: Throngs of followers wound up vomiting.
During another service, Daniels allegedly put a few congregants to sleep then ordered them to slap and trample on one another. On Facebook, Daniels reportedly boasted about his ability to put people to sleep and went as far as saying that he could even do so with arresting officers:
You can leave them like this for six months. I love this, I don’t want to be bored. You can even make police go to sleep when they come to arrest you,’ he said in a Facebook posting.
In addition to Daniels alleged curative powers apparently attracting believers from all walks of life, the good preacher also reportedly rakes in quite a bit of loot from the wares he is peddling from “miracle” bumper stickers to anointing oils that possess special powers to calendars. If folks do not have the cash to buy the allegedly blessed items, then the church will accept credit or debit cards.

But not everyone is convinced by Daniels spiritual claims. One Facebook poster remarked after seeing the pictures of the congregants eating grass, “Is this a scene in a movie…this can’t be real. God created animals to chew grass and made human beings to dominate over animals. Any person who reduces human beings to animals is definitely not of God.”
In the midst of all of the backlash, the only statement Daniel has made regarding the grass-eating event was on Thursday, when he posted on Facebook:
God is at work and His people are testifying right now at the farm. TO GOD BE THE GLORY.’
Sound off!
Source: Daily Mail Newspaper UK

የቀድሞዋ የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ ቅኝ ገዥ ፣ ፈረንሳይ፣ የእርስ በርስ መተላለቅ እንዳይከሠት ፣ የህዝብ መፈናቀልም እንዳይደርስ ለመግታት ፣«ሳንጋሪስ» የተሰኘ ልዩ ግብረ ኃይል ከላከች አንድ ወር ቢሆንም ፣ አንዳች ፋይዳ አለማስገኘቱን ራሷ

አመነች።ሰላም እስከባሪው ኃይል ቦንጊ ከገባ በኋላ ነው እንዲያውም፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳስታወቀው፣ አንድ ሚሊዮን ህዝብ ከቀየው የተፈናቀለው።
በኅዳር ወር ማለቂያ ገደማ ላይ ነበር፣ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ፍርንሷ ዖላንድ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ላይ በመድረስ ነበረ፤ ወደ ቀድሞዋ ቅኝ ግዛት 1,200
ተጨማሪ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች የላኩት። እነዚህም ነበሩ ቀደም ሲል በዚያ ሠፍረው የነበሩትን 400 ፈረንሳውያን ወታደሮችና 3,500 ውን የአፍሪቃ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ኃይሎች ለማገዝ የተሠማሩት። ፈረንሳይ ዖላንድ በገቡት ቃል መሠረትና የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ጥበቃው ም/ቤትም ስምምነት ላይ በመድረሱ ነበረ ፣ በማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ ሰብአዊ ቀውስ እንዳይከተል ለመግታት ጦር ያዘመተችበትን እርምጃ የወሰደች።
ይሁን እንጂ ፤ በዓለም ዙሪያ በደል ለሚደርስባቸው ነባር ህዝቦች መብት የሚቆረቆረው የጀርመን ድርጅት ተጠሪ Ulrich Delius የባሰ እንጂ የተሻለ ሁኔታ አለመከሰቱን ነው ያስታወቁት።
ሥልጣን በጨበጡት «ሴሌካ« አማጽያንና ከሥልጣን በተፈናቀሉት ፕሬዚዳንት ፍራንሷ ቦዚዜ ደጋፊዎች መካከል ፣ ትንንቁ እልባት ሳይገኝ ነው የቀጠለው። በአንድ ወር ውስጥ 1,000 ያህል ሰዎች ናቸው የተገደሉት፤ሰላም ማሥፈኑም ሆነ ፤ ሚሊሺያ ጦረኞችን ትጥቅ ማስፈታቱ ከቶ አልሠመረም።
ተልእኮው የከሸፈበት አንዱ ምክንያት ፤ የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የስልታዊ ግንኑነት ጉዳይ ተቋም ፤ የምርምር ክፍል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዣን -ክሎድ አላርድ እንደሚሉት በቂ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ባለመሠማራታቸው ነው። ከሞላ ጎደል አንድ ሚሊዮን ገደማ ኑዋሪዎች ላሏት ለመዲናይቱ ለቦንጊ ፤ ለመሆኑ በምን ስሌት ነው 1,600 ሰላም አስከባሪ ወታደሮች የተመደቡት በማለትም በአንክሮ ይጠይቃሉ። እንደ አላርድ ግምት በማዕከላዊት አፍሪቃ ሰላም እንዲሠፍን ለማድረግ ፣ 6,000 ወታደሮች እንኳ አይበቁም።
የፈረንሳይ ወታደሮች ፤ በቦንጊ እንደተሠማሩ በአማዛኙ ሙስሊሞቹን የ«ሴሌካ» አማጽያን ኃይሎችን ነበረ ትጥቅ ማስፈታት የጀመሩት። ይህን አጋጣሚ በመጠቀም፤ የክርስቲያኖቹ ሚሊሺያ ጦረኞች በቁጥር አነስተኛ በሆኑት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ጥቃት መሠንዘር ጀመሩ። በዚህም ሳቢያ በሥጋት የተዋጠው የከተማይቱ ኑዋሪ ገሚሱ መዲናይቱን ቦንጊን ለቆ ወጥቷል። በሴሌካ አማጽያን የሚደገፉት የሽግግሩ መንግሥት ፕሬዚዳንት ሚሸል ጆቶዲያ፤ ከሚገኙበት ጦር ሠፈር ውጭ ተጽእኖአቸው በሌላው ያስገኘው አንዳች ፋይዳ የለም።
የቀድሞው የቦንጊ ከንቲባ፤ ጆሴፍ ቤንዱንጋ ለዚህ ለተባባሰ ውዝግብ ኀላፊዋ ድሮ የማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ ቅኝ ገዢ የነበረችው ፈረንሳይ ናት በማለት ነቅፈዋል። የችግሩ አሳሳቢነት በፈረንሳይ መንግሥትም በኩልም ቀደም ሲል ይታወቅ እንጂ መላ አልተፈለገለትም።
የፈረንሳይ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሎራ ፋቢዩስ ፣ አገራቸው ፣ ጆቶዲያ ሥልጣን እንዲለቁ ግፊት እያደረገች እንደሁ ተጠይቀው ሲመልሱ፣ ፈረንሳይ፤ እንዲሁ ታዛቢ እንጂ ሌሎች ውሳኔዎችን እንዲቀበሉ የምታስገድድ አይደለችም፤ስለማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ መጻዔ ዕድል ውሳኔ የሚያሳልፉ የማዕከላዊት አፍሪቃ ሃገራት ናቸው ማለታቸው ተጠቅሷል።
በዛሬው ዕለት በቻድ የተሰበሰቡት የማዕከላዊው አፍሪቃ የኤኮኖሚ ማኅበረሰብ አባል ሀገራት ተጠሪዎች፤ የሽግግሩ ፕሬዚዳንት ጆቶዲያ ሥልጣናቸውን እንዲለቁ ግፊት ማድረጋቸው እንደማይቀር ተነግሯል። ራሳቸው ጆቶዲያ፤ ጠ/ሚንስትሩን ኒኮላ ቲያንጋዬንና የብሔራዊውን የሽግግር ም/ቤት ሊቀመንበር አሌክሳንደር ፈርዲናንድ እንጉየንዴን ይዘው በተጠቀሰው በቻድ በተከፈተው ጉባዔ በመሳተፍ ላይ ናቸው።
በመሃሉ፤ የአውሮፓው ኅብረት፤ በማዕከላዊት አፍሪቃ ሪፓብሊክ የተሠማሩትን የፈረንሳይ ወታደሮች የሚያግዝ ጦር ለመላክ ማቀዱን አስታውቋል። የ 28 ቱ አባል ሃገራት አምባሳደሮች ከ 700 እስከ 1,000 ያህል ወታደሮች ለመላክ ነገ ይወስናሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Source: www.dw.de 

የሰላም ንግግሩ ከሚያተኩርባቸው ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የተኩስ አቁም እንደሚሆን ይጠበቃል ። በንግግሩ የተኩስ አቁም ተግባራዊ መሆኑን መቆጣጠሪያ መንገድም ይቀይሳል የሚል ተስፋ አለ ። ከሁለት ሳምንት በፊት የተቀሰቀሰው የደቡብ ሱዳን ውጊያ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ። ውጊያው የመቆሙ ተስፋ በማይታይበት በዛሬው እለት ሁለቱ
ተፋላሚ ወገኖች በተስማሙት መሠረት በወቅቱ የአፍሪቃ ህብረትና የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን በምህፃሩ IGAD ሊቀመንበር በሆነችው በኢትዮጵያ ሸምጋይነት አዲስ
አበባ ውስጥ የሰላም ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው ። ፕሪቶሪያ ደቡብ አፍሪቃ የሚገኘው የዓለም ዓቀፍ የፀጥታ ጉዳዮች ጥናት ተቋም ሃላፊ ዶክተር ያኪ ሲልየር በሽምግልናው የኢትዮጵያ ሚና ምን ሊሆን እንደሚችል ገልፀዋል።
« ኢትዮጵያ የአፍሪቃ ህብረትና የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት በእንግሊዘኛው ምህፃር IGAD ሊቀ መንበር ናት ። በርግጥ አዲስ አበባ የአፍሪቃ ህብረትም መቀመጫ ነው ። አሁን የአፍሪቃ ህብረት ፣ IGAD ድርድሩን እንዲመራ የጠየቀ ይመስላል ። የኢትዮጵያ ሚና ሁለቱ ወገኖች ሊነጋገሩ የሚችሉበትን ገለልተኛ ስፍራ መስጠት ነው ። »
ከሁለት ሳምንት በላይ ባስቆጠረው በደቡብ ሱዳኑ ውጊያ ከ 1 ሺህ በላይ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ብዙዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ። የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሃብት ንብረታቸውን ተዘርፈው የተሰደዱም በርካታ ናቸው ። የሃገሪቱ የንግድ እንቅስቃሴም ተስተጓጉሏል ። ይህን ሁሉ ወደ ነበረበት መመለሱ ቀላል ይሆናል ተብሎ አይታሰብም ። የሰላም ንግግሩ የዚህ አንድ ተስፋ ሊሆን እንደሚችል ግን ይገመታል ። በዚህ የሰላም ሰላም ድርድርም ዶክተር ያኪ ሲልየ ቅድሚያ ትኩረት የሚሰጠው ዋነኛው ጉዳይ የተኩስ አቁም ሊሆን ይችላል ይላሉ ።
« መጀመሪያ የሚነጋገሩበት ጉዳይ የተኩስ አቁም እንዲፀና ማድረግ ና ተኩስ አቁሙ ተግባራዊ መሆኑን የሚቆጣጠሩበት መንገድ ላይ የሚሆን ይመስለኛል ። አሁን በምንነጋገርበት ሰዓት ውጊያው አልቆመም ። ቅድሚያ የሚሰጠው ውጊያውን ማስቆምና ከዚያ በኋላ የተኩስ አቁሙን መከበር መከታተል የሚቻልበትን መንገድና ስርዓት መዘርጋት ነው የሚሆነው ።»
ምንም እንኳን የተኩስ አቁም ዋነኛው ትኩረት ሊሰጠው የሚችል ጉዳይ ቢሆንም ተግባራዊነቱ ግን ማጠያየቁ አይቀርም ። ሲልየ እንደሚሉት ግን ደቡብ ሱዳን የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ኃይል በመጠናከሩ ለዚህ እገዛ ያደርጋል የሚል ትልቅ ተስፋ አለ ።
«ቁጥራቸው በእጥፍ ጨምሮ ወደ 12500 እንዲያድግ የተወሰነላቸው የተባበሩት መንግስታት ማለትም የUNMISS ኃይሎች ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ። እንደሚገባን ውጊያው አሁን በ2ት ግዛቶች ማለትም በዩኒቲና በጆንግሌ ክፍለ ግዛቶች ነው የሚካሄደው ። የጆንግሌ ክፍለ ግዛት ዋና ከተማ ቦር እንደገና በአማፅያኑ እጅ ገብታለች ። ስለዚህ ዋነኛው እንቅስቃሴ የሚደረገው በዚሁ አካባቢ መሆኑን መገመት ይቻላል ። እንደ እድል ሆኖ ዓለም ዓቀፉ ማህብረሰብ በደቡብ ሱዳን የተኩስ አቁም ተግባራዊ መሆኑን በመከታተል ሊያግዝ የሚችል የተባበሩት መንግሥታት ኃይል UNMISS አለው ።»
የሰላም ንግግር ይጀመራል በተባለበት በዛሬው እለት ከትናንት በስተያ ቦር የተባለችውን የጆንግሌ ክፍለ ግዛት ዋና ከተማ መልሰው የያዙት አማፅያን ወደ ደቡብ በመግፋት ላይ ሲሆኑ የመንግሥት ወታደሮች ደግሞ ወደ ቦር እየገሰገሱ ነው ። ዶክተር ስሊየ እንደሚሉት የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች አዲስ አበባ መግባታቸው ቢነገርም የልዑካን ቡድኑ ይዘት ግልፅ አይደለም ። ቀጥተኛ ድርድር ከመጀመሩ በፊትም አንድ ሁለት ቀን ሊወስድ ይችላል የሚል ግምት አላቸው
Source: www.dw.de
ግብፅ የቅኝ ግዛት የውኃ ኮታዋ እንዲከበር አሁንም ጠይቃለች
•ለመስማማት የገባችውን ቃል አፍርሳለች
የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የህዳሴውን ግድብ ግንባታ በተመለከተ ከግብፅና ከሱዳን መንግሥታት ጋር እያደረገ የሚገኘውን ድርድር ውጤት አስታወቀ፡፡ የግብፅ መንግሥት ያቀረባቸው የግዴታ ሐሳቦች በኢትዮጵያ በኩል ተቀባይነት አላገኙም፡፡ 

የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከግብፅና ከሱዳን አቻ ሚኒስቴሮች ጋር በህዳሴው ግድብ ላይ እያደረጋቸው የሚገኙ ድርድሮችን ማክሰኞ ዕለት ለባለድርሻ አካላትና ለመገናኛ ብዙኃን ሲያሳውቅ፣ ኢትዮጵያ ከግብፅ ጋር የተስማማችባቸውንና ያልተስማማችባቸውን ነጥቦች ይፋ አድርጓል፡፡ 
በሚኒስቴሩ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅ አህመድ ባቀረቡት ጽሑፍ፣ ሚኒስቴሩና ብሔራዊ የባለሙያዎች ቡድን ሥልታዊና የተጠና እንቅስቃሴ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጐን እንድትቆም ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡
ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ባለፈው ዓመት መጨረሻ
ላይ ያቀረበው የመፍትሔ ሐሳብ ሪፖርትን ኢትዮጵያና ሱዳን መቀበላቸውን የገለጹት አቶ ፈቅ፣ ይህ ሪፖርት በግብፅ በኩል ተቀባይነትን ያላገኘ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ነገር ግን የኢትዮጵያና የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባለፈው ዓመት መጨረሻ በአዲስ አበባ ተገናኝተው በተስማሙት መሠረት፣ የሦስቱ አገሮች የውኃ ሚኒስትሮች በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ተግባራዊነት ላይ ውይይት መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡ 
በጥቅምት ወር መጨረሻ ሱዳን የተገናኙት የሦስቱ አገሮች ሚኒስትሮች በመፍትሔ ሐሳቡ ተግባራዊነት ላይ በመወያየት የሚያመቻችና የሚከታተል ኮሚቴ ለመመሥረት በሐሳብ ደረጃ መስማማታቸውን፣ ነገር ግን በኮሚቴው አባላት ስብጥር ላይ መግባባት ባለመቻላቸው ውይይቱ ተቋርጦ ለሌላ ጊዜ መተላለፉን አስታውሰዋል፡፡ 
የኮሚቴው አባላት ሙሉ በሙሉ የሦስቱ አገሮች ባለሙያዎች ብቻ መሆን አለባቸው በሚለው የኢትዮጵያ ፍላጎት መኖሩና በግብፅ በኩል የውጭ ባለሙያዎች እንዲካተቱ አቋም መያዙ፣ የልዩነቱ ምክንያቶች እንደነበሩ አቶ ፈቅ ገልጸዋል፡፡ 
ይህንን ልዩነት ለመፍታት ከተያዘው ቀጠሮ ቀደም ብሎ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያና የሱዳን የጋራ ኮሚሽን ዓመታዊ ጉባዔን ምክንያት በማድረግ ወደ ሱዳን ማቅናቱንና በወቅቱም በሦስቱ አገሮች ድርድር ላይ የሱዳን መንግሥት የኢትዮጵያን አቋም እንዲረዳ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ 
የሱዳን የውኃና የኤሌክትሪሲቲ ሚኒስትር መንግሥታቸው የኢትዮጵያን አቋም ሙሉ በሙሉ ከመቀበል ባለፈ፣ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል የማግባባት ሚና እንደሚኖራት በመተማመን ሁለተኛው የሦስቱ አገሮች ድርድር ከመጀመሩ ቀናት በፊት ወደ ግብፅ ማቅናታቸውን ገልጸዋል፡፡ 
የሱዳን ሚኒስትር በካይሮ ቆይታቸው ከግብፅ ባለሥልጣናት ጋር በመገናኘት የኢትዮጵያን አቋም ማስረዳታቸውንና የግብፅ መንግሥት የኢትዮጵያን ሐሳብ እንደሚደግፍ ተገልጾላቸው መመለሳቸውን አስረድተዋል፡፡
‹‹ግብፅ የህዳሴው ግድብ ከፍታ ዝቅ ይበል የሚል ሐሳቧን፣ እንዲሁም ኢትዮጵያ የገንዘብ ብድር እንዳታገኝ የማደርገውን ሩጫ አቆማለሁ በማለት ለሱዳኑ ሚኒስትር ቃል ገብታ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ሁለተኛው ዙር ድርድር እንዲቀጥል ተደርጓል፤›› ያሉት አቶ ፈቅ፣ በዚህ ድርድር ላይ ግብፅ ይዛ የቀረበችው ሰነድ ከገባችው ቃል የተለየ ነበር ብለዋል፡፡ 
በግብፅ በኩል ለሁለተኛው ዙር ድርድር የቀረበው ሰነድ በሦስቱ አገሮች የሚቋቋመው ኮሚቴ በኢትዮጵያ በኩል የሚገኙ አዳዲስ የጥናት ውጤቶችን እንዲዳስስና የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ኮሚቴው እንዲከታተል ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ማለትም የግብፅና የሱዳን የውኃ ደኅንነትና ፍላጐት ሙሉ በሙሉ መከበር አለበት የሚሉ ነጥቦችን በድጋሚ በሰነዱ አካታ ማቅረቧን ገልጸዋል፡፡ 
‹‹ይህንን በጭራሽ ኢትዮጵያ የምትቀበለው አይደለም፤›› ያሉት አቶ ፈቅ፣ በዚህና በሌሎች የመወያያ ነጥቦች ላይ ትኩረት በማድረግ ውይይቱ እንዲቀጥል ለማድረግ እንደተሞከረ ገልጸዋል፡፡ 
በውይይቱ ላይ ግብፅ ከ20 በላይ ባለሙያዎችን እንዳሳተፈች በኢትዮጵያ በኩል ግን ስድስት ባለሙያዎች እንደተወከሉ የሚናገሩት ዳይሬክተሩ፣ በግብፅ በኩል ሆን ተብሎ ውይይቶችን እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በማጓተት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎችን የማዳከም ጥረታቸው ውጤት አልባ እንዲሆን በጥንካሬ መሠራቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ጥረት በሚመሠረተው ኮሚቴ አባላት ስብጥር ዙሪያ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ሐሳብ ተቀባይነት ማግኘቱን አቶ ፈቅ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኮሚቴው በሚቋቋምበት ዓላማና በተወሰኑ የኮሚቴው ተግባርና ኃላፊነቶች ላይ ኢትዮጵያ ያቀረበቻቸው ሐሳቦች ተቀባይነት ማግኘታቸው ታውቋል፡፡
ኮሚቴው ከዚህ ቀደም በዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን የቀረበውን የመፍትሔ ሐሳብ ተግባራዊነት የመከታተል ዓላማ የሚኖረው በመሆኑ፣ እስካሁን በሦስቱ አገሮች ተቀባይነት ካገኙ የኮሚቴው ተግባርና ኃላፊነቶች መካከል ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ያቀረባቸው ሁለት የመፍትሔ ሐሳቦችን ማስጠናትና የጥናት ውጤቱን ማፀደቅ ይገኝበታል፡፡ ዓለም አቀፍ የባለሙያዎቹ ቡድን ባቀረባቸው ሁለት ሐሳቦች በግድቡ ላይ ተጨማሪ የኃይድሮሎጂ፣ የአካባቢያዊና ማኅበራዊ ጥናቶች እንዲደረጉ ጠይቋል፡፡ 
በመሆኑም ኮሚቴው ለሁለቱ ጥናቶች አማካሪ ድርጅቶችን መቅጠርና ማስጠናት፣ የጥናቱን ሪፖርት መገምገም፣ ማስተካከልና ማቅረብ፣ በዚህ የጥናት ሪፖርት ላይ የኮሚቴው አባላት መግባባት ካልቻሉ ጉዳዩ ለሚኒስትሮች ቀርቦ እልባት እንዲያገኝ፣ በዚህ ካልተፈታ ዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ሙያዊ አስተያየት እንዲያቀርቡ የሚረዳ የቅጥርና የሥራ ዝርዝር ኮሚቴው እንዲያዘጋጅ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በቀሩ ጉዳዮች ላይ ለመወያየትም ሦስቱ ሚኒስትሮች በቀጣዩ ሳምንት መጨረሻ በሱዳን ተገናኝተው ስምምነት ባልተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በአማካሪ የሚጠኑት ሁለት ጥናቶች ሪፖርት ግምገማ ላይ የኮሚቴ አባላቱም ሆኑ ሚኒስትሮቹ መስማማት ካልቻሉ፣ ሙያዊ አስተያየት የሚሰጥ አማካሪ ለመቅጠር ስምምነት ተደርሷል፡፡ ነገር ግን ሙያዊ አስተያየት የሚሰጠው አማካሪ ቡድን ቅጥር የሚፈጸመው በሦስቱ አገሮች ባለሙያዎች ስምምነት ነው የሚለው ላይ ከስምምነት አልተደረሰም፡፡ ሙያዊ አስተያየት እንዲሰጥ የሚቋቋመው ቡድን በጥናቶቹ የመጨረሻ ሪፖርት ላይ ብቻ አስተያየቱ ይወሰናል በሚለው የኢትዮጵያ አቋም ላይ ያለውን አለመግባባት መቅረፍ ሌላው የውይይቱ አካል ነው፡፡ 
እስካሁን የተደረጉ ድርድሮችን ውጤቶቹን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ውይይት ላይ የተገኙት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ትልቅ አገራዊ ጉዳይ ላይ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ በእጅጉ አድንቀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬ በበኩላቸው፣ የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት የትኞቹንም የተፋሰስ አገሮች እንደማይጐዳ ለማሳወቅ ዩኒቨርሲቲው በአገር ውስጥ እያደረገ የሚገኘውን እንቅስቃሴ በማስፋት ወደ ጐረቤት አገሮች እንደሚዘልቅ አስረድተዋል፡፡ በዚህም መሠረት በመጪው መጋቢት ወር በሱዳን ሲምፖዚየም ለማዘጋጀት ከካርቱም ዩኒቨርሲቲ ጋር ስምምነት መፈረሙን ገልጸዋል፡፡
Source: Reporter

    ከ 4 ዓመት ገደማ በፊት፤ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዙ አንድ የኔልሰን ማንዴላ ድርጅት ዋና ተመራማሪ፤ ማንዴላን በማሠልጠን ያገዙ በሕይወት የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ ጠይቀው ያሰባሰቡት መረጃ ፣ ማንዴላ ከእሥራኤላውያን ጋር ግንኑነት እንደነበራቸው የሚያረጋግጥ አንዳችም እውነታ አልተገኘበትም። 
     ማንዴላን የጨበጣ ውጊያ ፣ የጦር መሣሪያ፣ አፈታትና አገጣጠም ፤ የቦንብ አጠቃቀምና የመሳሰለውን ያሰለጠኗቸው ኢትዮጵያ ውስጥ የነበሩ የእሥራኤል የስለላ ድርጅት(ሞሳድ) ሠራተኞች ናቸው ሲል «ሐዓሬትዝ» የተሰኘ በእስራኤል የሚታተም ጋዜጣ አስነብቧል። ይሁን እንጂ የኔልሰን ማንዴላ ድርጅት፤ በሰጠው መግለጫ፤ ከማንዴላ የግል ማኅደርም ሆነ ከሌላ ይህን ዜና የሚያረጋጋጥ አንዳች ፍንጭ እንደሌለ
አስታውቋል። ከ 4 ዓመት ገደማ በፊት፤ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዙ አንድ የኔልሰን ማንዴላ ድርጅት ዋና ተመራማሪ፤ ማንዴላን በማሠልጠን ያገዙ በሕይወት የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ ጠይቀው ያሰባሰቡት መረጃ ፣ ማንዴላ ከእሥራኤላውያን ጋር ግንኑነት እንደነበራቸው የሚያረጋግጥ አንዳችም እውነታ አልተገኘበትም። ታዲያ «ሐዓሬትዝ» የተሰኘው የእስራኤል ታዋቂ ጋዜጣ ይህንን መረጃ እንዴት ሊያወጣ ቻለ?
Source: www.dw.de
 
ከፖለቲካ ዲፕሎማሲዉ ይልቅ፥ ጠመንጃ ጦርነትን ያደጉ የኖሩበት ሳልቫ ኪር የዲንካን፥ እንደ ፖለቲከኛ-ሻጥርን፥ እንደ ዲፕሎማት ግድምድሞሽ ዘይቤን፥ እንደ ታጋይ የጫካ ዉጊያ አጣምረዉ የያዙት ዶክተር ሪክ ማቼር የኑዌር ጎሳን፥ ከየጎናቸዉ አሰልፈዉ ተፋጠዋል። 
 ዛሬ-ስምት ዓመት በዚሕ ወቅት ግድም የረጅም ጊዜዉ ጦርነት፥ የሚሊዮኖች እልቂት ፍጅት ስደት አበቃለት ተባለ።የዛሬ-ሰወስት ዓመት በዚሕ ወቅት ግድም ሕዝቧ በነፃ ዉሳኔዉ ነፃነትዋን ማስፀደቁ ተነገረ። የዓለም ፖለቲከኞች መሠከሩለትም።ደቡብ ሱዳን።ሐምሌ-ሁለት ሺሕ አስራ-አንድ (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) ነፃነቷ ታወጀ።ፌስታ።

ወዲያዉ ግን ግጭት። ደግሞ ጦርነት።ዛሬም ጦርነት ላይ ናት።አዲስ ሐገር፥ ግራ አጋቢ ምድር።እንዴት ለምን? ላፍታ አብረን እንጠይቅ።
አምና ነዉ።መስከረም።አዲሲቱን አፍሪቃዊት ሐገር ካሮጌ እልቂት ፎጅቷ ለመድፈቅ፧ አዳዲስ ጄኔራሎቿ የጀመሩት አመፅ፣ የአሮጌ ፖለቲከኞችዋን ነባር ሸኩቻ፤ የነባር ጎሶችዋን አሮጌ ግጭት ባዲስ መልክ አንሮታል።እንደ የበላይ የበታቾቻዉ ሁሉ በዉጊያ፣ አመፅ፣ ሽኩቻ፣ የኖሩት የያኔዉ የሐገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቼር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ኒዮርክ የገቡት አዲሱ አመፅ፣ ሽኩቻ ግጭት ከኖሩበትና ከዘወሩት ብዙ ብጤዉ እንደማይከፋ እያሰላሰሉ ነበር።
ማቼር ከጉባኤዉ አዳራሽ ሲደርሱ ካገጠሟቸዉ ጋዜጠኞች ቢያንስ አንዱ የአዲሲቱ ሐገራቸዉን አዲስ ቀዉስ ምናልባትም የራሳቸዉንም ቅሬታ በቅጡ የሚያዉቅ ሳይሆን አይቅርም። «መንግሥትዎን መፈንቅለ መንግሥት ያሰጋዋል ይባላል» ብሎ ጠየቃቸዉ።ጥያቄዉ ያሰቡትን-ወይም ያለሰቡትን የሚያሳስብ ሊሆን፥ ላይሆንም ይችላል።መልሳቸዉ ግን «በፍፁም» የሚል ነበር።
እንዲሕ አይነት እርምጃ «ጅልነት» አሉ-አሉ አንጋፋዉ የነፃነት ታጋይ፥ «አዲሱን መንግሥት በአመፅ መጀመር አንፈልግም።» አከሉ፥-የአዲሲቱ ሐገር የያኔ ትልቅ ሹም።አሁንም አምና ነዉ።ግን ሐምሌ። ኪር እና ማቸር በየልባቸዉ የሚያስቡ፥ የሚያሰላስሉትን ከነሱ በስተቀር በግልፅ የሚያዉቅ-ከነበረ ቢያንስ አስካሁን በግልፅ አይታወቅም።

ሁለቱም ሁለት ዓመት እንደኖሩበት የመጀመሪያዉ እንደ ፕሬዝዳት፥ ሁለተኛዉ እንደ ምክትል ፕሬዝዳት በዓሉን አከበሩ።የነፃነት በዓል-ሁለተኛ ዓመት። ወዲያዉ ግን የመጀመሪያዉ ከሥልጣን አባራሪ፥ ሁለተኛዉ ተባባራሪ ሆኑ።

«አሁን የአንድ ሰዉ አገዛዝ ነዉ ያለን።ያንድ አገዛዝ ምን ማለት ነዉ።አምገነንነት።»
የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት ሪክ ማቸር።ከሥልጣን በተባረሩ ማግሥት።ሐምሌ።ደቡብ ሱዳን፥ የሚነገር አይሆንባትም፥ የታቀደ አይፈፀምባትም፥የተነገረ-አይታመንባትም።ወይም የሚነገር፥ የሚባል፥ የሚታቀደዉ ከነባር እዉነቷ፥ከአቅም ማንነቷ ጋር ይጣረሱባታል።ማቼርም አምና መስከረም እንደ ምክትል ፕሬዝዳት ኒዮርክ ላይ የተቃወሙትን፥ባለፈዉ ሳምንት ለዕሁድ አጥቢያ ጁባ ላይ አደረጉት።መፈንቅለ መንግሥት።ከሸፈ።መዘዙ ግን ዛሬም አላባራም።
ፕሬዝዳት ሳልቫ ኪር የመላዉ ሱዳንን የምክትል ፕሬዝዳትነት ሥልጣን ከጆን ጋራግ ከወረሱበት ጊዜ ጀምሮ አደባባይ ሲወጡ አሜሪካኖች «የእረኛ» የሚሉት ሠፊ-ክብ ባርኔጣ ካናታቸዉ ተለይቶ አያዉቅም።ይወዱታል።ባርኔጣዉ በሚዘወተርበት ቴክስሳ ግዛት ያደጉ-የሚኖሩት የቀድሞዉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳት ጆርጅ ደብሊዉ ቡሽ ለሳልቫ ኪር የሸለሟቸዉም ይሕኑ ባርኔጣ ነበር።
ዕሁድ ግን ባርኔጣቸዉን አዉልቀዉ፥ ሱፍ ከረባትታቸዉን በጄኔራል ማዕረግ በተንቆጠቆጠ የዉጊያ ልብስ ቀይረዉ ከጦር ሜዳ እንደተመለሰ ጄኔራል እያጉረጠረጡ ከቴሌቪዥን ካሜራ ፊት ብቅ አሉ።
እርግጥ ነዉ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራዉ ከሽፏል።የአዲሲቱ ሐገር እዉነታ ግን ፕሬዝዳንቷ ካሉት ተቃራኒዉ ነዉ።ራሷ ጁባ፥ ቦር፥ ጃንጌሌይ፥ ዩኒቱ ከተሞች እና ግዛቶች ዛሬም በሳምንቱ በዉጊያ ይርዳሉ።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ፓን ጊሙን ይሕን መሠከሩ።
«እያሽቆለቆለ የመጣዉ የደቡብ ሱዳን የፀጥታ ሁኔታ በጣም አሳስቦኛል።ሁሉም የፖለቲካ፥ የጦር እና የሚሊሺያ ሐይላት መሪዎች ሰላማዊ ሰዎችን የሚጎዳዉን ጠብ፥ ግጭታቸዉን እንዲያቆሙ እጠይቃለሁ።»የሰማቸዉ እንጂ ቢያንስ እስካሁን የተቀበላቸዉ የለም።ጥንት በዚያ ግዛት እንዲያ ነበር።ድሮም።የዛሬ ስምንት ዓመትም እንዲሁ።ጥር ዘጠኝ።ሁለት ሺሕ አምስት።ናይሮቢ።
«ወገኖቼ፥ የሐገሬ ወንዶችና ሴቶች ሆይ! እንኳን ደስ አላችሁ።ደስታም በናንተ ላይ ይሁን። ንቅናቄያችሁ SPLM/SPLA እና የብሔራዊ ምክር ቤት መንግሥት አጠቃላይ የሠላም ስምምነት ተፈራርመዉላችኋል።ዛሬ የፈረምነዉና እናንተ ያችሁትን ፍትሐዊ እና የተከበረ የሠላም ዉል አቅርበንላችኋል።በዚሕ የሠላም ዉል መሠረት ከአፍሪቃ ረጅሙን ጦርነት አቁመናል።»
የቀድሞዉ የደቡብ ሱዳን ነፃ አዉጪ ጦርና ንቅናቄ መሪ ዶክተር ጆን ጋራንግ።ጋራንግ እንዳሉት ትልቂቱ አፍሪቃዊት ሐገር በ1956 ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ ከጥቂት ዓመታት ፋታ በስተቀር ጦርነት ተለይቷት አያዉቅም።ስምንቱ ሚሊዮኖችን የፈጀዉ፥ ከአራት ሚሊዮን በላይ ያሰደደዉን፥ ሰላሳ-ዘጠኝ ዓመታት ያስቆጠረዉን ጦርነት ማስቆሙ እርግጥ ነዉ።ከወጣትነት ዘመናቸዉ ጀምሮ ለአርባ ዓመታት ያኽል ያን ጦርነት ባንድ ወይም በሌላ መልኩ ሲዘዉሩ የነበሩት ጆንጋራንግ ያን ስምምነት ሲያበስሩ ዘግናኙ ጦርነት መቆሙን ብቻ ሳይሆን ሌላ ብጤዉ እንደማይከሰትም እርግጠኛ ነበሩ።ወይም ላዳመጣቸዉ መስለዉ ነበር።
«በዚሕ ሥምምነት መሠረት ከእንግዲሕ በየዋሕ ሕፃናትና እናቶች ላይ ከሠማይ የሚወርድ ቦምብ አይኖርም።ከእንግዲሕ ሕፃናት በደስታ የሚቦርቁበት፥ ባንድ ወይም በሌላ መልኩ ደስታቸዉን የተቀሙ እናቶች በእልልታ የሚደሰቱበት ሠላም ይሠፍናል።»«የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በርግጥ ከአቅሙ በላይ ተወጥሯል።እዚሕ ያለ ማንም ቢሆን የተለመደዉን ሠብአዊ ርዳታ ለማቀበል ነበር የተዘጋጀዉ።ጁባ ዉስጥም ሆነ በክፍለ ግዛቶች አሁን የተፈጠረዉ ቀዉስ ይፈጠራል ብሎ ማንም ሰዉ አልጠበቀም።»ከኑዌር የሚወለዱት ሪክ ማቼር እንደመሩት በሚታመነዉ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራና ሙከራዉን ባከሸፈዉ በፕሬዝዳት ሲልቫ ኪር ታማኞች መካካል ጁባ ዉስጥ ብቻ በተደረገዉ ዉጊያ ስድስት መቶ ሰዎች ተገድለዋል።በሌሎች ከተሞችና ክፍለ ግዛቶች በተደረገና በሚደረገዉ ዉጊያ የሞተ-የተሰደደ፥ የተፈናቀለዉን በትክክል የቆጠረዉ የለም።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳስታወቀዉ ጁባ እና ቦር በሚገኙ ሰወስት ቅጥር ግቢዎቹ ብቻ ከሠላሳ-አምስት ሺሕ በላይ ሕዝብ ተጠልሏል።ምዕራባዉያን ሐገራት ዜጎቻቸዉን ከምስቅልቅሊቱ ሐገር ማሸሹን ነዉ-ያስቀደሙት።ከዋና ፀሐፊ ፓን ጊ ሙን እስከ ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ያሉ መሪዎች ተፋላሚ ሐይላት ከተጨማሪ ጦርነት ታቅበዉ ልዩነታቸዉን በሰላም እንዲፈቱ መጠየቅ-፥ ማሰሰባቸዉ አልቀረም።«የደቡብ ሱዳን መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር ዝግጁ ነዉ።የምሥራቅ አፍሪቃ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ለድርድር የሚያስፈልጋቸዉን መረጃ ብቻ ሳይሆን ለጀመሩት ጥረት የደቡብ ሱዳን መንግሥትን ሙሉ ዉክልናም አግኝተዋል።»
ከኑዌር የሚወለዱት እዉቅ ጄኔራል ፔተር ጋዴት፥በቅርቡ ከዩኒቲ ግዛት አስተዳዳሪነት የተሻሩት ታባን ዴንግ ጋይ፥ ከባሪ የሚወለዱት የቀድሞዉ ሚንስትርና ጄኔራል አልፍሬድ ላዱ ጎር፥የአናሳዉ የመርል ጎሳ አባል የሆኑት ዴቪድ ያዩ፥ እና በርስበርሱ ጦርነት ወቅት «ነጩ ጦር» በመባል የሚታወቀዉ ሚሊሺያ ሐይል ሁሉም እንደ ጋራ ጠላት በሚያዩት በሳልቫ ኪር መንግሥት ላይ ጠመንጃቸዉን አነጣጥረዋል።ይተኩሳሉም።
«ከቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት ከዶክተር ሪክ ማቼር እና ከቡድናቸዉ ጋር የሚተባበሩ ወታደሮች ጁባ ዩኒቨርስቲ አጠገብ በሚገኘዉ በSPLA ዋና ፅሕፈት ቤት ላይ ጥቃት ፈፅመዋል።ጥቃቱ እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ ቀጥሎ ነበር።ይሁንና ለዜጎቼ በሙሉ፥ መንግሥታችሁ ጁባ ያለዉን የፀጥታ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን ማሳወቅ እፈልጋለሁ።»

ተናገሩ።አልበሽር (የሰሜን ሱዳን ፕሬዝዳንት) ቦምብ የሚባለዉን ቃል ሲሰሙ ፈገግ አሉ። ጆንግ ጋራንግ የሠላም ስምምነቱን ዉጤት ለማየት፥ የሐራቸዉን ነፃነት ለመመልከት አልታደሉም።ከአርባ ዘመን ጦርነት አምልጠዉ በቅፅበት የሔሊኮብተር አደጋ-ሞቱ።ጋራንግ እንዳሉት እኒያ የሰሜን ሱዳን አዉሮፕላኖች የሚያወርዱት ቦምብ ከሁለት ሺሕ አምስት በኋላ ቆሟል።ደቡብ ሱዳን ግን ሠላም ሆና አለማወቋ እንጂ ቁጭቱ።
የጁባ ነዋሪዎች
በነፃነትዋ ዋዜማ ኮርዶፋን ግዛት ለተደረገዉ ጦርነት ሰሜን ሱዳኖችን መዉቀስ፥ መወነጅሉ፥ ለዛሬዎቹ የጁባ ገዚዎችም፥ ለምዕራባዉያን ደጋፊዎቻቸዉም ቀላል ነበር።አምና መጋቢት ሒጂሊጅ እና አካባቢዉን ያጋየዉን ዉጊያ የቆሰቆሱት ሳል ቫኪር መሆናቸዉ አለጠያየቅም፥ ጦርነቱ የቆመዉ ግን ሐያሉ ዓለም አልበሽርን አዉግዞ አስጠንቅቆ፥ ኪርን ካባበለ በኋላ ነበር።


ደቡብ ሱዳን እስከ ዛሬም ከአስሩ ግዛቶችዋ ዘጠኙ በእርስ በርስ ጦርነት፥በጎሳ ግጭትና ቁርቁስ እንደተመሠቃቀሉ ነዉ።እና ሰሜን ሱዳኖች የሚያወርዱት ቦምብ በርግጥ የለም።የደቡብ ሱዳን ሕዝብ ግን ዛሬም እንደተገደለ፥ እንደ ቆሰለ፥ እንደተሰደደ፥ እንደተራበ ነዉ።የሳልቫ ኪርን አገዛዝ እና የሳልቫ ኪር ጎሳ የዲንካን የበላይነት በመቃወም በየሥፍራዉ ያመፁት ሰባት የተለያዩ ቡድናት ከመንግሥት ጦር እና እርስር በርስ በሚያደርጉት ዉጊያ በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ ተገድሏል።በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ተፈናቅሏል።ወይም ተሰዷል።
አሁን ደግሞ መፈንቅለ መንግሥትና መዘዙ ያንመከረኛ ሕዝብ ከዳግም እልቂት፥ ስደት፥ ዶሎታል። አምና መስከረም ጋዜጠኛዉ ማቸርን ሥለመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የጠየቀዉ፥ የሐገሪቱን የፖለቲካ ዉጥንቅጥ፥ የጎሳ ጠብ፥ ቁርቁስን ሥላወቀ፥ ወይም ሥለገመተ እንጂ-ነብይነት ቃጥቶት አልነበረም።
በጁባ የዩናይትድ ስቴትስዋ አምባሳደር ሱዛን ፔጅ በቀደም እንዳሉት ግን የሆነዉ እንደሚሆን ማወቅ አይደለም የጋዜጠኛዉን ያሕል እንኳን አልገመቱም ነበር።ማንም አልጠበቀም ይላሉ በጁባ የልዕለ ሐያሊቱ ሐገር ዲፕሎማት።ደቡብ ሱዳን፥ የሚባል አይደረግባትም።ከፖለቲካ ዲፕሎማሲዉ ይልቅ፥ ጠመንጃ ጦርነትን ያደጉ የኖሩበት ሳልቫ ኪር የዲንካን፥ እንደ ፖለቲከኛ-ሻጥርን፥ እንደ ዲፕሎማት ግድምድሞሽ ዘይቤን፥ እንደ ታጋይ የጫካ ዉጊያ አጣምረዉ የያዙት ዶክተር ሪክ ማቼር የኑዌር ጎሳን፥ ከየጎናቸዉ አሰልፈዉ ተፋጠዋል።የዚያች ሐገር አበሳ-በሁለቱ ታዋቂ ፖለቲከኞችዋ ጠብ፥ ግጭት አለማብቃቱ ነዉ ክፋቱ።

የኢትዮጵያን ጨምሮ የአካባቢዉ ሐገራት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ጠብ፥ ግጭት፥ ጦርነቱን በሰላም ለመፍታት ባለፈዉ ሳምንት የጀመሩት የድርድር ጥረት ፍሬማ ዉጤት ማሳየቱን ጠቁመዋል።የደቡብ ሱዳኑ ማስታወቂያ ሚንስትር ሚካኤል ማኩይ በፋንታቸዉ መንግሥታቸዉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን አስታዉቀዋል።

ከምሥራቅ አፍሪቃ ሐገራት መካካል ዩጋንዳ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሯን ብቻ ሳይሆን ጦሯንም ነዉ-ጁባ ያዘመተችዉ።የሠላም፥ ዲፕሎማሲና የዉጊያ ዘመቻ!! «የደቡብ ሱዳን ማስታወቂያ ሚንስትር መንግሥታቸዉ «ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር መዘጋጀቱን ሲገልፁ፥የሐገሪቱ የጦር አዛዦች ባንፃሩ አማፂያኑ የሚቆጣጠሩትን ቦርን መልሶ የሚይዝ ጦር እያዘመቱ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል።

አል በሽር አሁንስ ይፈግጉ ይሆን? ደቡብ ሱዳንስ ወዴት፥ እንዴት ትጓዝ ይሆን? ሥለ ማሕደረ ዜና ያላችሁን አስተያየት፥ ማሕደረ ዜና ቢቃኘዉ ጥሩ ነዉ የምትሉትን ጥቆማ በደብዳቤ፥ በስልክ፥ በፌስ ቡክ፥ በኢሜይል፥ በኤስ ኤም ኤስ ላኩልን።እስካሁን አስተያየት ጥቆማ የሰጣችሁኝን አመሰግናለሁ። ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ
Source: www.dw.de 

ሊያበቃ ጥቂት ቀናት የቀረው 2013 ዓም በአፍሪቃ በፖለቲካው እና በማህበራዊው ዘርፎች ከታዩት ዓበይት ክንውኖች ጥቂቱ ባጭሩ ይቃኛል። 
እአአ መጋቢት አምስት፣ 2013 ዓም ኬንያ ውስጥ የአጠቃላዩ ምርጫ ቀን ነበር። ብዙ ሕዝብ ነበር ድምፁን ለመስጠት የወጣው። በተፎካካሪዎቹ ኡሁሩ ኬንያታ እና በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎቹ ጎራ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ነበር የታየው። በምርጫው ኡሁሩ ኬንያታ አሸናፊ ቢሆኑም፣ ድላቸው አካራካሪ ነበር፣ ምክንያቱም፣ ከአምስት ዓመት በፊት እኢአ በ2007 ዓም የተካሄደው ምርጫ ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ በተከተሉት ወራት በሀገሪቱ የ 1,200 ሰዎች ሕይወት የጠፋበትን ግጭት ቀስቅሰዋል በሚል ብዙዎች የሚወቅሱዋቸው ኬንያታ እና በምርጫው ዘመቻ ወቅት
ምክትላቸው እንደሚሆኑ ያጩዋቸው ዊልያም ሩቶ በስብዕና አንፃር ወንጀል ፈፅመዋል በሚል ጥርጣሬ ዘ ሄግ በሚገኘው በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤት፣ በምሕፃሩ በአይ ሲ ሲ ክስ ተመሥርቶባቸዋል። ሆኖም ፕሬዚደንታዊው ምርጫ ከተጠናቀቀ ከአራት ቀናት በኋላ ኬንያታ ተፎካካሪያቸውን ራይላ ኦዲንጋን በጠባብ የድምፅ ብልጫ ማሸነፋቸው በይፋ ተረጋገጠላቸው።
« ውድ የሀገሬ ዜጎች፣ ኬንያውያን ዛሬ የዴሞክራሲን ፣ የሰላምን ድል እና የብሔራዊ አንድነትን ድል እናከብራለን። በዓለም ብዙዎች ምርጫውን በትክክለኛ መንገድ ማካሄድ መቻላችንን ተጠራጥረውት ነበር፤ እኛ ግን ከጠበቁት በላይ ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ብስለት አሳይተናል። » ።

ኬንያታ በአይ ሲ ሲ አንፃር የያዙትን አቋም ካጠናከሩ በኋላ የሀገራቸው ምክር ቤት ኬንያን ከአይ ሲ ሲ ምሥረታ ተፈራራሚ አባል ሀገራት ለማስወጣት ወስኖዋል። ይህ ውሳኔው ግን በኬንያታ እና በሩቶ ላይ በተመሠረተው ክስ ላይ የሚቀይረው ነገር አይኖርም። የኬንያታ ችሎት ያው ቀጠሮ እንደተያዘለት የፊታችን የካቲት በዘ ሄግ ይጀመራል
ግንቦት፣ 2013 በናጀሪያ አክራሪው የሙሥሊሞች ቡድn ቦኮ ሀራም በሰሜናዊ የሀገሪቱ አካባቢ ጥቃቱን አጠናከረ። የናይጀሪያ ፕሬዚደንት ጉድላክ ጆናታን ጦራቸውን በቦኮ ሀራም አንፃር ከማሠማራቱ ጎን፣ በሦስት ያካባቢው ግዛቶች ውስጥ እስከተያዘው አውሮጳዊ ዓመት ማብቂያ ድረስ የሚቆይ አስቸኳይ ጊዜ አወጁ። የገዢው ፓርቲ ቃል አቀባይ አብዱላጂ ጃሎየፕሬዚደንቱን አቋም ገልጸዋል።
« ፕሬዚደንቱ ዝግጁ አይደሉም። በፍፁም ዝግጁ አይደሉም። አንድ ስንዝር መሬት እንኳን በጠላት(ቦኮ ሀራም) የሚያዝበትን ሁኔታ በቸልታ አይመለከቱም። » ይሁንና፣ የጦር ኃይሉ ዘመቻ አሁንም አከራካሪ ከመሆኑም ሌላ ያን ያህል ውጤታማ አይደለም። ባለፈው ሀምሌ በፖቲስኩም በአንድ የአዳሪ ትምህርት ቤት ላይ በተጣለ የቃጠሎ አደጋ ቢያንስ 27 ተማሪዎች እና አንድ መምህር ተገድለዋል። ሌሎች ጥቃቶችም ተከትለዋል። ወደ 500 የሚጠጉ የፅንፈኛው አሸባሪ ቡድን በዚህ ወር መጀመሪያ በማይዱግሪ ከተማ በሚገኘው የአየር ኃይል ሠፈር ላይ በጣሉት ጥቃት አሁንም ጠንካራ መሆኑን ለማሳየት ሞክሮዋል።

ማይዱግሪ ነዋሪ ሙሀመድ ሙሳ የሰዓት እላፊ እያለ ይህን መሳይ ጥቃት በመጣሉ ቅር መሰኘቱን ገልጾዋል። « ጥቃቱ መንግሥት ባካባቢው ላለው የፀጥታ ችግር አንዳችም መፍትሔ እንደሌለው ነው ያሳየው። መንግሥት ስራውን በትክክል እንዲሰራ ነው የምንጠብቀው። ይህ ብቻ ነው ፀጥታ ሊያስገኝ የሚችለው። የአስቸኳይ ጊዜ የሚፈይደው ነገር የለም። »
የዚምባብዌ ላይላይ ፍርድ ቤት ባለፈው ሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ አጠቃላዩ ምርጫ በዚያው በሀምሌ 31፣ እንዲካሄድ ወሰነ። ከአምሥት ዓመት በፊት በሀገሪቱ በተካሄደው የመጀመሪያው ዙር ምርጫ እንደሚታወሰው የተቃዋሚው ወገን ዕጩ ሞርገን ቻንጊራይ ካለፉት ሦስት አሠርተ ዓመታት በላይ በሥልጣን ላይ የሚገኙትን ፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤን በሰፊ የመራጭ ድምፅ ነበር የመሩት። ይሁንና፣ የመለያው ምርጫ ሊደረግ ጥቂት ጊዜ ሲቀረው እና ሙጋቤ በኃይሉ ተግባር መጠቀም ሲጀምሩ ቻንጊራይ የኃይሉ ተግባር እንዳይባባስ በመስጋት ዕጩነታቸውን ሰረዙ። ይህም ካለ ተፎካካሪ የቀረቡትን ሙጋቤ በሥልጣናቸው እንዲቆዚ አስችሎዋል። በዚህ ዓመቱ አጠቃላይ ምርጫም ወቅት ሙጋቤ በምርጫ ማሸነፍ እና መሸነፍ ያለ ነገር መሆኑን ነበር ለተፎካካሪዎቻቸው ለማጉላት የሞከሩት።

« አንድ ሰው ራሱን ለአንድ ውድድር ካቀረበ ሁለት አማራጮች ብቻ መኖራቸውን አውቆ መግባት ይኖርበታል። ማሸነፍ ወይም መሸነፍ ፤፣ ሁለቱን ማግኘት አይቻልም። ወይ ታሸንፋለህ ወይም ትሸነፋለህ። ከተሸነፍክ ሽንፈትህን መቀበል ይኖርብሀል። እና እኛ ይህንን እናደርጋለን፣ ደንቡንም እናከብራለን።
በይፋ በወጡ ውጤቶች መሠረት፣ ፈላጭ ቆራጩ ሙጋቤ በ2013 ዓምም ሥልጣናቸውን እንደገና ለማጠናከር ችለዋል፤ እንዲያውም በምክር ቤት ውስጥ ሕገ መንግሥቱን መቀየር የሚያስችላቸውን ፍፁሙን የመራጭ ድምፅ ነው ያገኙት።

በማሊ የቀድሞው ፕሬዚደንት አማዱ ቱማኒ ቱሬ መጋቢት 2012 ዓም በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ከተወገዱ ወዲህ ሀገሪቱ ቀውስ ላይ ትገኛለች። በሰሜናዊ ማሊ የሚንቀሳቀሱት የቱዋሬግ ዓማፅያን እና አክራሪ ሙሥሊሞች ጥቃታቸውን አጠናክረው አካባቢውን በመቆጣጠር ሕዝቡን ማሸበር እና ወደ መዲናይቱ ባማኮም ግሥገሣቸውን በጀመሩበት ጊዜ ፈረንሳይ ማሊን ለመርዳት እና የዓማፅያኑን ሂደት ለማስቆም ባለፈው ጥር 2013 ዓም በጦር ኃይሏ ጣልቃ ገባች። ከፈረንሳይ ድጋፍ ያገኘው የማሊ ጦርም ያማፅያኑን ቱዋሬጎች ግሥገሣ በመግታት የተኩስ አቁም ደንብ እንዲደርሱ ማድረግ ከተሳካለት ብኋላ ባለፈው ሀምሌ ወር ፕሬዚደንታዊው ምርጫ ተካሂዶ ኢብራሂም ቡባከር ኬይታ አዲሱ ዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጡ ፕሬዚደንት ሆነዋል።
«በኢግዚአብሔር እና በማሊ ሕዝብ ፊት በመቆም ማሊን በታማኝነት ለመከላከል እና ሥልጣኔንንም የሀገሪቱን ጥቅም ለማስጠበቅ እንደምጠቀምበት ፣ ዴሞክራሲን ለመጠበቅ እና የብሔራዊ አንድነትን እና የሀገሪቱን ነፃነት፣ እንዲሁምየግዛት ሉዓላዊነቱን ዋስትና ለማረጋገጥ እንደምሰራ እምላለሁ። »
በዓመቱ የመጨረሻ ወራት ግን በማሊ በተለይ በሰሜኑ ውጥረቱ እንዳዲስ ተካሮዋል። በቱዋሬግ ዓማፅያን እና በጦር ኃይሉ መካከል በተደጋጋሚ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ ዓማፅያኑ ባለፈው ሀምሌ የደረሱትን የተኩስ አቁም አፍርሰዋል። ውጥረቱ ቢካረርም ግን በማሊ የፕሬዝደንት ኢብራሂም ቡባከር ኬይታ ፓርቲ እና ተጓዳኞቻቸው ምክር ቤታዊውን ምርጫ ማሸነፋቸው ተገለጸ። አንድ የመንግሥቱ ባለሥልጣን እንዳስታወቁት፣ በእሁዱ ሁለተኛ ዙር ምክር ቤታዊ ምርጫ ላይ ራሱን ለማሊ የተቋቋመ የጋራ ንቅናቄ ብሎ የሚጠራው ፓርቲ እና ሸሪኮቹ 147 መቀመጫዎች ባሉት ምክር ቤት ውስጥ 115ቱን አግኝተዋል።

መስከረም 21፣ 2013 ዓም በኬንያ መዲና ናይሮቢ፤ አሸባሪዎች ዌስትጌት የተባለውን ግዙፍ መደብር አጥቅተው በርካቶችን ገድለዋው ብዙዎችን አቆሰሉ። ለጥቃቱ የሶማልያ አሸባብ ቡድን ኃላፊነቱን ወስዶዋል።« ኬንያውያን አሁን በዌስትጌት የገበያ መደብር የደ,ረሰባቸው ጥቃት የናንተ ጦር ለሚፈፅመው ወንጀል ማካካሻ ነው። »
ኬንያ ጦሯን ወደ ሶማልያ ከላከች ወዲህ ሶማሊያውያን አሸባሪዎች ኬንያ ውስጥ በተደጋጋሚ ጥቃ ጥለዋል። ከጥቃቱ በኋላ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ ባሰሙት ንግግር በጥቃቱ ዘመዶቻቸውን እና የዝርቦቻቸውን ላጡት ሀዘናቸውን ገልጸዋል። «በዚህ ጥቃት የቤተሰብ አባላትን ላጡ ወገኖች ሃዘኔን እገልጻለሁ። ምን አይነት የሃዘን ስሜት ዉስጥ እንዳሉ መገመት አይሳነኝም፤ ምክንያቱም እኔም በዚህ ጥቃት በጣም ቅርብ ዘመዶቼን አጥቻለሁ»
ጥቃቱ በተጣለ በአራተኛው ቀን የኬንያ ወታደሮች ወደ መደብሩ በመግባታ አምሥት አጋቾችን ገድለዋል። በጥቃቱን 67 ገደሉ፣ 300 አቆሰሉ፣ ከ 60 በላይ የሚሆኑትም ደብዛቸው እንደጠፋ ነው። ሞዛምቢክ ውስጥ የርስበርሱ ጦርነት ካበቃ ከሁለት አሠርተ ዓመት በኋላ የቀድሞው ያማፅያን ቡድን b ሬናሞ የ16 ዓመቱን የርስ በርስ ጦርነት ያበቃውን እአአ በ1992 ዓም ከገዚው የፍሬሊሞ ፓርቲ ጋ በይፋ የተፈራረመውን ውል ባለፈው ጥቅምት 2013 ዓም ማፍረሱን አስታወቀ። ሬናሞ ይህን ርምጃ የወሰደው የመንግሥቱ ጦር የጦር ሠፈሩን በቦምብ ያጠቃበትንና የያዘበትን ድርጊት በመቃወም ነበር።
ካለፈው ሚያዝያ ወዲህ መንግሥት የተቃዋሚው ቡድን አባላትን በብዛት ማሰር ከጀመረ ወዲህ ሬናሞ በምላሹ በፀጥታ ኃይላት ላይ ጥቃቱን በማጠናከር ዋነኛውን መተላለፊያ መንገድ ዘጋ፣ ብዙዎች ይህንን ሂደት በሀገሪቱ ከሁለት አሠርተ ዓመታት በፊት ታይቶ የነበረው ዓይነቱ የከፋ ቀውስ ሊነሳ እንደሚችል የሚጠቁም ሆኖ ተመልክተውታል።
« በስጋት መንፈሥ ውስጥ ነው የምንኖረው። እርግጥ፣ በዋናው መተላለፊያ መንገድ መዘጋት በቀጥታ ተጎጂ የሆኑት ሰዎች ርምጃው ያን ያህል እንዳላስጨነቃቸው ገልጸዋል። ይሁንና፣ ከዚሁ አካባቢ ጋ የተጎራበቱት ግዛቶች ሕዝብ ሞዛምቢክ እንደገና እርስ በርሱ ጦርነት ውስጥ ልትወድቅ ትችል ይሆናል በሚል መስጋቱ አልቀረም። »


እአአ ጥቅምት ሦስት፣ 2013 ዓም 500 የሚቆጠሩ ስደተኞችን ያሳፈረች ጀልባ በኢጣልያዋ ደሴት ላምፔዱዛ አቅራቢያ ሰጠመችበት አደጋ 390 ሞቱ። ከሊቢያ ወደ አውሮፓ ስትጓዝ በሰጠመችው ጀልባ ከተሳፈሩት ስደተኞች መካከል ብዙዎቹ ኤርትራውያን እና ሶማልያውያን ነበሩ። የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ አደጋ በደረሰበት ዕለት በሰጡት መግለጫ ላይ እጅግ ማዘናቸውን አስታውቀዋል።
« በዚህ ዛሬ በላምፔዱዛ እንደገና በደረሰው አሳዛኝ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡትን ሰለባዎች ማሰብ እፈልጋለሁ። አደጋው መድረሱ አሳፋሪ ነው። »
አደጋው የአውሮጳ ሀገራት በሚከተሉት የስደተኞች አቀባበል ፖሊሲ ሰፊ ክርክር አስነስቶዋል። ፖለቲካኞች ለጀልባዋ መስመጥ ሕገ ወጦቹን ሰው አሸጋጋሪዎች ተጠያቂ አድርገዋል። በኢጣልያ የሚገኙት ኤርትራዊው ካቶሊካዊው ቄስ አባ ሙሴ ግን በፖለቲከኞቹ አስተሳሰብ አይስማሙም። እንደ እርሳቸው አስተያየት፣ ስደተኞቹ ሕይወታቸውን ለአደጋ ለሚያጋልጡበት ሁኔታ ሕገ ወጦቹ ሰው አሸጋጋሪዎች መንሥዔ አይደሉም። መንሥዔው በየሀገሮቻቸው ያለው ጨቋኝ ሥርዓት እና ምስቅልቅል ሁኔታ ነው ባይ ናቸው። « አውሮጳውያት ሀገራት በሕገ ወጦቹ ሰው አሸጋጋሪዎች አንፃር በርግጥ መታገል ከፈለጉ ብቸኛው አማራጭ ተገን ፈላጊዎቹ ወደ አውሮጳውያቱ ሀገራት በሕጋዊ መንገድ መግባት እንዲችሉ ድንበሮቻቸውን ክፍት ማድረግ አለባቸው። »
በዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ በመንግሥቱ ጦር አንፃር የተዋጋው ራሱን «ኤም 23» ብሎ የሚጠራው ያማፅያን ቡድን አባላት ካለፈው አንድ ዓመት ወዲህ በምሥራቃዊ የሀገሪቱ ከፊል ሕዝቡን ሲያሸብሩ ቆይተዋል። በኮንጎ ጦርና በ «ኤም 23» መካከል ውጊያው ተባብሶ ከቀጠለ እና በተለይ ያማፅያኑ ጥቃት ሰላማዊ ሰዎችን ዒላማ ቢያደርግም፣ በኮንጎ ሰላም አስከባሪዎች ያሠማራው የተመድ በውዝግቡ ጣልቃ መግባት አልቻለም ነበር፤ ምክንያቱም ተልዕኮው ስለማይፈቅድለት። በዚህም የተነሳ፣ የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት የሕዝቡን ስቃይ ለማብቃት ይቻል ዘንድ አንድ 3000 ወታደሮች የሰለፈ አጥቂ ቡድን ለመላክ ወሰነ። ጀርመናዊው ማርቲን ኮብለር የመሩት ይኸው ቡድን ወዲያው ከኮንጎ መደበኛ ሠራዊት ጎን በመሆን የጥታ ስጋቱን በማስወገዱ ተግባር ላይ ተሠማራ።
« ወደ ኮንጎ የመጣነው ለሕዝቡ ከለላ ለመስጠት ነው፤ ማለትም፣ በተለይ ለጎማ ሲቭል ሕዝብ ከለላ መስጠት ነው ዋናው ተልዕኳችን። በሲቭሉ ሕዝብ ላይ የሚሰነዘረው ጥቃት እንዳይደገም ለማድረግ ስንልም ከኮንጎ ጦር ጎን በመሰለፍ በሚቻለን ሁሉ ባማፂው ቡድን አንፃር ወታደራዊው ዘመቻ አካሂደናል። »
በዚሁ የተመድ እና የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፑብሊክ ጦር የጋራ ዘመቻ «ኤም 23» ተሸንፎ እአአ ባለፈው ህዳር አምስት ናይሮቢ ኬንያ ላይ መንግስቱ ጋ የሰላም ስምምነት ተፈርሞዋል። ሁለቱ ወገኖች በተፈራረሙት ስምምነት መሠረት አማፂዉ ቡድን ተዋጊዎቹን ትጥቅ በማስፈታት ራሱን ወደፖለቲካ ፓርቲነት መለወጥ እና የሰላም ስምምነቱ የ«ኤም 23» አባላት በጦነቱ ለፈጸሙት ጥፋት ምህረትን የሚያገኙበትንም መንገድ መመልከት ይኖርበታል


የሳውዲ ዐረቢያ መንግሥት ሕገ ወጥ ያላቸውን የውጭ ዜጎች ከሀገሩ ለማስወጣት ከጀመረች ወዲህ የኢትዮጵያ መንግሥት ወደ 140,000 የሚጠጉ ዜጎቹን ወደ ሀገር መመልሶዋል። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸዉ ረዳ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳይኖራቸዉ ሳዉዲ ሚገኙት ዜጎች ወደሀገር መመለሱ ተግባር ቅድሚያ ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
የሳውዲ ዐረቢያ መንግሥት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ለሌላቸው የውጭ ዜጎች የሰጠው የሰባት ወር የምሕረት ቀነ ገደብ ባለፈው ህዳር ወር ካበቃ በኋላ ከፖሊስ ጋ በተፈጠረ ግጭት ሦስት ኢትዮጵያውያን መገደላቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የፈላስያን ጉዳዮች ተመልካች ድርጅት «አይ ኦ ኤም» በቅርቡ ከሪያድ፣ ከጄዳ እና ከመዲና ተጨማሪ 35,000 ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ ብለው ይጠብቃሉ።
የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ቀውስ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ባለፈው መጋቢት ፣ 2013 ዓም የሴሌካ ዓማፅያን ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር የቀድሞ የሀገሪቱን ፕሬዚደንት ፍራንስዋ ቦዚዜን በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ በሀገሪቱ በሚሼል ጆቶጂያ የሚመራ የሽግግር መንግሥት ተቋቁሞዋል። የታጠቁ፣ በብዛት ሙሥሊሞች የሆኑ የቀድሞዎቹ ያማፅያን ቡድኖች ብዙውን የሀገሪቱን ከፊል ተቆጣጥረዋል። እርግጥ፣ ከሽግግሩ መንግሥት ምሥረታ በኋላ የሀገሪቱ መሪ ሚሼል ጆቶጂያ ያማፀያኑን ቡድንኖች በመበተን በብሔራዊው ጦር ውስጥ ቢያዋህዱም፣ ትጥቅ ያልፈቱት በብዛት ሙሥሊሞቹ የቀድሞ ሴሌካ ዓማፅያን በርካታ መንደሮችን እያጠቁ በብዛት ክርስትያኑን ሲቭ ሕዝብ በማሸበር ላይ እንደሚገኙ ተገልጾዋል። ራሳቸውን ከሴሌካ ጥቃት ለመከላከል በተደራጁ የክርስትያን ሚሊሺያዎች እና ዓማፅያኑ መካከል በቀጠለው ግጭት ብዙዎች መገደላቸውን እና መፈናቀላቸው ተሰምቶዋል። ውዝግቡ ወደ ሀይማኖት እና ጎሳ ግጭት ሊቀየር እና በርዋንዳ የታኢ,ውን ዓይነት የጎሣ ጭፍጨፍ እንዳይከሰት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስጠንቅቀዋል። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ፣ ሂውማን ራይትስ ዎች ባልደረባ የቡድኑን ጥቃት አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን አስጠንቅቋል።

« ሂውማን ራይትስ ዎች የቀድሞ የሴሌካ ዓማፅያን በርካታ አስከፊ ወንጀሎችን መፈፀማቸውን የሚያሳዩ ማስረጃዎችን ሰብስቦዋል። በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች፣ በመዲናዋ ባነግዊን ጭምር የሚገኙት እነዚሁ ዓማፅያን ባሁኑ ጊዜ ከቁጥጥር ውጭ ሆነዋል። በመጨረሻ የመዘገብነው አሰከፊ ወንጀል በጋጋ አካባቢ፣ ኦምቤላምቦኮ በተባለ መንደር ሲሆን በዚያ የሴሌካ ዓማፅያን በመንደሩ ላይ ጥቃትበመሰነዘር በነዋሪዎቹ ላይ እጅግ አስከፊ ወንጀል ፈፅመዋል። »
ይህን ተከትሎ የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤትየቀድሞ የማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ ፍሪቃዊቱ ሀገር ያለውንከ3500 ወደ 6000 ከፍ ይላል የሚባለውን የአፍሪቃ ህብረት ጓድ እንዲጠናክር ያቀረበችው ማመልከቻን አፅድቋል። በዚህም መሠረት በዚያ 600 ወታደሮች ያሉዋተ ፈረንሳይ ተጨማሪ 1000 ልካለች። በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የፈረንሳይና የአፍሪቃ ኅብረት ኃይሎች ቢገኙም የሰላማዊ ሰዎች ግድያ አልቆመም።

የቀድሞውን የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝዳንት እና እውቁ የፀረ አፓርታይድ ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ እአአ ታህሳስ አምሥት 2013 ዓም በ95 ዓመታቸው ማረፋቸውን የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ጄኮብ ዙማ በይፋ አስታወቁ። የነፃነት እና የመቻቻል ተምሳሌት ሆኑትን ለኔልሰን ማንዴላ ሶዌቶ ደቡብ አፍሪቃ በሚገኝ ስታድዮም በተደረገው ይፋ ስንብት ላይ ወደ አንድ መቶ የሚጠጉ የዓለም መሪዎች፤ ቤተሰቦቻቸው፤ ወዳጆቻቸው እና በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ከመላው ደቡብ አፍሪቃ የመጣ ህዝብ ተገኝቶ ነበር፣ ከዚያም የደቡብ አፍሪቃ ሕዝብ ለሦስት ቀናት በፕሪቶርያ ከተወዳጁ መሪው ስንብት ካደረገ በኋላ ሥርዓተ ቀብራቸው በትውልድ መንደራቸው ኩኑ 4,500 ሰዎች፣ በርካታ መሪዎች ጭምር በተገኙበት ተፈፅሞዋል።
ከሁለት ዓመት በፊት ነፃነቷን ባገኘች ደቡብ ሱዳን ውስጥ በፕሬዚደንት ሳልቫ ኪር እና በቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት ሪክ ማቻር ታማኝ ወታደሮች መካከል ካለፈው እሁድ ወዲህ ውጊያው ቀጥሎዋል። በመዲናይቱ ጁባ ብቻ ከ500 የሚበልጥ ሰው መገደሉ እና በርካቶች መቁሰላቸው ተሰምቶዋል። ከ16000 የሚበልጡም መፈናቀላቸው ተገልጾዋል።
ስለመዲናይቱ ጁባ ወቅታዊ ሁኔታ አስተያየት የሰጡት በዚያ ያሉት የተመድ ሰብዓዊ ርዳታ አስተባባሪ ቶቢ ላንዛ ሲቭሉ ሕዝብ ለደህንነቱ መስጋቱን ገልጸዋል።
« በአሁኑ ጊዜ ጁባ ውስጥ ሁኔታው ጥቂት ተረጋግቶዋል። 16,000 ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ግን የተመድ ሰላም አስጠባቂዎችን ከለላ ለማግኘት ሲሉ በከተማይቱ ባሉት ሁለት ሠፈሮቻችን ውስጥ ወይም በዚያው አቅራቢያ ይገኛሉ። እንደሚመስለኝ ውኃን የመሳሰሉ መሠረታዊ ርዳታዎች ጭምር ያስፈልጋቸዋል። »
ሳልቫ ኪር ማቻርን ከከሸፈ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ ሁከት እንዲባባስ አድርገዋል ሲሉ ይወቅሳል። አሁን ከመዲናይቱ ጁባ ወደ ሌሎች አካባቢዎች የተስፋፋው ውጊያ ደቡብ ሱዳንን በጎሣ ከፋፍሏታል።
አርያም ተክሌ
ልደት አበበ
Source: www.dw.de

የሰሜን ሱዳን የፖለቲካ ተጽእኖና ፤ የዐረብ ባህል ጫና አንገሽግሾት 22 ዓመታት መሪር ትግል ያካሄደው የደቡብ ሱዳን ህዝብ፤ ነጻነት ባወጀ በ 2 ዓመት ከመንፈቅ ገደማ ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ውጊያ እንዳያመራ አሥግቷል። ባለፈው እሁድ በመዲናይቱ 
በጁባ ያገረሸው ውጊያ ፣ የ 500 ያህል ሰዎችን ሕይወት ቀጥፎ ፤ 34,000 ሰዎች፤ በተባበሩት መንግሥታት ጣቢያዎች መጠለያ እንዲሻ አስገድዷል ። የሥልጣን መቀናቀን ነው የተባለለት ውዝግብ ፣ በጎሣ ልዩነት ተካሮ ባፋጣኝ ወደሌሎች አካባቢዎች መዛመቱ የሚታወስ ነው። ጉዳዩ ያሳሰባቸው የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት ሚንስትሮች ፤ የአፍሪቃ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ተወካዮች ጁባ ውስጥ ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት
ሳልባ ኪር ጋር በዛሬው ዕለት እንደሚወያዩ ይጠበቃል። ስለደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ይዞታ ፣ በፀጥታ ጉዳይ ተቋም፤ (ISS)የምሥራቅ አፍሪቃ ፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ በማነጋገር የተጠናቀረው ዘገባ የሚከተለው ነው።
ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ባለፈው ዓመት በሐምሌ ወር ምክትላቸውን ሪኤክ ማቻርን ከስልጣን ካሰናበቱ ወዲህ ቁርሾው አይሎ፣ የሥልጣን ሽኩቻው ባለፈው እሁድ መፈንዳቱ የሚታወስ ነው። የጎሣ ልዩነትን ብቻ መሠረት ባደረገ በዚያ የተኩስ ልውውጥም ሆነ የኃይል እርምጃ፤ ብዙ ሰዎች ያላበሳቸው የጥይት ራት የሆኑበት ድርጊት የተባበሩትን መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ኀላፊ ናቪ ፒላይን እጅግ እንዳሳዘነ ተመልክቷል። ራሳቸው የተ መ ድ ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን፤ በበኩላቸው ፣ ውዝግቡ ባስቸኳይ በፖለቲካ ውይይት መላ እንዲፈለግለት ነው ያስገነዘቡት።
አንዳንድ የ ምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት (IGAD) አባል ሃገራት ውዝግቡን በቀላል ሊፈታ እንደሚችል በተስፋ ይሁን ዲፕሎማሲያዊ ፈሊጥ አድርገው ያን ያህል የሚያሳስብ እንዳልሆን መግለጫ ቢሰጡም፤ ተጨባጩ ይዞታ የሚያረጋጋ ሆኖ አልተገኘም። አንዳንድ መንግሥታት ዜጎቻቸውን ለማስወጣት አኤሮፕላኖች ን በመላክ ላይ ናቸው። አሶኬ ሙከርጂ የተባሉት ህንዳዊ የተባበሩት መንግሥታት ልዑክ፤ 3 ህንዳውያን ሰላም አስከባሪዎች፤ ሆን ተብሎ የጥይት ዓላማዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ዩጋንዳ ዜጎቼን ለመጠበቅ ነው በሚል ሰበብና ከጁባ መንግሥትም ጥሪ ቀርቦልኝ ነው በማለት ፤ በዛሬው ዕለት በደቡብ ሱዳን መዲና ጦር ሠራዊት አሠማርታለች። ትናንት ብርቱ ማስጠንቀቂያ ያሰሙት የዩናይትድ እስቴትሱ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ 45 ወታደሮቻቸው እንዲሠማሩ አድርገዋል። የዚህ ያልተጠበቀ መስሎ የቆየው ውዝግብ ፍንዳታ ዋና መንስዔው ምን ይሆን? ዋና ጽ/ቤቱ በፕሪቶሪያ ፤ ደቡብ አፍሪቃ በሚገኘው የፀጥታ ጉዳይ ተቋም ፣ የምሥራቅ አፍሪቃ የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ አንድርውስ አታ አሳሞዋ--
\ «ጉዳዩን ሰፋ አድርገን ካየነው፣ በፕሬዚዳንቱ ክብር ዘብ የተፈጠረ ምሥቅልቅል፤ የአገሪቱን የፖለቲካ ክፍፍል አሥፍቶታል። የጎሣ ልዩነትም እንዲጎን ነው ያደረገው። ቀስ በቀስምየጎሳ ልዩነትን በማባባስ፣ በፖለቲካው አመራር ለረጅም ጊዜ የቆየውን ክፍፍል በጦር ሠራዊቱና በብሔረሰቦችም ዘንድ ጥርጣሬውን ያባብሰዋል። ይህ ደግሞ፣ አገሪቱ ነጻነት ከማወጇ በፊት አንስቶ ብዙዎች ሲፈሩት የነበረውን ውዝግብ እውን ሊያደርገው በቅቷል።»

ደቡብ ሱዳን እ ጎ አ ከ 1983-2005 ባካሄደችው የ 22 ዓመታት መሪር የትጥቅ ትግል ከ 2 ሚሊዮን በላይ ተወላጆቿን እንዳጣች ነው ታሪኳ የሚያስረዳው። ስለሆነም ሰፊ መስዋእትነት የከፈለ ህዝብ አሁን እርስ በርስ እንዳይፋጅ ያሠጋበት አደጋ ስለመኖሩ በሚነገርበት ወቅት ውዝግቡ በቀላል እንደሚፈታ መገመት ይቻላል?
«ሳልቫ ኪርንና ሪኤክ ማቻርን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ማምጣቱ ከሞላ ጎደል ቀላል ሊሆን ይችላል። ይህ ግን ሁለቱን የፖለቲካ መሪዎች ወይም ተቀናቃኞች የሚመለከት ነው። ግን ፤ ጉዳዩ የዲንካና የኑኤር መቀናቀን መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም። በፖለቲካው መስክ በከፍተኛ አመራር ላይ ባሉት ቅራኔውን እንደምንም ማርገብ ቢቻል እንኳ በሀገሪቱ በመላ ሲብላላ የቆየው ችግር እንደምናስበው በቀላሉ ሊወገድ የሚችል አይደለም።»
የደቡብ ሱዳንን ውዝግብ፣ የካርቱምን መንግሥት በጥሞና ነው የሚመለከተው። በአንድ በኩል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ጋር የሚወያዩባቸው አንዳንድ ዐበይት የጋራ ጉዳዮች በአንጥልጥል እንዲቀሩ አይሻም። በሌላ በኩል የካርቱም መንግሥት ለአፈንጋጩ ሪኤክ ማቻር ሊያደላም ሆነ ሊደግፍ እንደሚችል የሚናገሩ አሉ። በደቡብ ሱዳን የተፈጠረው ውዝግብ እንዲወገድ ተጽእኖ በማድረግም ሆነ በመሸምገል መፍትኄ ሊያፈላልጉ የሚችሉ አገሮች ን መጥቀስ ያቻላል?

«የአካባቢው አገሮች፤ ዩጋናዳ ኬንያና ኢትዮጵያ ጁባን በሰፊው ማግባባት የሚችሉ ናቸው። ጎረቤቶች ስለሆኑ ብጻቻ አይደለም። ሰሙኑን ሳያገልሉ፣ በጦርነቱ ወቅት የተጫውቱት ሚና እጅግ ከፍ ያለ ነው። ደቡብ ሱዳን ለአነዚህ አገሮች ዐቢይ ከበሬታ ነው ያላት። ብዙዎች ደቡብ ሱዳናውያን፤ ኬንያን በአስተናጋጅነቷ ብቻ ሳይሆን ፤ ብዙ የሚያቀራርቧቸው ጉዳዮች እንዳሉም ይሰማቸዋል። ያም ሆነ ይህ «ኢጋድ» በመሪነት መላ ቢሻ በጣም ጥሩ ነው፤ ይሁንና ዩጋንዳን የመሳሰሉ አገሮችም ለደቡብ ሱዳን መልሶ ሰላም ለማስገኘት በከፍተኛ ደረጃ ተሰሚነት ያላቸው መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም።»
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሠ
Source: www.dw.de

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚለዉ ፕሬዝዳት ኪየር የሚወለዱበት የዲንካ እና ማቼር የሚወለዱበት የኑዌር ጎሳዎች መልክ እና ባሕሪ የያዘዉ ዉጊያ ፈጣን መፍትሔ ካላገኘ አደገኛ ነዉ።ደቡብ ሱዳን፥ ነፃነት ያወጀችበትን ሁለተኛ ዓመት-ከመንፈቅ፥ ከረጅም ጦርነት የተላቀቀችበትን ሥምንተኛ ዓመት፥ እነሆ በጦርነት ልታከብር ዉጊያ ጀምራለች።
የደቡብ ሱዳን መንግሥት ጦር እና በመንግሥት ላይ ያመፁት ሐይላት ወታደሮች ባለፈዉ ዕሁድ ርዕሠ-ከተማ ጁባ ዉስጥ የጀመሩት ዉጊያ ወደ ሌሎች የሐገሪቱ አካባቢዎች እየተዛመተ ነዉ።የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት የሪክ ማቼር ታማኞች የተባሉት ሐይላት ዛሬ ቦር የተባለችዉን ከተማ ተቆጣጥረዋል።በሌሎች አካባቢዎችም ዉጊያዉ መቀስቀሱ ተዘግቧል።የዉጪ መንግሥታት ዜጎቻቸዉን ከአዲሲቱ ሐገር እያሰወጡ ነዉ።ለግጭቱ ሠላማዊ መፍትሔ ለማፈላለግ ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የአካባቢዉ ሐገራት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮቻቸዉን ወደ ጁባ ልከዋል።ነጋሽ መሐመድ አጭር ዘገባ አለዉ።

አዲሲቱ አፍሪቃዊት ሐገር ነፃነትዋን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርግጥ ዉጊያ ጦርነት ተለይቷት አያዉቅም።የእስካሁኑ ጦርነት ዓለም ፈጥኖ-ጣልቃ ለመግባት፥ አለያም ከዋሽግተን፥ ብራስልስ ብዙ ጊዜ እንደሚሰማዉ ካርቱሞችን ደፍሮ ለማዉገዝ የሚጣደፍበት ነበር።ወይም «የጎሳ ግጭት» ብሎ የሚያቃልለዉ ዓይነት።ያሁኑ ከመጀመሪያዉ ይልቅ-ሁለተኛዉን፥ ከሁለተኛዉ ይበልጥ ደግሞ የፖለቲካ ሽኩቻ፥ የሥልጣን ሽሚያ፥ እና የርስ-በርስን ጦርነት መልክ እና ባሕሪ የተላበሰ ነዉ።

እርግጥነዉ የወቅቱን የአፍሪቃ ሕብረት እና የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በእንግሊዝኛ ምሕፃረ-ቃሉ የሊቀመንበርነት ሥልጣን የያዘችዉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸዉ ረዳ ግጭቱ በመገናኛ ዘዴዎች እንደሚዘገበዉ አይደለም ይላሉ።
ከጁባ፥ ከካምፓላ፥ ከናይሮቢ የሚወጡ ዘገቦች ግን ተቃራኒዉን ነዉ የሚሉት።ዕሁድ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራን ተላብሶ ጁባን እስከ ትናንት ባናወጠዉ ዉጊያ በትንሽ ግምት ከስድስት መቶ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።ወደ ሃያ ሺሕ የሚጠጉ አንድም ተሰደዋል፥ አለያም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅጥር ግቢዎች ሙጥኝ ብሏል።
ዛሬ ርዕሠ-ከተማይቱ ዉጊያዉ ጋብ፥ ቀለል ሲልላት ቦርን ይለብቃት ይዟል።የመንግሥት ጦር ቃል አቀባይ ፊሊፕ አጉዋር ጦራቸዉ ቦር ላይ መሸነፉን ዛሬ ጠዋት አምነዋል።ቃል አቀባዩ እንዳሉት ቦርን የሚቆጣጠረዉ የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት የሪክ ማቻር ታማኞች ናቸዉ።
በ2011 በመንግሥት ላይ አምፀዉ ኋላ ተደራድረዉ የመንግሥት ጦርን ተቀላቅለዉ የነበሩት ሐይለኛ የጦር ጄኔራል ፒተር ጋዴት ማቼርን ደግፈዉ ጆንግሌይ የሠፈረዉን የመንግሥት ጦር ማጥቃት ይዘዋል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚለዉ ቶሪት የተባለችዉ ከተማም በዉጊያ እየራደች ነዉ።ዩናይትድ ስቴትስ፥ ብሪታንያ እና ሌሎችም ምዕራባዉያን ሐገራት ተፋላሚዎችን ከመሸምገል በፊት ሁሌም-እንደሚያደርጉትን የዜጎቻቸዉን ሕይወት ለማትረፍ ከዚያ ማስወጣቱን አስቀድመዋል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል አቀባይ ጌታቸዉ ረዳ እንዳሉት መንግሥታቸዉ እንደሌሎቹ መንግሥታት ሁሉ ዜጎቹን ባያስወጣም የጥንቃቄ እርምጃ እየወሰደ ነዉ።


ፕሬዝዳት ሳላቪ ኪር እና ኪር ከሥልጣን ያስወገዷቸዉ የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት ሪክ ማቻር እንደጫሩት የሚታሰበዉን እሳት ለማጥፋት «አንድ ሁለት» ማለት የጀመሩት የኢጋድ አባል ሐገራት ናቸዉ።ኢትዮጵያ፥ ኬንያ፥ ጀቡቲ እና ዩጋንዳ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮቻቸዉን ወደ ጁባ ልከዋል።
የሚንስትሮቹ ተልዕኮ ሁኔታዉ «እንዳይባባስ መግታት» ከሚል ጥቅል መግለጫ በስተቀር ዝር ዝር ጉዳዩ አልተነገረበትም።መፈንቅለ መንግሥት በማሴር የተወነጀሉት የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝዳት ማቼር ያሉበት ሥፍራ አይታወቅም።በመፈንቅለ መንግሥቱ የተጠረጠሩ አስር የቀድሞ ባለሥልጣናት እና ፖለቲከኞች ታስረዋል።አንዳድ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ሚንስትሮቹ ምናልባት ተፋላሚዎችን ለማደራደር ይሞክሩ ይሆናል።አቶ ጌታቸዉ ግን ይሕን ማረጋገጥ አልፈለጉም።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚለዉ ፕሬዝዳት ኪየር የሚወለዱበት የዲንካ እና ማቼር የሚወለዱበት የኑዌር ጎሳዎች መልክ እና ባሕሪ የያዘዉ ዉጊያ ፈጣን መፍትሔ ካላገኘ አደገኛ ነዉ።ማም-ምን አለ ምን ደቡብ ሱዳን፥ ነፃነት ያወጀችበትን ሁለተኛ ዓመት-ከመንፈቅ፥ ከረጅም ጦርነት የተላቀቀችበትን ሥምንተኛ ዓመት፥ እነሆ በጦርነት ልታከብር ዉጊያ ጀምራለች።
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ
Source: www.dw.de
 
በፓሪስና በኒው ዮርክ የሚገኙት ፣ ድንበር አያግዴው የጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) እና ለጋዜጠኞች ህልውናና መብት ተሟጋቹ ፤ (CPJ)፣ በዓለም ዙሪያ የጋዜጠኞችን ፍዳ የሚዘረዝረውን ዓመታዊ መግለጫቸውን ይፋ አደረጉ። ለመገባደድ 2 ሳምንት ገደማ በቀረው 2013 ጎርጎሪዮሳዊው ዓመት
ውስጥ 71 ጋዜጠኞች መገደላቸውናና 178 በእሥራት በመማቀቅ ላይ እንደሚገኙ የወጣው ዘገባ ያስረዳል። ጋዜጠኞችን አሥሮ በማሠቃየት ከተወቁት 10 ሃገራት መካከል፤ ኤርትራ ፣ ኢትዮጵያ፤ግብፅ ፣ ቪየትናም፤ ሶሪያ ፤ አዘርባጃንና ዑዝቤኪስታን ይገኙበታል። በአፍሪቃው ቀንድ የጋዜጠኞችን ይዞታ የሚከታተሉትን ፤ በምሥራቅ አፍሪቃ የ CPJ ን ተጠሪ በማነጋገር ፤ ተከታዩን ዘገባ አቅርበናል።
በሥራ ላይ እንዳሉ ጋዜጠኞች ሕይወታቸውን ያጡባቸው አካባቢዎች ፤ እስያ፤ (24 ናቸው የተገደሉት፤)መካከለኛው ምሥራቅና ሰሜን አፍሪቃ (23) ከሰሐራ ምድረ በዳ በስተደቡብ በሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራት አምና 21 እንደተገደሉ ሲታወቅ ዘንድሮ ከሞላ ጎደል በግማሽ ቀንሶ (10) ጋዜጠኞች
ናቸው ሕይወታቸውን የገበሩት። ግድያው በአመዛኙ ፍልሚያ በሚካሄድባት ሶማልያ ነው የተፈጸመው። አምና 18 ፤ ዘንድሮ 7!
በአፍሪቃው ቀንድ ፤ በእሥራት የሚማቅቁት ቁጥር ቀላል አይደለም። ስለሆነም CPJ ቢ,ታሠሩ ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ ከመጠየቅ አልቦዘነም፣ የአፍሪቃውን ቀንድ፤ በተለይ የኢትዮጵያ ን የኤርትራንና የጂቡቲን ጋዜጠኞች ይዞታ እንዴት እንደሚገመግሙት ፤ የ CPJ ውን ተወካይ ቶም ሮደስን በስልክ ጠይቄአቸው ነበር።
«ሂደቱ ፤ አዝማሚያው ፤ የሚያሳዝን ነው፤ አለመታደል ሆኖ ባለፉት ዓመታት የታዘብነው ነው እንደቀጠለ ያለው። ከሰሐራ በስተደቡብ በሚገኙ አገሮችን አያያዝ፣ በዛ ያሉ ጋዜጠኞች የመታሠራቸው ጉዳይ የአፍሪቃው ቀንድ ይዞታ ፤ የአፍሪቃ ሕብረት አያኢዝ ተምሳሌት ነው።»
CPJ, RSF, እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ AI ,HRW ስለጋዜጠኞችም ሆነ በአጠቃላይ ስለሰብአዊ መብትና የፕረስ ነጻነት እንደሚቆረቆሩ የሚሰማ ጉዳይ ነው። ተሰሚነት ያላቸው እዚህ ላይ አንዳንድ ምዕራባውያን መንግሥታት ፣ ምን ማድረግ ይኖርባቸዋል ይላሉ?


«ጥሩ ጥያቄ ነው ያነሣህ፤ ግን ጥሩ መልስ አላገኝልህም። ልክ ነህ፤ CPJ ፤ RSF እና ሌሎች ያለማቋረጥ፤ ብዙዎች ጋዜጠኞች መታሠራቸውን እናወግዛለን። የወረበባቸውንም ክስ አጠያያቂ አድረገን ነው የምንመለከተው። ለምሳሌ የኤርትራውን ብትመለከት፣ በ 22 የክስ አንቀጾች የተከሰሱት ሰዎች ጉዳይ ሲመረመር ፣ አንዳችም ፍርድ ቤት ክስ አልተመሠረተባቸውም። እነዚህን መንግስታት በተቻለ መጠን እንሟገታቸዋለን።
ህጋዊ ምርመራ እንዲካሄድ እንደጠይቃለን፤ ለምሳሌ በኢትዮጵያ የተደረገው ዓይነት ማለት ነው፤---። ግን ይህ በቂ አይመስለኝም። በመጨረሻ ፍትሕ እንዲያገኙ ማድረግ ይጠበቅናል። ብዙዎች፤ በሚያሠቅቅ ሁኔታ ነው እሥር ቤት ውስጥ የሚገNUት። ታሣሪዎቹ ጋዜጠኞች፤ ሊፈቱ በሚችሉበት ተስማሚ መፍትኄ ከመንግሥት ጋር ለማግኘት ከዚህ የላቀ ተግባር ማከናወን ይጠበቅብናል።»
ዋና ጽ/ቤቱ በኒውዮርክ የሚገኘው ለጋዜጠኞች ደህንነት የሚታገለው ድርጅት CPJ የአፍሪቃው ቀንድ ጉዳይ ተመልካች ቶም ሮደስ ፤ በደል የፈጸሙ ሰዎች ከመከሰስ ነጻ የሆኑበትን አሠራር እስመልክተው እንዲህ ነበረ ያሉት።


« CPJ ዘመቻ ከሚያካሂድባቸው ጉዳዮች አንዱ በደል ፈጽሞ በቸልታ መታለፍን ነው። እናም መንግሥታት፤ ያወጡትን ሕግ አክብረው መብት እንዲጠበቅ ያደርጉ ዘንድ ነው የምናስገነዝባቸው። እንደሚመስለኝ፤ችላ መባል ነው፤ በአፍሪቃው ቀንድ ዘገባችን እንደሚያመለክተው ብዙ ጋዜጠኞች እንዲታሠሩ ያደረገው።»

ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሰ
Source: www.dw.de
ፍልስጤም-እስራኤሎች፥ ዋሽንግተን፥ ሞስኮዎች፥ ዋሽንግተን፥ ቤጂንግ፥ ዋሽንግተን ቴሕራኖች፥ ዋሽንግተን ሐቫናዎች፥ አስመራ-አዲስ አበቦች፥ ኢሕአዲግ ተቃዋሚዎች፥ ሶማሌዎች፥ ሶሪያዎች፥ ብዙ ናቸዉ። ቁጥራቸዉን መዘርዘሩ ያታክታልም። ከማንዴላ ምግባር ጥቁቱን፥ ከዴክላክ ድፍረት ትንሹን እንኳን ገቢር አለማድረጋቸዉ በርግጥ ያጠያይቃል 
ማንዴላ ተቀበሩ። ታላቁ የነፃነት፣ የእኩልነት አርበኛ ከሞቱበት እስከ ተቀበሩበት ድፍን ዓለም አዘነ፥ ወይም ማዘኑን ገለፀ። ከቄሱ እስከ ሼኩ፥ ከዘማሪዉ እስከ ዘፋኙ፥ ከተዋኙ እስከ ስፖርተኛዉ ለዚያ ታላቅ-ክቡር ሠዉ ታላቅ አድናቆት፥ አክብሮቱን ሲያንቆረቁር ሰነበተ። ከፕሬዝዳት ዙማ-እስከ ፕሬዝደንት ኦቦባ፥ ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለ ማርያም እስከ ጠቅላይ ሚንስትር ካሜሩን የትንሽ ትልቁ ሀገር መሪ የማንዴላን አብነት ለመከተል፥ ዓላማ፥ ራዕይ አስተምሕሯቸዉን ገቢር ለማድረግ ቃል ገባ። ካንጀት-ይሆን ካንገት ማረጋገጪያዉ-በያኙ በርግጥ ምግባር እና ጊዜ ነዉ። ማንዴላ
ፈጥራ በማንዴላ የተፈጠረችዉ ራስዋ-ደቡብ አፍሪቃ ግን በማንዴላነቷ መቀጠሏ ካሁኑ አያነጋገረ ነዉ። ብልጭ ያሉ፥ እዉነት፥ አስተያየቶቾን እያጠቃቀስን ላፍታ አብረን እንቆዝም።

ባለፈዉ ማክሰኞ፥ ለማንዴላ የሐዘን ስንብት ድግሥ በታደመዉ ሕዝብ መሐል፥ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦቦማ የኩባ አቻቸዉን ራዑል ካስትሮን መጨበጣቸዉ ማንዴላ ሞተዉም ጠላቶችን ያጨባበጡ፥ ጉደኛ ሰዉ አሰኝቶ ነበር። እያሰኘም ነዉ። ይሁንና ኦባማ-ከፖለቲካ መርሕ አብነታቸዉ ከክሊንተን፥ ራዑል ከትግል ጓድ፥ ከስልጣን ርዕዮተ-ዓለም፥ አዉራሻቸዉ፥ ከሁሉም በላይ ከታላቅ ወንድማቸዉ ከፊደል የተለየ ነገር አላደረጉም።

መስከረም 8 ሁለት ሺሕ (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ።) የያኔዎቹ የሁለቱ ሃገራት መሪዎች ቢል ክሊንተን እና ፊደል ካስትሮ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ ላይ ተጨባብጠዉ ነበር። ያኔም እንዳሁኑ በርግጥ ጉድ ተብሎ ነበር። እና አሁን ጉድ ካሰኘ-ጉድ ማሰኘት የነበረ-ያለበት፥ የሚኖርበትም የዓለም አቻ የለሽ ግዙፍ፥ ኃያል፥ ሀብታም ሀገር ከትንሽ፥ ደሀ፥ ደካማይቱ ደሴት ጎረቤቷ ጋር ለስልሳ ዘመናት በጠላትነት መፈላለጓ በሆነ ነበር።

ጉድ ካሰኛ የትልቂቱ ሀገር የመጀመሪያ የጥቁር-ነጭ ክልስ መሪ የማንዴላን አብነት ገቢር ማድረግ እንደማይችሉ ባደባባይ ማመናቸዉ ጉድ ባሰኘ ነበር።


«ኔልሰን ማንዴላን ብጤ ከእንግዲሕ ብጨራሽ አናገኝም። ይሁንና ለአፍሪቃ እና ለመላዉ ዓለም ወጣቶች የሚከተለዉን ልናገር፥-የማንዴላን የሕይወት ምግባር የራሳችሁ ማድረግ ትችላላችሁ። ከሠላሳ ዓመት በፊት ገና ተማሪ እያለሁ ስለማንዴላ እና እዚች ሀገር ስለሚደረገዉ ትግል ተምሬያለሁ። ይሕ በዉስጤ የሆነ ነገር አጭሯል። ለሌሎች እና ለራሴ ኃላፊነት እንዳለብኝ ቀስቅሶኛል። እና ዛሬ ከዚሕ ካደረሰኝ አስቸጋሪ ጉዞ ዶሎኛል። የማዲባን አብነታዊ ምሳሌ ገቢር ለማድረግ ቢያቅተኝም የተሻለ ሠዉ ለመሆን እንድጥር አድርጎኛል።»

ማንዴላ ተወንጅለዉ፥ ታስረዉ፥ የጠላቶቻቸዉን ቋንቋ ተምረዉ፥ ተፈተዉ፥ ለጠላቶቻቸዉ ይቅር ብለዉ ደቡብ አፍሪቃን ዴሞክራሲያዊት ደቡብ አፍሪቃን ፈጥረዉ፣ መርተዉ፣ ኖረዉ ሞቱ። የዓለም ፖለቲከኞች እንዳሉና እንደሚሉት የዓለም የትንሹም የትልቁም አብነት ናቸዉ። በተለይ ለአፍሪቃ -የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር እና የወቅቱ የአፍሪቃ ሕብረት ሊቀመንበር አቶ ኃይለ ማሪያም ደሳለኝ እንዳሉት የወደፊት ተስፋዋም አብነት ናቸዉ።

«እንደ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት እዉነተኛ መሪ እና ልዩ ሰብዕናቸዉ ሁሉ፥ የማንዴላ ሕይወት የክፍለ-አሐጉሪቱን የወደፊት (ተስፋ) የሚወክልም ነዉ።»

ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ከአዲስ አበባ ወደ ቁኑ ከመብረራቸዉ በፊት-አርብ፥ ከዚያዉ ከአዲስ አበባ ይሕን ሰምተን ነበር።

ፍልስጤም-እስራኤሎች፥ ዋሽንግተን፥ ሞስኮዎች፥ ዋሽንግተን፥ ቤጂንግ፥ ዋሽንግተን ቴሕራኖች፥ ዋሽንግተን ሐቫናዎች፥ አስመራ-አዲስ አበቦች፥ ኢሕአዲግ ተቃዋሚዎች፥ ሶማሌዎች፥ ሶሪያዎች፥ ብዙ ናቸዉ። ቁጥራቸዉን መዘርዘሩ ያታክታልም። ከማንዴላ ምግባር ጥቁቱን፥ ከዴክላክ ድፍረት ትንሹን እንኳን ገቢር አለማድረጋቸዉ በርግጥ ያጠያይቃል። አጠያየቀም አላጠያየቀ ኦባማ እንዳሉት ማለትና-ማድረግ ለየቅል፥ አንዳንዴም ተቃራኒ ናቸዉ።

«ስለዚሕ እኛም ለፍትሕ (ሥርፀት)፥ ለሰላም (ፅናት) እርምጃ መዉሰድ አለብን። የማዲባን በዘር መካካል እርቅ የማዉረድ ዉርስ-ቅርስን በደስታ የሚቀበሉ፥ ግን በተቃራኒዉ ሥር የሠደደ ድሕነትን፥የኑሮ ተባለጥ ለመቋቋም፥ መጠነኛ ለዉጥ ማድረግን እንኳን ከልባቸዉ የሚቃወሙ በርካታ ሰዎች አሉ።»

ማንዴላ እራሳቸዉ ደጋግመዉ እንዳሉት ተዓምረኛም፥ ቅዱስም አይደሉም። ብዙዎች እንደመሠከሩት ግን አንድ ሰዉ ሊያደርገዉ ከሚገባዉ በላይ አድርገዉ፥ ዴሞክራሲያዊት ደቡብ አፍሪቃን ፈጥረዉ እንደ አንድ ሰዉ አረፉ፥ አለፉ። የማንዴላ ደቀመዛሙርት፥ የርዕዮተ-ዓለም፥ የሥልጣን ወራሾች እንደተቀረዉ ዓለም መሪዎች ሁሉ የማንዴላን ጅምር ለመቀጠል፥ ራዕይ-አስተምህሯቸዉን ገቢር ለማድረግ ቃል ገብተዋል።

«(ማዲባ) በህይወታችን ከአንድ መሪ የምንፈልገዉና ሊኖረን የሚገባዉ መሪ ሆነህ በአስቸጋሪ ወቅት በመገኘትህ እናመሰግናለን። ለነፃነት የተደረገዉ ረጅም አካላዊ ጉዞ ቢያበቃም፥ የኛ የራሳችን ጉዞ ግን ይቀጥላል። አበክረሕ የጣርክለትን ዓይነት ማሕበረሰብ ለመመሥረት በጀመርከዉ መቀጠል አለብን። ጅምርህን ወደፊት ማራመድ አለብን። ከበለፀገዉ ልዩ ምግባርህና ከሕይወት ልምድህ መማራችንን እንቀጥላለን።»

ፕሬዝደንት ጄኮብ ዙማ። ዕሁድ። የማንዴላዋ ዴሞክራሲያዊት ደቡብ አፍሪቃ በ1994 ስትመሠረት በምጣኔ ሀብት ዕድገት የነበራትን ሥፍራ ዛሬም አለቀቀችም። ከአፍሪቃ አንደኛ ናት። ከአፍሪቃ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ ሃያ-አራት በመቶዉን ትይዛለች። ማንዴላ ሲፈጥሯት ትንሽ የነበረዉ ሙስና ግን ዛሬ ሰንጎ ይዟታል።

የማንዴላን ፅናት፥ ሥልት፥ የአስተዳደር አመራር ብልሐትን ለመቀጠል ቃል የገቡት ፕሬዝደንት ዙማ ራሳቸዉ በመንግሥት ገንዘብ በሃያ-ሁለት ሚሊዮን ዶላር መኖሪያ ቤት ማስገንባታቸዉ በሰፊዉ እየተነገረ ነዉ። ዙማ ቤቱን ከቤተሰባቸዉ በተሰጣቸዉ ገንዘብ ማስገንባታቸዉን መናገራቸዉ አልቀረም። ያመናቸዉ ግን የለም።

ማንዴላ ሁሉንም ዘር ያሳተፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በመሠረቱበት ወቅት የደቡብ አፍሪቃዊዉ ሥራ አጥ ቁጥር አስራ-ስድስት በመቶ ነበር። ዘንድሮ ግን ከአንድ አራተኛ የሚበልጠዉ ደቡብ አፍሪቃዊ ሥራ የለዉም። ሃያ-አምስት ከመቶ። በዚሕ ቁጥር ላይ ሥራ መፈለግ ያቆመዉ ሁለት ሚሊዮን ያህል ሕዝብ ሲጨመርበት የሥራ-አጡ ቁጥር ሠላሳ ሰባት ከመቶ ሊደርስ ይችላል።


የሠራተኞች ተደጋጋሚ የሥራ ማቆም አድማ፥ የባለሥልጣናት ሙስና፥ የግልፅ የምጣኔ ሀብት መርሕ ችግር ከዓለም የምጣኔ ሀብት ክስረት ጋር ተዳምሮ የአፍሪቃዋ የምጣኔ ሀብት ቋት ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገት በእጅጉ እያዘገመ ነዉ። የአብዛኞቹ የአፍሪቃ ሃገራት ምጣኔ ሀብት ከአምስት-እስከ ሰባት ከመቶ በሚያድግበት በዚሕ ዘመን የደቡብ አፍሪቃ አማካይ የምጣኔ ሀብት ዕድገት 3.5 ከመቶ ላይ ያጣጥራል።

ከማንዴላ በፊት የሠላም ኖቤልን የተሸለሙት ቄስ ዴዝሞንድ ቱቱ የማንዴላ ጅምር ዳር እንደሚዘልቅ፥ የሐገራቸዉ የወደፊት ጉዞ እንደሚሰምርም ይናገራሉ።

«አባታችን ሞተ፥ ከእንግዲህ ምን ይገጥመናል? ሞቱ የምፅዓት ቀንን እና ጥፋትን ያስከትልብን ይሆን? አንዳንዶች እሱ አሁን እንዳለፈዉ ካለፈ በኋላ ሀገራችን ትነዳለች ይላሉ። ይሕ እንደሚመስለኝ እኛን ደቡብ አፍሪቃዉያንን አሳንሶ መመልከት ነዉ። የእሱን ቅርስ ማሳነስ ነዉ። ጀምበሯ ነገም ተወጣለች፥ ከነገወዲያ፥ በሚቀጥለዉ ቀንም። እንደ ትናንቱ ደማቅ አትሆን ይሆናል፥ ሕይወት ግን ይቀጥላል።»

እንደመንፈሳዊ አባት መጪዉን ዘመን በበጎ ተስፋ ከመቃኘት፥ ጥሩ ጥሩዉን ከመስበክ ሌላ-ሌላ ማለት በርግጥ የቄስ ምግባር አይደለም። ቱቱ እንዳሉት ሕይወት ደብዛዛም ቢሆን ይቀጥላል። ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከደቡብ አፍሪቃ ጥቁሮች ስልሳ ሁለት በመቶ ለሚሆኑት የነዙማ መንግሥት ፈጣን መፍትሔ ካለመጣላቸዉ ሕይወታቸዉ የሚቀጥለዉ ከድሕነት ጠገግ በታች እየማቀቁ ነዉ።

ፖለቲካዉም ከኤኮኖሚዉ የተለየ አይደለም። ከ1994 ጀምሮ ደቡብ አፍሪቃ ያለ ብዙ ተቀናቃኝ የሚመራዉ የደቡብ አፍሪቃ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት (ኤ.ኤን.ሲ) በመሪዎቹ ሽኩቻ፥ መጠላለፍና ሙስና ግራ ቀኝ እየተላጋ ነዉ። ANC በሁለት ሺሕ አራት በተደረገዉ ምርጫ ሰባ ከመቶ ያህል ድምፅ አግኝቶ ነበር። ከአምስት አመት በሕዋላ በተደረገዉ ምርጫ ግን ANC ያገኘዉ ድምፅ ስልሳ፥ ስድስት ከመቶ እንኳን አይሞላም።

በመጪዉ ዓመትም ምርጫ አለ።2014 እርግጥ ነዉ የዙማ እና የኢምቤኪ (የቀድሞዉ ፕሬዝዳት) ደጋፊ በሚል በሁለት የተከፈሉት የፓርቲዉ አባላት ንትርክ ቀዝቀዝ ያለ መስሏል። ይሁንና ምርጫዉ የሚደረገዉ አድማ በመቱ የማዕድን ቆፋሪዎች ላይ በተፈፀመዉ ግድያ ሰበብ እስካሁን ለኤ.ኤን ሲ ያላሰለሰ ድጋፍ ሲሰጡ የነበሩት የሠራተኞች ማሕበራት መሪዎች ከፓርቲዉ መሪዎች ጋር በሚወዛገቡበት ወቅት ነዉ።

የቀድሞዋ የፀረ-አፓርታይድ እዉቅ ታጋይ ዶክተር ማምፌሌ ራምፌሌ ለረጅም ጊዜ ከሚደግፉት ከኤ.ኤን ሲ አፈንግጠዉ ባለፈዉ የካቲት የራሳቸዉን ፓርቲ መስርተዋል። የኤ.ኤ.ን ሲን የወጣቶች ክንፍ ይመሩ የነበሩት ጁሊየስ ማሌማም ከፓርቲዉ ከተባረሩ በኋላ ባለፈዉ ጥቅምት አዲስ ፓርቲ መስርተዋል።

የአንጋፋዉ ፓርቲ መሰነጣጠቅ ነጮች ለሚበዙበት ለዋነኛዉ ተቃዋሚ ፓርቲ ለዴሞክራቲክ ሕብረት ጥሩ አጋጣሚ ነዉ። እየተራበ፥ እየተቸገረ፥ መሪዎቹ በስሙ በያዙት ሥልጣን እንደሚቀማጠሉ እያወቀ የማንዴላ ሥም፥ ግርማ ሞገስ፥ የገድል-ድላቸዉ ዝና ብቻ ትዕግስት ሆኖት የቆየዉ ሕዝብ እስካሁን በታገሰበት መንገድ መታገሱ አጠራጣሪ ነዉ። እሳቸዉ ደግሞ ይሰጋሉ።ነጭ ናቸዉ።ደቡብ አፍሪቃዊት።

«ያሰጋኛል። ምክንያቱም፥ እንደሚመስለኝ ይህ የአንድ ዘመን ፍፃሜ ነዉ። ነጮች እና ጥቁሮች አብረን የኖርንበት ዘመን ፍፃሜ እንዳይሆን እፈራለሁ። ብዙ መጥፎ ሰዎች እሳቸዉን (ማንዴላን) ስለሚያከብሩ ብቻ መጥፎ ነገር ከማድረግ የታቀቡ ይመስለኛል። እነዚሕ ሰዎች ይህቺን ሀገር ምናልባት ወደ ሌላ አቅጣጫ ይነዷታል ብዬ እሰጋለሁ።»

ሰዉዬዉ፥ በ1962 ከደቡብ አፍሪቃን በሕገ-ወጥ መንገድ በመዉጣት እና የሥራ ማቆም አድማን በማነሳሳት በተከሰሱ ወቅት፥ ከሳሹ አቃቤ ሕግ ፒ.ጄ ቡሽ ይባሉ ነበር። አቃቤ ሕጉ ነጭ እና የነጭ ዘረኞቹ መንግሥት አቀንቃኝ ናቸዉ። ማንዴላ ላይ ሊፈረድ ሲል «አንዴ ለብቻዉ ላነጋግረዉ እፈልጋለሁ» ይላሉ አቃቤ-ሕጉ። ተፈቀደላቸዉ። ማንዴላን ጨበጧቸዉ አሏቸዉም «መልካሙን ሁሉ እመኝልሃለሁ።» ለሳቸዉ የሰላም እረፍት፥ ለናንተ መልካም ጊዜ ልመኝ። እና እንደተለመደዉ ስለ ማሕደረ ዜና አስተያየታችሁን፥ በደብዳቤ፥ በስልክ፥ በኢሜይል፥ በፌስ ቡኩም እንድትሰጡ ጠይቄ ልሰናበት። ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ
Source: www.dw.de
 

በደቡብ ሱዳን ትላንት የተሞከረው የመንግስት ግልበጣ መክሸፉን የኣገርቱ መንግስት ኣስታወቀ። በቀድሞው ም/ፕሬዝደንት ማቻር የተመራው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ የከሸፈው ለፕሬዝደንት ሳልቫኪር ታማኝ የሆኑ ወታደሮች የበላይነትን በማግኘታቸው ነው ተብሏል። 
የቀድሞው የኣገሪቱ ም/ፕሬዝደንት ከስልጣን የተባረሩት ባለፈው ሀምሌ ወር ሲሆን ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደሚሉት ከዚያ ወዲህ በመንግስትም ሆነ በገዚው የSPLM ግንባር መካከል ክፍፍል ተፈጥሯል።
ከእሁድ ቀትር በኃላ ጀምሮ እስከ ዛሬ ማለዳ የዘለቀው የተኩስ ልውውጥ ኣሁን መቆሙን እና በከተማይቱ ጁባ ኣንጻራዊ መረጋጋት መስፈኑን የኣይን እማኞች ይናገራሉ።
በቀድሞው ም/ፕሬዝደንት የሚመሩ ያኮረፉ ወታደሮች እና ፖለቲከኞች በመንግስት ኃይሎች በተለይም በቤተመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ላይ የከፈሩት ድንገተኛ ተኩስ ከየኣቅጣጫው
እያስተጋባ ትላንት ምሽት እና ለሊቱን በሙሉ በከተማይቱ ጁባ የዘለቀ ሲሆን የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን የጠቀሱ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ውጊያው ዛሬ ጧትም በመጠኑ ቀጥሏል። ዓለማውም በዓለማችን የመጨረሻው ዓዲስ መንግስት የሆነውን የደቡብ ሱዳን መንግስት ለመገልበጥ ነው ተብሏል። በኣገሪቱ ጦር ውስጥ የሚገኙ የተወሰኑ የሰራዊቱ ዓባላትም በዋና ከተማይቱ ጁባ የሚገኘውን የመሳሪያ ግ/ቤት ወረው ለመዝረፍ ሞክረው ነበር። የደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ለአሶሺዬትድ ፕሬስ እንደነገሩት ከሆነ ግን ወረራውን በመመከት የመሳሪያ ግ/ቤቱን ለመታደግ ተችሏል። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ እንደሚሉት ኣንዳንድ ፖለቲከኞችም ተይዟል። የመፈንቅለ መንግስት ሙከራውን የመሩት የቀድሞው ም/ፕሬዝደንት ሬክ ማቻር ስለመያዛቸው ግን ማረጋገጥ ኣልቻሉም። የደ/ሱዳን የመ/ሚኒስቴር ቃ/ኣቀባይ ኮ/ል ፊሊፕ ኣጉዬር ዛሬ ረፋዱ ላይ ለዜና ሰዎች እንዳስረዱት ለፕ/ት ሳልቫኪር ታማኝ የሆኑ ወታደሮች በኣሁኑ ሳዓት የጁባ ከተማን ሙሉ በሙሉ ይቆጣጣራሉ።
በቅጡ የታጠቁ እና መትረየስ በተገጠመባቸው ተሽከርካሪዎች የታገዙ በርካታ ወታደሮች በጁባ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ለቁጥጥር ተሰማርተው እንደሚንቀሳቀሱ የገለጹት የዓይን እማኞችም ከወታደሮች በስተቀር ዛሬ ጎዳናዎች ላይ የሚታይ ሰላማዊ ሰው ኣለመኖሩን ለዜና ሰዎች ኣስረድቷል። የግብጽ አየር መንግድም የጁባ ኣውሮፕላን ማረፊያ በመዘጋቱ ዛሬ ወደዚያው ያደርገው የነበረውን በረራ ለመሰረዝ መገደዱን ኣስታውቐል። በዚያ የሚገኘው የተመድ ሰላም ኣስከባሪ ጦር በበኩሉ በከተማይቱ በተጋጋለው የከባድ መሳሪያ ተኩስ ልውውጥ የተነሳ በተጠንቀቅ መሆኑን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰዎችም ወደ ካምፓቸው እየሸሹ መሆናቸውን ኣስታውቐል። በኣዲሲቷ የዓለማችን ኣገር ደ/ሱዳን መንግስት ውስጥ ልዩነት እና ፍጥጫ የነገሰው ፕ/ት ሳልቫኪር ባለፈው ሀምሌ ወር ምክትላቸውን ማቻርን ከስልጣን ማባረራቸውን ተከትሎ ነው። ከሁለት ዓመታት በኃላ በ2015 በዚያች ኣገር በሚካሄደው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ የሳልቫኪር ብርቱ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት የቀድሞው ም/ፕ/ት ማቻር ከስልጣን እንደተባረሩ በሰጡት መግለጫ ኣገሪቱ ኣንድ ሆና እንድትቀጥል ከተፈለገ የኣንድ ሰው ኣገዛዝ ማክተም ኣለበት። ኣንባገነናዊ ኣገዛዝን መታገስ የለብንም ብለውም ነበር። የማቻር መባረር ከመንግስት ም/ቤትም ኣልፎ በገዢው ፓርቲ ውስጥም ክፍፍል መፍጠሩን የተረዱት የUS አሜሪካ እና የኣውሮፓ ህብረት ዲፕሎማቶች ውጥረቱ ወደ እርስ በእርስ ግጭት እንዳያመራ ስጋታቸውን ገልጸው ነበር።
ሳልቫኪር የቀድሞው ሸማቂ እና የኣሁኑ ገዢ ፓርቲ SPLM የወታደራዊ ክንፍ መሪ በነበሩበት ወቅት ማቻርን ጨምሮ ኣሁን ከእሳቸው ጋር የተባረሩት የግንባሩ አባላት ለአስርተ ዓመታት ከሱዳን መንግስት ጋር በተካሄደው ውጊያ ወቅት በከፍተኛ የዓመራር እርከን ላይ የነበሩ ናቸው። ዘ ሱዳን ትሪብዩት የተሰኘው ጋዜጣ እንደዘገበው ከሆነ ግጭቱ የተጀመረው፣ ትላንት እሁድ መሆኑ ነው፣ ከፕ/ት ሳልቫኪር የዲንካ ጎሳ የሆኑ ወታደሮችን ለማጥቃት በተንቀሳቀሱ ከኑዌር ጎሳ የሆኑ የማቻር ታማኝ ኃይሎች መካከል ነበር። ጁባ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲም ዜጎቹ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኣሳስቧል። የተመድ የደ/ሱዳን ልዩ መልዕክተኛም ውጥረቱ ኣሁንም ድረስ ኣለመቀረፉን ጠቅሰው ሁለቱም ወገኖች በኣስቸኩዋይ ተኩስ ኣቁመው ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲያፈለልጉ ጥሪ ኣድርገዋል።
ጃፈር ዓሊ
ሸዋዬ ለገሰ
Source: www.dw.de


የነፃነት እና የፀረ-ዘረኝነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ ስርዓተ ቀብር እሁድ ታኅሣሥ 6 ቀን 2006 ዓም ደቡብ አፍሪቃ ኩኑ በተባለችው የትውልድ መንደራቸው ተካሄደ። ለማንዴላ ክብር በቀብር ስርዓቱ 21 ጊዜ መድፍ የተተኮሰ ሲሆን፤ የጦር ጀቶች ከዕድምተኛው በላይ ሲያንዣብቡም ታይተዋል።
  ከእንስሳት ቆዳ የተሰፉ ባሕላዊ ልብሶችን የለበሱ ሀዘንተኞች ለማንዴላ ውዳሴ አሰምተዋል። የደቡብ አፍሪቃ አፓርታይድ ስርዓት ከተገረሰሰ በኋላ የሀገሪቱ የመጀመሪያው በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጡት ኔልሰን ማንዴላ ግብዓተ መሬት የተፈፀመው በምሥራቃዊ ደቡብ አፍሪቃ በምትገኘው ኩኑ በተሰኘችው ገጠራማ መንደር ውስጥ ነው። በቀብር ስርኦቱ ላይ በበርካታ መቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደተገኙ የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። ቀደም ብሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳሚዎች በማንዴላ ቅፅር
ውስጥ በተዘጋጀው ሰፊ ድንኳን በመገኘት ለነፃነት ታጋዩ ውዳሴ በማሰማት የጭፈራ ትርዒት አሳይተዋል። ኔልሰን ማንዴላ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ሐሙስ፣ ኅዳር 26 ቀን 2006 ዓም ማረፋቸው ይታወሳል።
ገና ከማለዳው ነበር መላ የኩኑ ነዋሪዎች ማለት በሚቻል ሁኔታ ሕዝቡ በአጠቃላይ ወደ አደባባይ የወጣው። የመጀመሪያዎቹ ወደ 5000 የሚጠጉት የቀብር ታዳሚዎች የማንዴላ ስርዓተ-ቀብር ላይ ለመሳተፍ ተሰባስበዋል። ሞተረኛ ፖሊሶችም የውጭ ሃገራት መሪዎችን በማጀብ አውራ ጎዳናዎቹ ላይ በመመላለስ ተጠምደዋል። በማንዴላ የትውልድ መንደር ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ሰዎችም ከጎዳናዎቹ ራቅ እንዲሉ ፖሊሶች ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል።
ለዓለም ማኅበረሰብ ስርዓቱን ለመዘገብ በቀብር ስርዓቱ ላይ ወደ 2000 የሚጠጉ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችም መታደማቸው ታውቋል። የቀብር ስርዓቱ ለበርካታ ታዳሚዎች እጅግ ስሜታዊ እንደነበረም ተዘግቧል። የቀብር ስርዓቱ ወደ አራት ሠዓት ገደማ መዝለቁም ተጠቅሷል።
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ልደት አበበ
Source: www.dw.de


| Copyright © 2013 Lomiy Blog