በዓባይ ጉዳይ የግብፅ መንግሥት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም አዘዘ

By: Ethiopian Reporter
 ሱዳን በቅርቡ ከግብፅ ጐራ ልታፈነግጥ ትችላለች
በዘካሪያስ ስንታየሁ
አዲሱ የግብፅ መንግሥት በዓባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊነሳ በሚችል ግጭት ምክንያት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም ቢያዝም፣ የግብፅ የጦርነት እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሱዳን ጠረፍ 40 ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገባ ብላ በምትገኘውና ቡምባዲ በምትባለው አካባቢ 5,250 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለውን ታላቁ የሚሌኒየም ግድብ ፕሮጀክት ይፋ ካደረገች በኋላ፣ ግብፅ የተለያዩ ጫናዎችን በኢትዮጵያ ላይ ለማሳደር እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡ ግብፅም በዚህ ግድብ ምክንያት የዓባይ የውኃ መጠን ሊቀንስ ይችላል የሚል ስጋት ስላላት፣ የዲፕሎማሲ ጫና ከማድረጓ በተጨማሪ የጦር ሠራዊቷን በተጠንቀቅ እንዲቆም እስከማዘዝ ደርሳለች፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
ግን ይህ እንቅስቃሴ ግብፆች የውስጥ ችግራቸውን ትኩረት ለማስለወጥ ከመሆኑ በተጨማሪ የድርድር ስትራቴጂ ነው ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ያላት ሚና ከፍተኛ በሆነበት በዚህ ወቅት በእሷ ላይ ጦርነት ማወጅ የማይታሰብ ነው፤›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ግብፆች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ ጳውሎስ ጋር ለመነጋገር የራሳቸውን ልዑክ እንልካለን እያሉ መሆናቸውን አምባሳደር ዲና ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ መንግሥት ከአፍሪካ ዲፕሎማሲ ርቆ ነበር፡፡ ስለሆነም አዲሱ የግብፅ መንግሥት ወደ አፍሪካ ዲፕሎማሲ መቀላቀል ከፈለገ የትብብር ማዕቀፉን የፈረሙ አገሮችን መቃረን እንደሌለበት አምባሳደር ዲና አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነቱን ሱዳን በቅርብ ጊዜ ትፈርማለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ሱዳኖች ለጊዜው ግብፅ ችግር እንዳትፈጥርባቸው ጉዳዩን በሚስጥር እንደያዙት ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተያያዘ ዜና ባለፈው ሰኞ ወደ ኡጋንዳ ኢንቴቤ የተጓዘው የግብፅ የልዑካን ቡድን ከፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር የተወያየ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ ኡጋንዳ በተፋሰስ አገሮቹ አማካይነት የተመሠረተውን ተቋም የማፍረስ ምንም አቋም እንደሌላት አስረድተዋል፡፡ ሆኖም ግብፅ ውስጥ የተከሰተው አለመረጋጋት እስኪረጋጋ ድረስ ኡጋንዳ ስምምነቱን እንደማታፀድቀውና ግብፅን ልትጠብቃት እንደምትችል፣ ሙሴቪኒ በቀድሞ የግብፅ ፕሬዚዳንት ጋማል አብደል ናስር ልጅ ለሚመራው የግብፅ ልዑካን ቡድን ገልጸዋል፡፡

አምባሳደር ዲና እንዳሉት፣ ‹‹ኡጋንዳዎች በመጀመሪያም ወደ ስምምነቱ ሲገቡ ጥቅማቸውን አይተው ስለሆነ ወደኋላ ይመለሳሉ ብለን አናምንም፡፡›› ኡጋንዳዎች ይህን ያሉት ምክንያታዊ ለመሆን ይሆናል ያሉት አምባሳደር ዲና፣ በማናቸውም ሁኔታ በኡጋንዳ በኩል ያለውን ቁርጠኝነት አንጠራጠርም ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ወደ ኡጋንዳ ካመራው የግብፅ ልዑክ ውስጥ ለፕሬዚዳንትነት የሚወዳደሩ ሦስት ግለሰቦች በመኖራቸው ይህን ጉዳይ ለምርጫ መቀስቀሻነት ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡ የጦርነት እንቅስቃሴውም ቢሆን በዓባይ ላይ በፕሮፓጋንዳ ድምፅ ማግኘት ስለሚፈልጉ እንጂ ዘላቂ ነገር አይደለም ብለዋል፡፡
- ሱዳን በቅርቡ ከግብፅ ጐራ ልታፈነግጥ ትችላለች
በዘካሪያስ ስንታየሁ
አዲሱ የግብፅ መንግሥት በዓባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊነሳ በሚችል ግጭት ምክንያት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም ቢያዝም፣ የግብፅ የጦርነት እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሱዳን ጠረፍ 40 ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገባ ብላ በምትገኘውና ቡምባዲ በምትባለው አካባቢ 5,250 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለውን ታላቁ የሚሌኒየም ግድብ ፕሮጀክት ይፋ ካደረገች በኋላ፣ ግብፅ የተለያዩ ጫናዎችን በኢትዮጵያ ላይ ለማሳደር እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡ ግብፅም በዚህ ግድብ ምክንያት የዓባይ የውኃ መጠን ሊቀንስ ይችላል የሚል ስጋት ስላላት፣ የዲፕሎማሲ ጫና ከማድረጓ በተጨማሪ የጦር ሠራዊቷን በተጠንቀቅ እንዲቆም እስከማዘዝ ደርሳለች፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ግን ይህ እንቅስቃሴ ግብፆች የውስጥ ችግራቸውን ትኩረት ለማስለወጥ ከመሆኑ በተጨማሪ የድርድር ስትራቴጂ ነው ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ ያላት ሚና ከፍተኛ በሆነበት በዚህ ወቅት በእሷ ላይ ጦርነት ማወጅ የማይታሰብ ነው፤›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ግብፆች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ ጳውሎስ ጋር ለመነጋገር የራሳቸውን ልዑክ እንልካለን እያሉ መሆናቸውን አምባሳደር ዲና ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ መንግሥት ከአፍሪካ ዲፕሎማሲ ርቆ ነበር፡፡ ስለሆነም አዲሱ የግብፅ መንግሥት ወደ አፍሪካ ዲፕሎማሲ መቀላቀል ከፈለገ የትብብር ማዕቀፉን የፈረሙ አገሮችን መቃረን እንደሌለበት አምባሳደር ዲና አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነቱን ሱዳን በቅርብ ጊዜ ትፈርማለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ሱዳኖች ለጊዜው ግብፅ ችግር እንዳትፈጥርባቸው ጉዳዩን በሚስጥር እንደያዙት ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተያያዘ ዜና ባለፈው ሰኞ ወደ ኡጋንዳ ኢንቴቤ የተጓዘው የግብፅ የልዑካን ቡድን ከፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር የተወያየ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ ኡጋንዳ በተፋሰስ አገሮቹ አማካይነት የተመሠረተውን ተቋም የማፍረስ ምንም አቋም እንደሌላት አስረድተዋል፡፡ ሆኖም ግብፅ ውስጥ የተከሰተው አለመረጋጋት እስኪረጋጋ ድረስ ኡጋንዳ ስምምነቱን እንደማታፀድቀውና ግብፅን ልትጠብቃት እንደምትችል፣ ሙሴቪኒ በቀድሞ የግብፅ ፕሬዚዳንት ጋማል አብደል ናስር ልጅ ለሚመራው የግብፅ ልዑካን ቡድን ገልጸዋል፡፡

አምባሳደር ዲና እንዳሉት፣ ‹‹ኡጋንዳዎች በመጀመሪያም ወደ ስምምነቱ ሲገቡ ጥቅማቸውን አይተው ስለሆነ ወደኋላ ይመለሳሉ ብለን አናምንም፡፡›› ኡጋንዳዎች ይህን ያሉት ምክንያታዊ ለመሆን ይሆናል ያሉት አምባሳደር ዲና፣ በማናቸውም ሁኔታ በኡጋንዳ በኩል ያለውን ቁርጠኝነት አንጠራጠርም ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ወደ ኡጋንዳ ካመራው የግብፅ ልዑክ ውስጥ ለፕሬዚዳንትነት የሚወዳደሩ ሦስት ግለሰቦች በመኖራቸው ይህን ጉዳይ ለምርጫ መቀስቀሻነት ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡ የጦርነት እንቅስቃሴውም ቢሆን በዓባይ ላይ በፕሮፓጋንዳ ድምፅ ማግኘት ስለሚፈልጉ እንጂ ዘላቂ ነገር አይደለም ብለዋል፡፡

No comments:

| Copyright © 2013 Lomiy Blog