የፓን አፍሪካኒዝም ራዕይ ጭንገፋ!


              ክፍልአንድ 
W. E. B. Du Bois
 ምዕራባዊያንአፍሪካን በበጎ ነገርአያነሷትም፡፡ የቀደምት ስልጣኔዋንምአምነው አይቀበሉትም፡፡ አፍሪካዊያኑምቢሆኑ ስለማንነታቸውና ስለታሪካቸው ያላቸውእውቀት ፈረንጆች አፍሪካንከሚያውቋት እጅግ ያነሰነው፡፡ ይህ ነገርደግሞ አሁን አፍሪካ ካለባት ችግርበተጨማሪ ነገሩ የገለባእሳት ሆኖባታል፡፡ አፍሪካ ባንድወቅት ኃያል ሃገር ነበረች፡፡ ነገር ግን ስልጣኔዋ ተሸመደመደና ወደጨለማው ዘመን ገባች፡፡የስልጣኔ መሽመድመድ በታሪክአፍሪካ ብቻ ሳትሆንአውሮፓንም ደቁሷታል፡፡ ምስጋናይግባቸውና የሰሜን አፍሪካሙሮች (Moors) በሰባተኛውመቶ ክፍለ ዘመን ወደ አውሮፓ ተሻግረው፣ ጨለማውስጥ የምትገኘውን አህጉር አቀኑ፡፡ከዚያ በኋላ አውሮፓ ሰለጠነችና አፍሪካንተቀራመተች፡፡ ይህንን የአፍሪካቅርምጥ የአብርሆት (Enlightenment) ዘመንልሂቃን የሚባሉት ጭምርደግፈውታል፡፡ የአፍሪካ ህዝብሰብአዊ መብቱ ተገፎሰው ያለመሆኑ ታወጀ እናለባርነት ተጋዘ፣ ተገረፈ፣ተሰቃየ፣ ተሰቀለ፣ ታደነ፣ታነቀ፣ ተገደለ፣ ንብረቱተዘረፈ፣ የአገር ባለቤትነቱንተነጠቀ፣ ሳይፈልግ የወራሪዎቹንባህል፣ ትምህርት፣ ኃይማኖትእንዲቀበል ተገደደ ………. ምንያልሆነው አለ? እናምይሄንን ግፍ አሽቀንጥረውለመጣል ሃሳብ ያላቸውጥቁር ልሂቃን በየቦታው ማኮብኮብጀመሩ፡፡ በመጀመሪያ ሰለእነዚህን ንቅናቄዎች እናኢትዮጵያኒዝም ትንሽ እንመለከታለን፡፡ከዚያም ወደ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ እናዓላማ፣ በመጨረሻም የፓንአፍሪካኒዝም ራዕይ እንዴትበአፍሪካዊያን አምባገነን መሪዎችእንደጨነገፈ
በሶስት ተከታታይክፍሎች እንመለከታለን፡፡ 19ኛውክፍለ ዘመን መጨረሻ በደቡብ አፍሪካበነጮች ይጨቆኑ የነበሩትእና በእምነቱ ውስጥ ምንምቦታ ያልተሰጣቸው ጥቁሮች ከአንግሊካንእና ሜቶዲስት ደብር (Church) ተገንጥለውበውጣት ኢትዮጵያዊ ደብር(Ethiopian Church) መሰረቱ፡፡ በሰበካቸው ውስጥምአፍሪካ ለአፍሪካዊያንየሚልነበረው፡፡ ይህም እንቅስቃሴኢትዮጵያኒዝም የሚባልአስተሳሰብ እንዲጀመር ረድቷል፡፡የዌስልያን ሚኒስተር ማንጌናሞኮን (Mangena Mokone) ኢትዮጵያኒዝም የሚለውንቃል ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተጠቀመብዙዎች ያምናሉ፡፡ የኢትዮጵያኒዝምእሳቤ ወደ ምዕራብ አፍሪካ ሀገራትናይጄሪያ፣ ጋና፣ ካሜሮን፣ሮዶዥያና ሌሎችም አንሰራርቶነበር፡፡ ከአፍሪካ ውጭደግሞ ይህ እሳቤ በካረቢያን እና ሰሜንአሜሪካ እንደሰደድ እሳትተስፋፍቶ ነበር፡፡ አንዳንድጸሐፍት ኢትዮጵያኒዝም የሚለውንጽንሰ ሃሳብ ለማብራራት እንደሚያስቸግር ቢያትቱምዋና ጽንሰ ሃሳቡ ኃይማኖታዊና ፖለቲካዊ ፍልስፍናንያካተተ ነው፡፡ በሃይማኖታዊውካየነው ጥቁሮች በነጮችየበላይነት የሚመራውን ደብርትተን፣ የራሳችንን ከማንነታችንጋር ትስስር ያላትን አፍሪካዊት(ኢትዮጵያዊት) ደብር እንመስርትየሚል ነው፡፡ ፖለቲካዊው ደግሞበአለም የሚገኙ ጥቁሮችየነጮችን የፈላጭ ቆራጭገዥነትን ለመገርሰስ ኢትዮጵያንእንደ አርዓያ በመውሰድ የሚደረግእንቅስቃሴ ነበር፡፡ በተለይየአድዋ ድል፣ የኢትዮጵያቀደምትነት ስልጣኔ እናበመጽሐፍ ቅዱስ ስሟመጠቀሱ ለኢትዮጵያኒዝም እሳቤእና ለፓን አፍሪካኒዝም ፍልስፍና ጉልህአስተዋጽኦ ነበራቸው፡

 ፓን አፍሪካኒዝም- በመላውዓለም የሚገኙትን አፍሪካዊያን አንድነት(ሶሊዳሪቲ) የሚቀሰቅስ ርዕዮተዓለምነው፡፡ ፓን አፍሪካኒዝምመነሻውን ከጥንት የአፍሪካዊያንስልጣኔ ጋር ያይዛል፡፡ጥቁሮች ከጥንት ጀምረውእስካሁን ይዘውት የመጡትንናጥንት የነበሩትን ታሪካዊ፣ ባሕላዊ፣ኪነ-ጥበባዊ፣ መንፈሳዊ፣ ሳይንሳዊናፍልስፍናዊ እሴቶችን በሕዝብዘንድ ማስረጽ አንደኛው ዓላማቸውነው፡፡ የፓን አፍሪካኒዝምንቅናቄዎች ቀደም ሲልየተጀመሩ ቢሆንም ዘመናዊውየፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ የተጀመረውግን 1887 በትሪኒዳዱ የህግምሁር ሄነሪ ሲልቬስተር ዊሊያምስ አፍሪካንአሶሴሽንበሚል ስያሜነበር የተቋቋመው፡፡ እዚህ ላይ(ስለ መጀመሪያው የፓን አፍሪካንመስራች) በታሪክ ሰዎችዘንድ ልዩነት አለ፡፡ አንዳንድየታሪክ መጽሐፍት ላይ(ጸሐፊዎች) የመጀመሪያው የፓንአፍሪካን መስራች (ጽንሰሃሳብ አመንጭ) ላይቤሪያዊው መምህር፣ጸሐፊ፣ ዲፕሎማትና ፖለቲከኛኤድዋርድ ዊልሞት ብላይደንነው ሲሉ ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ፡፡ ሌሎችደግሞ ሄነሪ ሲልቬስተር ዊሊያምስ ነውይላሉ፡፡ በአፍሪካም ይህንየፓን አፍሪካኒዝም አስተሳሰብ ካስፋፉትናድርጅታዊ መሰረት ከሰጡትአንዱ የማላዊው ዜጋ የነበረውየባብቲስት ሚሲዮናዊ ዮሴፍቡዝ ነበር፡፡ 
የፓን አፍሪካንየመጀመሪያውን ጉባኤም በሐምሌወር 1900 ለንደን ላይበሄነሪ ሲልቬስተር ዊሊያምስአስተባባሪነት ከአፍሪካ፣ ከዩናትድስቴትስ፣ ከካረቢያን እናከአውሮፓ ሃገራት በተውጣጡ32 ተወካዮች ተካሄደ፡፡ በዚህስብሰባ ላይ ከአፍሪካየጋና (ጎልድ ኮሰት) ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ እናኢትዮጵያ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡የኢትዮጵያው ንጉሰ ነገሰትዳግማዊ ምኒሊክ የሃይቲውንቤኒቶ ሲልቪያን ወክለው ልከውነበር፡፡ በዚሁ ስብሰባፓን አፍሪካን አሶሴሽንየሚል ድርጅትም አቋቋሙ፡፡ ከተሰብሳቢዎቹአንዱ ታዋቂው አፍሮ አሜሪካዊውምሁር ዱቦይስ ( ) ተገኝቷል፡፡  ዱቦይስ ከሃርቫርድዩኒቨርስቲ በማህበራዊ ጥናትዶክትሬቱን ያገኜ ሲሆንበአሜሪካም በጥቁሮች ታሪክየመጀመሪያ ጥቁር ሰውነው ደኮትሬት በማግኜት፡፡ በአትላንታዩኒቨርስቲም የታሪክ፣ ማህበራዊሳይንስ (ሶሲዎሎጅ) እናምጣኔ ሃብት ፕሮፌሰር ነበር፡፡ ዱቦይስየአሜሪካን ጥቁሮች በማንቃትበኩል ያደረገው ትግል እጅግከፍተኛ ነበር፡፡ ብዙመጽሐፍትን ጽፏል፡፡ ታላቅስራው (Magnum Opus) ተደርጎ የሚወሰደውBlack reconstruction in America ሲሆን ሌላውተወዳጅ ስራው ደግሞThe Souls of Black Folk ነው፡፡ National Association for the Advancement of Colored People (NAACP) መስራችሲሆን የዚሁ ድርጅት ልሳን ለሆነውThe Crisis ዋና ኤዲተር ነበር፡፡ ፓንአፍሪካን ከመሰረቱት መካከልግንባር ቀደሙ ነው፡፡ 

1913 የኢትዮጵያኮኮብ (The star of Ethiopia) የሚል ተውኔትደርሶ ለህዝብ እንዲታይ አድርጓል፡፡በተጨማሪም ኢትዮጵያን የሰውልጆች ሁሉ እናት(መፈጠሪያ)ብሎ ይጠራትእና ያስተምር ነበር፡፡ የዓለምስልጣኔ ሁሉ ከናይልሸለቆ (ግብጽና ኢትዮጵያ) እንደተጀመረምያቀነቅን ነበር፡፡ የፓንአፍሪካን እንቅስቃሴም ለግማሽምዕተ ዓመት ያህል መርቷል፡፡ ከለንደኑ ስብሰባበኋላ አራት የፓን አፍሪካን ስብሰባዎች (1919 ፓሪስ፣ 1921 ሎንዶንናብራሰልስ፣ 1923 ሎንዶንናሊዝበን፣ 1927 ኒውዮርክ) የተዘጋጁት በዚህ ምሁርመሪነት ነበር፡፡ ያለዱቦይስ አሰተዋጽኦ ፓንአፍሪካኒዝም ወይም በተዘዋዋሪየአሁኑ አፍሪካ ሕብረትምን አልባትም ላይኖር ይችላል፡፡የሚገርመው የኢትዮጵያና የአፍሪካዋያንብዙ መገናኛ ብዙሓን ስለዚህጎምቱ የጥቁር ምሁርና የፓንአፍሪካን አባት ሚናሲናገሩ፣ ሲጽፉ ወይምሲዘክሩ አይታይም፡፡ ዱቦይስእና ኩዋሜ ንኩርማህ በፓን አፍሪካንምስረታ ጉዳይ የሚነጻጸሩአይደሉም፡፡ ርቀታቸው የሰማይናየምድር ነው ብሎየዚህ ጦማር ጸሀፊ ያምናል፡፡ ንኩርማህ፣ጁሊየስ ኒሬሬ፣ጆሞ ኬንያታ ወዘተ. 1945የማንቸስተሩ ፓን አፍሪካንስብሰባ ላይ የተገኙየርዕዮቱ ልጆቹ ናቸው፡፡በርግጥ ከማንቸስተሩ የፓንአፍሪካን ስብሰባ በኋላመሪነቱ በአፍሪካዊያን እጅገብቷል፡፡ ዱቦይስ በሶሻሊዝምፍቅር ጋር እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ የወደቀነበር፡፡ የሶሻሊዝም ፍልስፍናውእንዳልገባው ቢናገሩም እሱግን ካፒታሊዝም የሰው ልጆችዘረኛ እንዲሆኑ አድርጓል ይላል፡፡እንም ዘረኝነትን ለማስቀረት ሶሻሊዝምፍቱን መፍትሔ ነው ብሎያምናል፡፡ በዚህ ምክንያትምአሜሪካ አንቅራ ነበርየምትጠላው፡፡ 1957 ጋናነጻነቷን ስታገኝ የክብርእንግዳ አድርጋ ጠራችው፡፡ነገር ግን አሜሪካ ጋና አትሄዳትምአለችና ፓስፖርቱን ቀማችው፡፡ነገር ግን 1960 ፓስፖርቱን ስላገኜወደ ጋና ሄደ፡፡ እናም ለጋናየሪፓብሊክ ምስረታ በዓልላይ ተገኘ፡፡ በዚሁ ሰዓትምከንኩርማህ ጋር ኢንሳክሎፒዲያአፍሪካን ለማዘጋጀት ተስማሙ፡፡በጀቱም በጋናዊያን መንግስትነበር የሚሸፈነው፡፡ እናም 1961 ከአሜሪካ ሚስቱን ይዞበመምጣት ጋና ከተመ፡፡የኢንሳክሎፒዲያውን ስራም ጀመረ፡፡1963 አሜሪካ ፓስፖርቱንለማደስ ፈቃደኛ ስላልሆነችየክብር እንግዳ ሆኖጋና ተቀመጠ፡፡ ነገር በዚያውዓመት በነሃሴ ወር 1963 አክራውስጥ ሕይወቱ አለፈች፡፡ የተቀበረበትቦታም የዱቦይስ መታሰቢያ ማዕከልተብሎ ተሰይሟል፡፡

ሌላው ፓንአፍሪካን ሲነሳ ከመስራቾቹግንባር ቀደም የሆነውናአነጋጋሪው ማርቆስ ጋርቬይንእናገኛለን፡፡ አንዳንዶች ጋርቬይንየጥቁሮች ሙሴ እያሉይጠሩታል፡፡ ሙሴ እስራኤላዊያንንከግብጽ ባርነት አላቆወደ ተስፋይቱ ምድር በመውሰድነጻ እንዳወጣቸው ሁሉ፣ ጋርቬይምጥቁሮቹን ከጭቆናና ከባርነትአላቆ ወደ ተስፋይቱ ምድር አፍሪካለመውሰድ እና ጥቁሮችንአንድ ለማድረግ (ለማስተሳሰር) ያደረገውተጋድሎ ግሩም ነበር፡፡ፍልስፍናውም ጋርቬይዝም ይባልነበር፡፡ ጋርቬይ ዓለምአቀፍ የጥቁሮች መሻሻል ማህበር፣አፍሪካን ኮሚኒቲስ ሊግ፣ብላክ ስታር ላይን ኮርፖሬሽን የሚባሉ ድርጅቶችንአቋቁሟል፡፡ ጋርቬይ የጥቁርአሜሪካዊያን ድርጅት በሆነውኔሽን ኦቭ-ኢዝላም ያለው ክብርበጣም የገዘፈ እና እንደነብይምየሚመለከቱት ነው፡፡ በራስተፈሪያን እምነትም ከንጉስኃይለሥላሴ ቀጥሎ እንደአምላክ (ነብይ) የሚቆጠርሰው ነው፡፡ ነገር ግንእዚህ ላይ አንድ ማንሳት ያለብን ተቃራኒጉዳይ አለ፡፡ ጣሊያን ኢትዮጵያንስትወር፣ ንጉስ ኃይለስላሴ ወደ እንግሊዝ የመሄዳቸውን ጉዳይጋርቬይ እንዲህ በቀላሉአላለፈውም፡፡ ንጉስ ቀዳማዊኃይለ ሥላሴን በአደባባይ ለስጋቸውሳስተው፣ ወገናቸውን ጦርነትውስጥ ማግደው አውሮፓ እጃቸውንሊሰጡ መጡ ብሎ ከመሳለቁም በላይ ቦቅቧቃናፈሪ ብሎ ሰደባቸው፡፡ ስለዚህ ጉዳይበዝርዝር ሌላ ጊዜይዘን እንመጣለን፡፡ 

ጋርቬይ ነጮችንስግብግቦች፣ ራስ ወዳዶችእና ፍቅር የለሾች ሲል በተለያየጊዜ ይገልጻቸው ነበር፡፡ ፍቅር፣መተሳሰብና ለጋስነት ምንጩአፍሪካ ግብጽና ኢትዮጵያእንደሆነ ይሰብክ ነበር፡፡በአሜሪካም በየጎዳነው እናንተየሃያላን ልጆች ሆይአትነሱም ወይ እያለመሳጭ ንግግር ያደርግ ነበር፡፡የሚገርመው ይህ ጥቁሮችንበመላው ዓለም ያንቀሳቀሰናያነቃው ሰው (ጋርቬይ) ከዱቦይስ ጋር  የከረረጠብ ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ ዱቦይስበመጀመሪያ ብላክ ስታርላይን የተሰኘውን የመርከብ ንግድእቅድ (በማርከስ ጋርቬይ የተነደፈውን) ደግፎት ነበር፡፡ ጋርቬይጥቁሮች በሙሉ ወደአፍሪካ ይመለሱ፣ በአፍሪካአሜሪካዊያንም ይመሩ (ይስተዳደሩ) ሲል፣ ዱቦይስ ደግሞ ወደአፍሪካ እንመለስ የምትለውንሃሳብ እደግፈዋለሁ፡፡ ነገር ግንአፍሪካ በአፍሮ አሜሪካዊያንይመሩ የምትለው ነገር ፈጽሞየማይሆን ነው በማለትይቃወመዋል፡፡  በዚህ ሁለትጽንፍ ሃሳብ ባለመስማማት ባደባባይ እስከመሰዳደብ ደርሰዋል፡፡ ዱቦይስጋርቬይን በአሜሪካና በመላውዓለም ለሚኖሩ ጥቁሮች አደገኛጠላት ብሎ ከመፈረጁም በላይ ይሄሰው ከሃዲ ወይም እብድ መሆን አለበት ሲል ወርፎታል፡፡ጋርቬይ ደግሞ ዱቦይስንአንተ እኮ ነጭ እና የጥቁር ዲቃላ በተጨማሪምየነጭ ኔግሮ (White men’s nigger) ነህ’’ ይለውነበር፡፡ ከዚህ ሌላጋርቬይ ብላክ ስታርላይን የሚባለውን ድርጁቱን ለማጥፋትአሻጥር እየሰራብኝ ነውበማለት ይወቅሰው ነበር፡፡

ሌላው ለፓንአፍሪካኒዝም ድርጅት ምስረታትልቅ አስተዋጽኦ ካደረጉት መካከልኢትዮጵያዊውን . ራስመኮነን እናገኛለን፡፡ መኮነንየተወለደው ጉያና (Guyana) ውስጥሲሆን አያቱ ከሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይበአንድ ስኮትላዳዊ የማዕድንሰራተኛ ነበር የተወሰደው፡፡ስሙን የቀየረው (. ራስመኮነን የተባለው) በሁለተኛውየጣሊያን ኢትዮጵያን ወረራጊዜ ነበር፡፡ ለምን ስሙንቀየረ ካላችሁ፣ አፍሪካዊ ዝርያእንዳለው ለማመልከት ነበር፡፡አሜሪካ ኮርኔል ዩኒቨርስቲከተማረ በኋላ ያቀናውወደ ዴንማርክ-አውሮፓ ነበር፡፡ያኔ ታዲያ ኮፐንሃገን-ዴንማርክ ውስጥየእርሻ ኮሌጅ ውስጥእየተማረ እያለ ዴንማርክለጣሊያን የኢትዮጵያን ንጹሃንሕዝቦች መግደያ የሚሆንጅምላ ጨራሽ መርዝ አምርታ ትሰጣት ነበር፡፡ይህንን ድርጊት ጋዜጦችላይ ጦማር በመጻፍ በግልጽ ተቃወመ፡፡18 ወር ከተቀመጠባት ዴንማርክም ተባረረ፡፡ከዚያ ወደ እንግሊዝ ተጓዘና በእነጆርጅ ፓድሞር በተመሰረተው ኢንተርናሽናልአፍሪካን ሰርቪስ ቢሮንቁ ተሳታፊ በመሆንና የቢሮውምየቢዝነስ ማናጄር በመሆንአገልግሏል፡፡ ከሁለተኛው የዓለምጦርነት በኋላ ግንወደ ማንቸስተር ዩኒቨርስቲ በማቅናትታሪክ አጠና፡፡ በእንግሊዝም የስራፈጣሪ በሆን ብዙ ሆቴሎችን ከፈተ፡፡ ከጆርጅፓድሞር እና ኩዋሜንኩርማህ ጋር በመሆንም1945ቱን የፓንአፍሪካን ኮንግረስ ለማደራጄትብዙ ደክሟል፡፡ 1947 ፓንአፍሪካ የተባለ ህትመትልሳን መሰረተና የአፍሪካን የቀንተቀን ስቃያቸውንና ፍላጎታቸውን ለመላውአፍሪካዊያንና አሜሪካዊያን ያሰራጭነበር፡፡ 

1957 ጋናነጻነቷን ስታገኝ መኮነንከንኩርማህና ፓድሞር ጋርሆኖ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትንለመመስረት ወደ ጋናሄደ፡፡ 1966 ንኩርማህመፈንቅለ መንግስት ከተካሄድባቸውበኋላ መኮነን ወደ እስርቤት ተወረወረ፡፡ ከእስር የተፈቱትበጆሞ ኬንያታ ጥረት ነበር፡፡ከዚያም ጆሞ ኬንያታአገሬ አገርህ ነው በማለትይመስላል ወደ ኬንያወሰዱት፡፡ ከዚያም የኬንያዜግነት ሰጥተው የአገሪቱየቱሪዝም ሚነስተር አድርገውሾሙት፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያዊዝርያ ያለውን ፓን አፍሪካኒስትብዙዎቻችን አናውቅም፡፡ ምንአልባት የናይሮቢ ዩኒቨርሰትቲፕሮፌሰር የሆኑት ኬኔትኪንግ ከዘጠኝ ወር በላይሞኮነንን ቃለ መጠይቅአድርጎ 1973 ያሳተመውንPan-Africanism from Within ማግኜት ብንችልየበለጠ ሰለማንነቱ ማወቅይቻል ይሆናል፡፡
 ክፍልሁለትን በሚቀጥለው ሕትመትይዘን እንመጣለን፡፡ ቸር ሰንብቱ፡፡

 መጣለን፡፡ ቸር ሰንብቱ፡፡

No comments:

| Copyright © 2013 Lomiy Blog