መስፍን ወልደ ማርያም:- 
ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።
የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ
የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ
ሌላ ነው፤ ከኑሮውም ተርፎ ለሲጃራና ለጫት እያወጣ ነው፤ ወይም ሌሎች እያወጡለት ነው፤ ትግሬነታቸው ብቻ እንዲህ የደላቸው በጣም፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ ስለዚህም በወያኔ አገዛዝ ትግሬ ሁሉ ተጠቅሞአል ማለት ከጉልሁ እውነት ጋር የሚጋጭ ስሕተት ነው፤ አብርሃ ሰዎች ትግሬ ሁሉ ተጠቃሚ ሆኗል ሲሉ ‹‹ያመኛል›› ማለቱ ይገባኛል።
ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው፤ ወንጀል በዘር አይተላለፍም፤ እያንዳንዱ ሰው ለሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነትን ይወስዳል፤ ጊዜው ሲደርስ ውጤቱንም ለመቀበል ይገደዳል፤ ይህ የሚሆነው ሰው ሁሉ በመንፈሳዊ ኃይል በጎ መንፈስ አድሮበት፣ አእምሮው በትምህርት ተገርቶ በትክክል ማሰብ ሲችል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን በአለበት ሁኔታ በጎ መንፈስ የራቀው ይመስላል፤ አእምሮም ጭራሹኑ በእኩይ መንፈስና በጥላቻ እየዛገ ነው፤ ስለዚህ ያስፈራል፤ በደቡብ ሱዳን ሁለት መቶ ሰዎች በዘር ተለይተው ታረዱ ሲባል ያስፈራል፤ በናይጂርያ፣ በኮንጎ የሚካሄደውን የዘርና የሃይማኖት እልቂት ስንሰማ ያስፈራል፤ በ1997 ዓ.ም. መለስ ዜናዊና አዲሱ ለገሰ እንዳስታወሱን የሩዋንዳ የጎሣ እልቂት በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ አለ፤ የቅርብ ተኳሽ የሆነው የአግዓዚ ጦርም አድፍጦ መጠበቅ ያስፈራል፤ ሌላውም ይህንን አውቆ አድፍጦ መጠበቁ ያስፈራል፤ ሰማይ ጠቀስ የሠሩት፣ የሥልጣን ኃላፊነትን ችላ ብለው በሥልጣን የሚነግዱና የሚከብሩት፣ የማይኖሩበትን ሕንጻ የሚክቡት፣ ከሕዝብ ጋር ያላቸው የአይጥና የድመት ኑሮ ያስፈራል፤ አቶ አስገደ ወያኔ መደንገጡን ይነግረናል፤ መደንገጥ የማይቆጣጠሩት ፍርሃት ነውና አደጋ ያመጣል፤ አደጋው አደጋን ይጠራል፤ ይህም ያስፈራል።
በትግራይ ዙሪያ ያለው ምንድን ነው? የትግራይ ሕዝብ በየትኛው አቅጣጫ ነው አንደልቡ እየተዘዋወረ ለመሥራትና ለመኖር የሚችለው? ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከሰሜን ከወገኑ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አቃብቶታል፤ በደቡብ-ምሥራቅ ከወሎ መሬት ቆርሶ የወሎን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ በደቡብ-ምዕራብ ከጎንደር መሬት ቆርሶ የጎንደርን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ የራስን ወገኖች አስቀይሞ ሱዳንን በመሬት ለመደለል የሚደረገው ጥረት ሁሉ ፋይዳ የለውም፤ ሱዳን ለራሱም ያልበጀ አገር መሆኑ እየታየ ነው፤ ወደፊት ደግሞ ይበልጥ ይታያል፤ በትግራይ ውስጥ ደግሞ ወያኔ የፈጠረው አፓርቴይድ የወያኔን የኑሮ ደረጃ ወደሰማይ ሲያስጠጋው፣ የቀረውን ወደአንጦርጦስ የደሀነት ገደል ውስጥ ከቶታል፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ከተማ ከነልጆቻቸው እየተዘዋወሩ የሚለምኑ ሞልተዋል፤ ይህ ልመናም ለወያኔ ለመገበር ነው፤ ብዙዎቹ እንደሚናገሩት የሚለምኑት የማዳበሪያ ዕዳቸውን ለወያኔ ለመክፈል ነው።
ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ጥላቻ ወደንዴት፣ ንዴት ወደቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉም ሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደአውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።
ሌላ አገር እንዲህ አልሆነም፤ እዚያ አገር እንዲህ አልሆነም፤ የሚባል ነገር የለም፤ እኛ ዘንድ ሌላ ነው፤ የኢትዮጵያ ደሀዎች እንባ የእግዚአብሔርን ሰማይ አጨቀየው!
ክፋት እንደእሳት ይቃጠላል፤ ኵርንችቱንና እሾሁን ይበላል፤ ጭፍቅ የሆነውንም ዱር ያቃጥላል፤ ጢሱም ተትጐልጕሎ እንደዓምድ ይወጣል፤ በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ቁጣ ምድር ተቃጥላለች፤ ሕዝቡም እሳት እንደሚበላው እንጨት ሆኖአል፤ ሰውም ለወንድሙ አይራራም፤ ሰው በቀኙ በኩል ይነቅላል፤ ይራብማል፤ በግራም በኩል ይበላል፤ አይጠግብምም፤ እያንዳንዱም የክንዱን ሥጋ ይበላል፤ ምናሴ ኤፍሬምን፣ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላል፤… ኢሳይያስ 9/18-21

ትንቢተ ኢሳይያስ ለሩዋንዳውያን ብቻ አይደለም፤ ጥላቻና ክፋት በተዘራበት ቦታ ሁሉ ውጤቱ ጥፋት ነው፤ ምናሴ ኤፍሬምን በልቶ አይቀርም፤ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላዋል።

 ጸሓፊ፡-አፈንዲ ሙተቂ:-
ፕሮፌሰር መስፍንን በአካል ያየሁት ሁለት ጊዜ ያህል ብቻ ነው፡፡ በነዚህም ጊዜያት ከመጨባበጥ በቀር ሌላ ነገር ማውጋት አልቻልንም፡፡ ብንጨዋወት እንኳ በፖለቲካ አመለካከታችን የምንግባባ አይመስለኝም፡፡ ለምሳሌ እሳቸው “ኢትዮጵያ ውስጥ ነገዶችና ጎሳዎች እንጂ ብሄሮችና ብሄረሰቦች የሉም፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አንድ ብሄር ብቻ
ነው” ነው የሚሉት፡፡ እኔ ግን “በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ፤ ነገድና ጎሳ የብሄር ቅርንጫፎች እንጂ ራሳቸውን የቻሉ ህዝቦች አይደሉም” ነው የምለው፡፡ በሌላ በኩል ፕሮፌሰር መስፍን “የብሄረሰቦችን መብት ለማስከበር በብሄር መደራጀቱ ለሀገር አንድነት አደጋ አለው” የሚል እምነት አላቸው፡፡ እኔ ግን “ለመጥፎ ዓላማ እስካልሆነ ድረስ በብሄር መደራጀቱ መጥፎ አይደለም” የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሌላም ብዙ ልዩነት ማስቆጠር ይቻላል፡፡
ይሁንና በፖለቲካ እንዲህ የተለየኋቸውን ምሁር ለአንድም ቀን እንደ ጠላት አይቼአቸው አላውቅም፡፡ በተቃራኒው ህሊናን በሚያምራምሩ ብዙ ባህሪያቶቻቸው በጣም ያስቀኑኛል፡፡ “እኛስ መቼ ነው እንደርሳቸው ሆነን ለሀገራችንና ለህዝባችን ክብር የምንቆረቆረው” እላለሁ፡፡ ከዚህ ፈቅ የሚሉት አንዳንድ አድራጎታቸው ግን በነቢያትና በቅዱሳን ካልሆነ በቀር ከኛ ዘመን ሰው የሚጠበቁ አይደሉም፡፡

በእርግጥ እላችኋለሁ! ፕሮፌሰር መስፍን በብዙ አጋጣሚዎች “ሰው ማለት… ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋ ዕለት” የተሰኘውን ብሂል በተግባር ከውነው ያሳዩን ብሄራዊ ጀግና ናቸው፡፡ እኝህ ታላቅ ሰው ሀገራችን ሰው በምትፈልግበት ልዩ ልዩ አጋጣሚዎች በልዩ ድፍረትና ልበ ሙሉነት በከወኗቸው ድርጊቶቻቸው የህዝብ ልጅ መሆናቸውን አስመስክረዋል፡፡
ፕሮፌሰር መስፍን ለብቻቸው ሆነው የፈጸሟቸውን በርካታ ገድሎች መዘርዘር እንችላለን፡፡ ለዛሬው ግን በጣም ጥቂቶቹን ብቻ እንዲህ እንዘክርላቸዋለን፡፡
=== የትግራይና ድርቅና ረሃብ===
ብዙዎቻችን በ1965 ስለተከሰተው የወሎ ረሃብ በቂ መረጃ አለን፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በ1950ዎቹ ስለተከሰተው የትግራይ ረሃብ ግን ብዙም ሲጻፍ አላነበብኩም፡፡ ችግሩ የተከሰተው የያኔው ረሃብ እንደ 1965ቱ ረሃብ በቂ የሚዲያ ሽፋን ባለማግኘቱ ይመስለኛል፡፡
በርግጥም ያ ረሃብ ከፍተኛ እልቂት የታየበት ነበር፡፡ የንጉሡ መንግሥት የረሃቡ ወሬ ታፍኖ እንዲቀር በማድረጉ በልዮ ልዩ ክፍለ ሀገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ለትግራይ ወገኑ ሊደርስለት አልቻለም፡፡ መኳንንቱና መሳፍንቱ ከድሮም ጀምሮ የደሃው ህይወት ስለማያሳስባቸው የረሃቡን ጉዳይ ከቁብ አልቆጠሩትም፡፡ በዚያ ወቅት ድምጹን ያሰማው ብቸኛው ኢትዮጵያዊ መስፍን ወልደማሪያም ነበር፡፡
ፕሮፌሰር መስፍን የረሃቡን ወሬ የሰሙት ከተማሪዎቻቸው ነው፡፡ ረሀብ በትግራይ መኖሩ ሲነገራቸው ለንጉሡ መንግሥት ባለስጣናት አቤት አሉ፡፡ ሆኖም መንግሥቱ ለወሬው ደንታ አልነበረውም፡፡ በመሆኑም ፕሮፌሰር መስፍን የነበራቸው ብቸኛ አማራጭ ከተማሪዎቻቸው ጋር እየዞሩ ከህዝቡ እርዳታ መለመን ነው፡፡ በዚህም የተፈለገውን ያህል ውጤት ለማግኘት ባይችሉም የተወሰኑ ዜጎቻችንን ህይወት ለመታደግ በቅተዋል፡፡ በዚህም የተነሳ በወቅቱ ድምጻቸውን ያሰሙ ብቸኛው ሰው ሆነው በታሪክ ተመዝግበዋል፡፡
===የአጣሪ ኮሚሽን===
የቀዳማዊ ሃይለ ሥላሤ መንግሥት ሲንኮታኮት በርካታ ባለስልጣናት በስልጣናቸው አላግባብ በልጽገዋል በሚል ታስረው ነበር፡፡ የነዚያን ባልስጣናት ጉዳይ አይቶ ለፍርድ የሚያቀርብ አጣሪ ኮሚሽንም ተቋቁሞ ነበር፡፡ የዚያ ኮሚሽን ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መስፍን ነበሩ፡፡
አጣሪ ኮሚሽኑ ምርመራውን በከፍተኛ ሃላፊነትና በሰከነ መንፈስ ማካሄድ ጀመረ፡፡ ይሁንና የኮሚሽኑ አካሄድ ተናዳፊዎቹን የደርግ መኮንኖች ሊያረካ አልቻለም፡፡ በመሆኑም የደርጉ ም/ሊቀመንበር የነበረው ሻለቃ መንግሥቱ ኃይለማሪያም በኮሚሽኑ ስራ ጣልቃ ገብቶ ማወክ ጀመረ፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንንም “ቶሎ ቶሎ መታ አድርግና ጨርስ እንጂ! እስከመቼ ነው እነዚህን አሳማ ባለስልጣናት የምንቀልበው” አላቸው፡፡ ይሁንና ፕሮፌሰር መስፍን ለጓድ መንጌ ጫና አልተበገሩም፡፡ እንዲህ የሚል የድፍረት መልስ ሰጡት፡፡
“ጓድ ሊቀመንበር! የሀገር መሪ ለታሪክ ጭምር ማሰብ አለበት፡፡ ታሪክ ማለት ዛሬ ስለናንተ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚጻፈው እንዳይመስልዎት፡፡ ታሪክ ጊዜው ሲደርስ እውነቱ ከሐሰቱ ተጣርቶ የሚቀረው ቅሪት ነው”
ሻለቃ መንግሥቱ በፕሮፌሰር መስፍን አነጋገር ተናደደ፡፡ ወዲያኑ አጣሪ ኮሚሽኑን በመበተን በባለስልጣናቱ ላይ የሞት እርምጃ እንዲወሰድ አደረገ፡፡
=== የብሄራዊ እርቅ ጥያቄ===
ደርግ ከሻዕቢያና ከህወሐት ጋር የሚያደርገው ጦርነት እየተጠናከረ በመጣበት ወቅት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በጭንቀት ውስጥ ወደቀ፡፡ ብዙዎች “ሀገራችን እንደ ሶማሊያና ላይቤሪያ ልትሆን ነው” በማለት ተወጠሩ፡፡ ይሁንና አንድም ሰው ጦርነቱን ለማስቆም ይበጃል ያለውን ሀሳብ ለመሰንዘር አልቻለም፡፡ በተለይም የጊዜው መሪ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም የርሳቸውን ሃሳብ የሚጻረረውን ሁሉ ያጠፋሉ እየተባለ ይነገር ስለነበር ሁሉም ኢትዮጰያዊ በቤቱ ከትቶ ፈጣሪውን መማጸኑን ነው የመረጠው፡፡
አንድ ሰው ግን አላስቻለውም፡፡ “ሀገሬ በጦርነት አዙሪት ከምትጠፋ የመሰለኝን ሃሳብ ልሰንዝርና የሚሆነውን ልጠብቅ” በማለት የመሰለውን እርምጃ ለመውሰድ ተነሳ፡፡ “ጦርነቱን ለማቆም ብቸኛው መፍትሔ ብሄራዊ እርቅና ማድረግና የሽማግሌዎች ባለአደራ መንግሥት ማቋቋም ነው” በማለት ለፕሬዚዳንቱ ግልጽ ደብዳቤ ጻፈ፡፡ በሚቋቋመው መንግሥት አወቃቀር ላይ በሂልተን ሆቴል ማብራሪያ ሰጠ፡፡
ይሁን እንጂ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ “የባልና የሚስት ጥል እንጂ የኢትዮጵያ ጉዳይ በሽማግሌ አይፈታም” በማለት የሰላም ፎርሙላውን አጣጣሉት፡፡ በታሪክ አጋጣሚ የተሰጣቸውን የመጨረሻ እድል አበላሹት፡፡ በመሆኑም መንጌ በወሰዱት የጀብደኝት እርምጃ ለዘልዓለሙ የታሪክ ተወቃሽ ሆነው ቀሩ፡፡ የሰላም ፎርሙላውን ያቀረበው ሰውዬ ግን በታሪክ መዝገብ ስሙን በደማቁ አስጻፈ፡፡
እንግዲህ ያ ሰውዬ ማለት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ናቸው፡፡ ሰው በጠፋ እለት ሰው ሆነው የተገኙ ደፋር ሰው!!
===የለንደን ኮንፈረንስ===
በግንቦት ወር 1983 የተካሄደው የለንደን ኮንፈረንስ አዲስ የፖለቲካ አቅጣጫ ከአዲስ አዙሪት ጋር ሊያመጣ እንደሚችል ብዙዎች አስቀድመው ገምተዋል፡፡ ይሁን እንጂ የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል በማለት በኮንፈረሱ ቦታ የተገኘ ሰው አልነበረም፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ግን ስምንት ያህል ምሁራንን በማስተባበር ከኮንፈረንሱ ቦታ ሄደው ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡ በተለይም “የኢትዮጵያና ኤርትራ ፍቺ የሁለቱን ህዝቦች ፍላጎት ያገናዘበ ካልሆነ በስተቀር በሁለቱ ህዝቦች መካከል መቃቃርን ይፈጥራል” በማለት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ ያ አነጋገር ከሰባት ዓመታት በኋላ እውነት ሆኖ ብዙዎችን አስደንቋል፡፡
በዚያ ኮንፈረንስ ላይ በጣም አስገራሚ ሆኖ የተገኘው ሌላኛው ነገር ፕሮፌሰር መስፍን ከሻዕቢያው ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የነበራቸው ቆይታ ነው፡፡ ከኢሳያስ ጋር እንደ ወንድማማች ሆነው ሲጨዋወቱ ያዩዋቸው ሰዎች “ሁለቱ ሰዎች ከዚያ በፊት ይተዋወቁ ነበር እንዴ?” የሚል ጥያቄ አጭረዋል፡፡ ከአቶ ኢሳያስ ጋር ያወሩትን ያህል ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር አለመቀራረባቸውም ሌላኛው አስገራሚ ነገር ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
=== የሰብዓዊ መብት ጉባኤ===
በሰኔ 1983 የተመሰረተው የሽግግር መንግሥት ያጸደቀው ቻርተር በኢትዮጵያ ውስጥ የሃሳብና የመደራጀት ነጻነት መፈቀዱን አብስሮ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚያ በፊት ባልታየ መልኩ እንደ አሸን ፈሉ፡፡ ህብረ ብሄራዊና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ተመሰረቱ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ “ሰብዒ መብት” የሚል ለብዙዎች እንግዳ የሆነ ጽንሰ-ሃሳብ በሚዲያ መንሸራሸር ጀመረ፡፡
አብዛኛው ምሁር ከአንዱ የፖለቲካ ቡድን ጋር ራሱን አቆላለፈ፡፡ የዘመኑ እንግዳ ደራሽ የሆነውን የሰብዓዊ መብት ጽንሰ-ሃሳብ የሚያብራራ ሰው ግን ጠፋ፡፡ በዚህ መሀል ነው ታላቁ ኢትዮጵያዊ ምሁር ብዙዎች የረሱትን የሰብዓዊ መብት አጀንዳ በማንሳት ለህዝቡ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በማስረጃ ለመሞገት የተነሱት፡፡ እርሳቸው ያቋቋሙት ድርጅትም ባለፉት ሀያ ሁለት ዓመታት የሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠበቃ በመሆን ያሳለፈው ውጣ ውረድ እንዲህ በቀላሉ የሚገለጽ አይደለም፡፡
ስለ ሰብዓዊ መብትና መከራከርና በጉዳዩ ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጥ በዋነኛነት በመንግሥት መፈጸም የነበረበት ስራ ነው፡፡ በመሆኑም ፕሮፌሰር መስፍን በሰሩት ስራ መንግሥት ከፍተኛ ሽልማት ሊያበረክትላቸው ይገባ ነበር፡፡ ይሁንና የተደረገው የዚህ ተቃራኒ ነው፡፡ የመንግሥት ካድሬዎች ከኢትዮጵያዊ ባህልና ስነ-ምግባር ውጪ ፕሮፌሰር መስፍንን በአጸያፊ ስድቦች ሲያብጠለጥሏቸው ነው የሰነበቱት፡፡ እርሳቸው ግን ስድቡንም ሆነ እስሩን ችለው ለህዝቡ መከራከራቸውን ቀጥለዋል፡፡ ለህዝባቸው ሲሉ ሁሉንም የተጋፈጡ ጀግና ምሁር!
===የኤርትራዊያን መባረር===
የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት “የዐይናቸው ቀለም አላማረንም” የሚል ያልተለመደ ምክንያት እየተሰጠ በርካታ ኤርትራዊያን (በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ) ተባረዋል፡፡ ታዲያ የመንግሥት እርምጃ ከተቃዋሚዎችም ሆነ ከሌሎች ወገኖች ብዙም ተቃውሞ አልገጠመውም፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ግን አላስቻላቸውም፡፡ “ሻዕቢያ ወረረን ተብሎ ኤርትራዊያንን በጅምላ ማባረር ታሪካዊ ስህተት መፈጸም ነው፤ ሰዎቹ ከተባረሩም እንኳ የሰብዓዊ መብታቸውን በማይነካ መልኩ መሆን አለበት” በማለት ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ ታዲያ በዚያን ጊዜ የተፈጸመው ነገር እስከ አሁን ድረስ ለብዙዎች እንግዳ ነው፡፡ ለወትሮው ከፕሮፌሰር መስፍን ጋር በሃሳብ የሚጣጣሙት የግል ጋዜጦችም እንኳ በእርሳቸው ላይ ጀርባቸውን አዙረው የሚበቃቸውን ያህል አብጠለጠሏቸው፡፡ አንዳንዶቹ ጭራሽ ከሻዕቢያ ጉቦ የተቀበሉ አስመሰሏቸው፡፡
ጥቂት ወራት አለፉ፡፡ ኤርትራዊያንን በጅምላ ማባረር ስህተት መሆኑን ሁሉም አመነ፡፡ መንግሥት ካባረራቸው መካከል ጥቂት የማይባሉት እንደገና ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደረጉ፡፡ በ1997 እንዲያውም “ኖርማላይዜሽን” የሚል እቅድ በተግባር ላይ እንዲውል ተደረገና “በጣም ድንቅ ሃሳብ” ተብሎ ተሞካሸ፡፡ ይሁንና ሁሉንም አስቀድመው የተናገሩት ፕሮፌሰር መስፍን ነበሩ፡፡ ሌሎች የርሳቸውን ሃሳብ ቀምተው ተወደሱበት፡፡ እንዲህ ነች የኛ ኢትዮጵያ!
————————
ፕሮፌሰር መስፍን ማለት በዚህች አጭር ጽሑፍ የሚገለጹ ሰው አይደሉም፡፡ ብዙ ድርሳናትን የሚያስጽፉ ታላቅ ሰው ናቸው፡፡ እኝህ ደፋርና ለህሊናቸው ታማኝ የሆኑ ምሁር በቅርቡ ሰማኒያ ሁለተኛ ዓመታቸውን ያከብራሉ፡፡ ታዲያ አንድ የሚያሳዝነኝ ነገር አለ፡፡ ብዙዎች ግለ-ታሪካቸውን እየጻፉ የህይወት ልምዳቸውን በጥቂቱ እንድንመለከት እያደረጉን ነው፡፡ በዚህ ረገድ ፕሮፌሰር መስፍን እጅግ ዘግይተዋል፡፡ የ20ኛውን ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያን ጥልፍልፍ የታሪክ ጉዞ ሊያስተምሩን የሚችሉት ሰው ዝም ብለውናል፡፡
እነ ልደቱ አያሌውን የመሳሰሉ ትንንሽ ፖለቲከኞች እንኳ “ታሪኬን እወቁልኝ” እያሉ በሚነዘንዙበት ዘመን መስፍንን የመሰለ “አንድ ለእናቱ” የሆነ ሰው ዝም ማለቱ አግባብ አይመስለንም፡፡ ስለዚህ እኝህ የሀገር ቅርስ የሆኑ ታላቅ ሰው በቀሪው የህይወት ዘመናቸው በዚህ ላይ ሊያተኩሩ ይገባል እላለሁ፡፡
————————
አፈንዲ ሙተቂ
መጋቢት 6/2006
ሸገር -አዲስ አበባ

ሶስት ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ገብተዋል:: 
“ረብሻውን ያነሱት ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው”      የከተማው ኮሙዩኒኬሽን):-


“ባህርዳር በተካሄደው የስፖርት ውድድር ላይ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎ ተፈጽሟል” በማለት የተቧደኑ ወጣቶች፣ ባለፈው ሐሙስ የሱሉልታ ከተማ ነዋሪ የሆኑ በርካታ የአማራ ተወላጆች ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ 

በድብደባ በርካታ ሰዎች ከመጐዳታቸውም በተጨማሪ፤ ቤት ንብረት ላይም ጥፋት እንደደረሰ የተናገሩት ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች ጉዳዩን ሕገወጥ ነው ሲሉ አውግዘውታል፡፡ የከተማዋ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ፤ የስፖርት ውድድርን ሰበብ በማድረግ ረብሻ የቀሰቀሱ ሰዎች ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው ብለዋል፡፡ 
ረብሻውን ቀስቅሰዋል ተብለው ከተጠረጠሩት ውስጥ አራቱን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ገልፀዋል ሃላፊው፡፡ 
“የቤቴ በርና መስኮት እንዳልነበር ሆኗል፤ አጥር ተገነጣጥሏል፤ መስኮቶች ዱቄት ሆነዋል”  ያሉት አንድ የከተማዋ የረጅም ጊዜ ነዋሪ፤ ከ30 በላይ ቤቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡   የስድስት ልጆች እናት እንደሆኑ የገለፁልን ሌላዋ ነዋሪ፤ በቤታቸውና በንብረታቸው ላይ አደጋ መድረሱን ጠቅሰው፤ እንደሌሎች ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ባያጋጥማቸውም በእጃቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት በከተማዋ አንድ ክሊኒክ ህክምና እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡ 
“ይህ ህዝቡ በሰላም አብሮ እንዳይኖርና እንዳይግባባ ሆን ተብሎ የሚጫር የነገር እሳት ነው” ያሉት የ56 አመት አዛውንት በበኩላቸው፤ መንግስት መፍትሔ ከላበጀለት በቀር በአሁኑ ወቅት ከየአቅጣጫው የምንሰማው በዘር ተቧድኖ ግጭት የመፍጠር ጉዳይ አስጊ ነው ብለዋል፡፡ 
የከተማው አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መሳይ ከበደ፤ ከከተማ አስተዳደር በደረሳቸው ሪፖርት ተዘዋውረው እንደተመለከቱ ገልፀው፣ የተወራውን ያህል ባይሆንም የስምንት ቤቶች የበርና የመስኮት መስታወቶች ተሰባብረዋል፤ የቆርቆሮ አጥሮች ተገነጣጥለዋል ብለዋል፡፡  ሰዎች አራት እንደተጐዱና የሶስቱ ሰዎች ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነ በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ በክህምና ላይ መሆናቸውን አቶ መሳይ ጠቅሰው፤ አንዲት እናት በእጃቸው ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸው በከተማው ጤና ጣቢያ ታክመው ተመልሰዋል ብለዋል፡፡
“የረብሻው መንስኤ በቅርቡ ባህርዳር የተካሄደው የመላው ኢትዮጵያ ጫዋታዎች ውድድር ላይ በኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎና ተፅእኖ ተደርጓል የሚል ሰበብ ነው” ብለዋል አቶ መሳይ፡፡ 
“በረብሻው ዙሪያ ህዝቡንና የከተማ ነዋሪውን በመሰብሰብ ረብሻውን ያስነሱት ሰዎች ህዝብን የማይወክሉ እና ህዝብን ለማጋጨት ፍላጎት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች መሆናቸውን  ተወያተናል” ያሉት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊው፣ ህዝቡ እንዲህ ዓይነት ቡድኖችም ሆኑ ግለሰቦችን አሳልፎ እንዲሰጥ ተግባብተናል ብለዋል፡፡ ረብሻው ወዲያውኑ በፖሊሶችና ከጫንጮ በመጡ የፀጥታ ኃይሎች መቆሙን ተናግረዋል - ሃላፊው፡፡ 

 Source: Addis Admass

“ወደ አንድነት ፓርቲ የመጣነው መሬት ያስመልስልናል ብለን አይደለም” 
 ስምንቱ በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው አድረዋል  
“ያለ አግባብ የተያዘ መሬት ላይ ሁሌም እግድ ይጣላል” - የዞኑ አስተዳደር 
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ አዋዲ ጉልፋ ቀበሌ፤ የመጡ 29 የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች “መሬት እንዳናርስ ተከለከልን፤ ቅሬታችንን የሚሰማን አጣን” ሲሉ አማረሩ፡፡ ከ29ኙ ስምንቱ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ፣ ወረዳ ሰባት ፖሊስ ጣቢያ፣ ረቡዕ ማታ ታስረው
ማደራቸውንና ሀሙስ ረፋድ ላይ መለቀቃቸውን አርሶ አደሮቹ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ አብዛኞቹ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደርና ከሌሎች የአማራ አካባቢዎች መሸኛ በማምጣት መሬት እንደተሰጣቸው፣ በአዋዲ ጉልፋ፣ በአጂላ ዳሌና በዙሪያው መሬት በማልማት፣ ቤተእምነት በመገንባትና ሌሎት መሰረተ ልማቶችን በመስራት ከ20 ዓመታት በላይ በሰላም እንደኖሩ ገልፀው፣ ከ2004 ዓ.ም ወዲህ ግን በአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች ላይ የመሬት እቀባ እንደተጣለ ተናግረዋል፡፡ 
አቶ ቢያዝን አበራ የ65 ዓመት አዛውንት ናቸው። ትውልድና እድገታቸው ጎንደር ቢሆንም በመሬት ጥበትና በተፈጥሮ መጎዳት ሳቢያ ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ አዋዲ ጎልፋ ቀበሌ በ1986 ዓ.ም መጥተው መኖር እንደጀመሩ ይናገራሉ፡፡ ላለፉት 20 ዓመታት መሬታቸውን እያረሱ፣ ለመሰረተ ልማት መዋጮ እያዋጡ፣ አካባቢያቸውን እያለሙ ዘጠኝ ልጆቻውን ሲያሳድጉ መኖራቸውን ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ከ2004 ዓ.ም በኋላ ነገሮች እየተቀየሩ፣ የአካባቢው ባለስልጣናት ባህሪ እየተለወጠና በአማራ ተወላጆች ላይ ጫናው እየበረታ እንደመጣ ገልፀዋል፡፡ “በ2004 ዓ.ም የአማራ ህዝብ ከሰፈረባቸው ቀበሌዎች አንዱ በሆነው አጂላዳሌ ቀበሌ፣ ከሰሜን ሸዋ የመጡ የ150 አባወራዎች ቤት በእሳት ጋይቶ ሰዎቹ የት እንደደረሱ ጠፍተዋል” ያሉት አቶ ቢያዝን፤እርሳቸው በሚኖሩበት አዋዲ ጉልፋ ቀበሌም “ለአማራ ተወላጆች ሁለት ሁለት ሄክታር መሬት ይበቃል፤ ቀሪውን ለኦሮሚያ ወጣቶች እንሰጣለን” በሚል መሬታቸውን አርሰው እንዳይበሉ እንዳደረጉዋቸው ተናግረዋል፡፡ “ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከወረዳ ወደ ዞን፣ ከዞን ወደ ክልል አቤት ብለን ሰሚ በማጣታችን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት እና ወደ ፌዴሬሽን ም/ቤት አቤት ብለናል” ያሉት አዛውንቱ፤ “ይህን የሚያደርገው የአስተሳሰብ እጥረት ያለበት ነው፤ ወደ ቦታችሁ ተመለሱ ውሳኔ እንሰጣለን” ብንባልም እስካሁን ምንም ውሳኔ አላገኘንም ብለዋል፡፡ “ጉዳዩ በእንጥልጥል እያለ መጋቢት 8 ቀን 2006 ዓ.ም አንድም በአማራ ተወላጆች የተያዘ መሬት እንዳይታረስና እንዳይዘራ የሚል እግድ ደብዳቤ ወጣብን” በማለት የእግድ ደብዳቤውን በማስረጃነት አቅርበዋል፡፡ 
ደሳለኝ በላቸው የተባሉት ሌላው የ43 ዓመት ጎልማሳ፤ ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ ከአባታቸው ጋር ወደ ናኖ ወረዳ እንደመጡ ገልፀው፣ ከናኖ ወደ ዳኖ የመጡበት ምክንያት በወረዳው ሰዎች በተደረገላቸው የአብረን እንኑር ጥሪ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከደቡብ ጎንደር በልጅነታቸው እንደመጡ የገለፁት አቶ ደሳለኝ፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ስምንት ልጆችን አፍርተው በሰላም መኖር እንደ ጀመሩ ገልፀዋል፡፡ ከ29ኙ የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች ጋር በአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ቢሮ ውስጥ በተነጠፈ ጂባ ላይ ተቀምጠው ያገኘናቸው ጎልማሳው፤ በወረዳው ባለስልጣናት ከፍተኛ የመብት ጥሰት እየደረሰ እንደሆነ ገልጸው በአካባቢው ያሉ የመኪና መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን እና መሰል መሰረተ ልማቶችን ከመሰሎቻቸው ጋር መገንባታቸውን፣ ጠፍ የነበረውን መሬት አልምተው ግብር እየከፈሉ፣ ለመሰረተ ልማትና ለአባይ ግድብ እንደ ማንኛውም ዜጋ እያዋጡ እየኖሩ “አማራ ነህ ፤መሬት አይገባህም” መባላቸውን ተቃውመዋል፡፡ 
“ትምህርት የሚሰጠው በኦሮምኛ ብቻ በመሆኑ ልጆቻችንን ወሊሶና ወልቂጤ ልከን በስንቅ እናስተምራለን” ያሉት አቶ ደሳለኝ፤ “በወረዳውና በቀበሌው ኃላፊዎች ስብሰባ ተጠርተን ሄደን በኦሮምኛ ተጀምሮ በኦሮምኛ ያልቃል፤ ስብሰባው እኛን የማያሳትፍ ከሆነ ለምን ጠራችሁን ስንል፤ ግዴታችሁ ነው እንባላለን” ብለዋል፡፡ 
“ይባስ ብለው መሬት ለምን ትቀሙናላችሁ? አብረናችሁ የኖርን፣ አካባቢውን ያለማን ነን ስንል ድብደባና ግርፋት ደርሶብናል” ያሉት አቶ ደሳለኝ፤ በዚህ ሳቢያ ጌጡ ክብረት የተባለ የአጂላ ፉዳሌ ቀበሌ ነዋሪ የአማራ ተወላጅ፣ህግና ፖሊስ ባለበት ተደብድቦ ሞቷል፤ እስካሁን ገዳዮቹም አልተያዙም፤ ክስም አልተመሰረተም” ሲሉ አማረዋል፡፡ ከ20 ዓመት በላይ ኖረን ጥሩ ልማትና ጥሩ ስራ ስንሰራ “ህገ-ወጥ ሰፋሪዎች ናችሁ፤ ወደ ክልላችሁ ሂዱ፤ መሬቱ ለኦሮሞ ወጣቶች ይፈለጋል” ተባልን ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ ይሄም ኢትዮጵያዊነታችንን እንድንጠራጠር አድርጎናል ብለዋል፡፡ 
ለፌዴሬሽን ም/ቤት በተደጋጋሚ አቤት ማለታቸውንና ምላሽ አለማግኘታቸውን የገለፁት አርሶ አደሮቹ፤ በድጋሚም መምጣታቸውን ጠቁመው፤ “የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈጉባኤ ስለሌሉ ወደ ቦታችሁ ተመለሱ” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ የመጣችሁት ፌዴሬሽን ም/ቤት ከሆነ እንዴት ወደ አንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት መጣችሁ በማለት ላቀረብነው ጥያቄም፤ “በአገሪቱ መሪ በኢህአዴጋችን ምላሽ በማጣታችን ጉዳያችንን ለኢትዮጵያ እና ለዓለም ሚዲያ እንዲያሰሙልን በሚል ነው የመጣነው” ብለዋል አቶ ደሳለኝ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች ላይ በአካባቢው ባለስልጣናት እየደረሰ ያለው ግፍና በደል ቆሞ፣ መሬታቸውን እንዳያርሱ የተጣለው እግድ ተነስቶ፣ በሰላም መኖር እንደሚፈልጉ የገለፁት አርሶ አደሮቹ፤ይህ ምላሽ የሚገኘውም ከገዢው ፓርቲ እንደሆነ በመጠቆም አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድላቸው ተማፅነዋል፡፡ 
“ወደ አንድነት ፓርቲ የመጣነው መሬት ያስመልስልናል ብለን አይደለም” ያሉት ሌላው አርሶ አደር፤ በመንግስት በኩል ምላሽ አጥተን መተንፈሻ በማጣታችን ነው ብለዋል፡፡ “የትኛውንም የአካባቢው ተወላጆች የሚያደርጉትን መዋጮ ለአባይ ግድብ፣ ለመንገድ ስራ እያዋጣንና ግብር እየከፈልን ባለበት መሬት እንዳናርስ የታገድንበት ሁኔታ አሳዝኖናል፤ ዜግነታችንና ህልውናችን አደጋ ላይ ወድቋል፤ መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጠን” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ “አሁን ያላችሁበት አካባቢ አትኖሩም ከተባልንም መንግስት ሌላ የምንኖርበት ቦታ ወስዶ እንዲያሰፍረን እንጠይቃለን” ብለዋል፡፡ 
“በአሁኑ ሰዓት ሰሚ አጥን ስንከራተት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ተቀብለው ምግብ እና መኝታ እንድናገኝ አድረገውናል፤ ያለ ስንቅ ነበር የመጣነው” ብለዋል፤አርሶአደሮቹ፡፡ ጉዳያቸውን ለጋዜጠኞች አስረድተው ወደ አገራቸው ሲመለሱ፣ አውቶቡስ ተራ አካባቢ ፖሊሶች ለጥያቄ እንፈልጋችኋለን በማለት ቢያዝን አበራ፣ ደሳለኝ በላቸው፣ ኑሮዬ እንድሪስ፣ ፀጋ ዳምጠውና ሌሎች አራት ሰዎችን በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ ሰባት ፖሊስ ጣቢያ እንደወሰዷቸው የገለፁት አርሶ አደሮች፤ ለምን መጣችሁ፣ ወደ አንድነት ፓርቲ የመራችሁ ማን ነው፣ ከየት ነው የመጣችሁት እና ሌሎች ጥያቄዎች ቀርቦላቸው  መልስ ከሰጡ በኋላ፣ ፖሊስ ጣቢያ አድረው ሀሙስ 3፡30 መለቀቃቸውን  ገልፀዋል፡፡ 
የምዕራብ ሸዋ ዞን መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቱፋ ቴሶ በበኩላቸው፤ በአማራ ተወላጆች ላይ ደርሷል የተባለውን በደል እንደማያውቁት ገልፀው፣ ችግሮችም ካሉ ለዞኑ ማመልከትና ተበድለናል ያሉት አርሶ አደሮች ተሳታፊ በሆኑበት መንገድ ተወያይቶ መፍታት ይቻል እንደነበር ተናግረዋል፡፡ “ችግሩ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ እንዳለ አላውቅም፣ ወደ ኃላፊነቱ የመጣሁት በቅርብ ነው” ያሉት አቶ ቱፋ፤ ችግራቸውን በተዋረድ ሳያሰሙ ወደ ፌዴሬሽን ም/ቤት መሄዳቸው አግባብ እንዳልሆነና ለዞኑ ያሰሙት ቅሬታ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ “እኛ አማራ ቢሆኑም ከየትኛውም ብሔር ቢመጡም የምናያቸው በወንድምነት ነው“ ያሉት የመስተዳድሩ ጽ/ቤት ኃላፊ፤ አሁንም ቢሆን ችግራቸውን ቀርበው ያወያዩንና በስፍራው ተገኝተን ከወረዳው ኃላፊዎች ጋር ተመካክረን እንፈታዋለን” ብለዋል፡፡ 
የአማራ አርሶ አደሮች፣ልጆቻችን በአማርኛ ቋንቋ መማር አልቻሉም በማለት ባነሱት ቅሬታ ዙሪያ አቶ ቱፋ ሲመልሱ፤ “በአገር አቀፍ ደረጃ ከአንድ ክልል መጥተው ሌላ ክልል ውስጥ ለሚኖሩ ዜጎች ት/ቤት ተከፍቶ በልዩ ሁኔታ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ እየተደረገ ነው፡፡ በአጠቃላይ ግን ያለባቸውን ቅሬታ ከዞኑ መስተዳድር ጋር መነጋገር ይኖርባቸዋል” ካሉ በኋላ፣ከዳኖ ወረዳ ወደ ፌደራል መንግስት ቅሬታ ለማሰማት የሄዱ የአማራ አርሶ አደሮች መኖራቸውን የሰሙት በወሬ ደረጃ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ 
“አርሶ አደሮቹ ከአካባቢው ተወላጅ ተለይተው የሚታዩበት መንገድ የለም” ያሉት አቶ ቱፋ፤ ከመጠን በላይ የያዙት መሬት ካለም ሆነ ያለአግባብ ታግደውና መሬት ተወስዶባቸው ከሆነ፣ ሁሉም በህግና በስርዓት እንደሚታይ ገልፀው፤ ከህግ በላይ የሚሆን ማንም እንደሌለ ተናግረዋል፡፡  
የዞኑ ምክትል መስተዳድር አቶ ከሳዬ ገመቹ በበኩላቸው፤ “የታገደ መሬት ካለም ያለ አግባብና በህገ-ወጥ መንገድ የተያዘ ነው” ካሉ በኋላ ከዚህ ቀደም በዚህ ጉዳይ ቅሬታ ያነሱ ሰዎች እንደነበሩና በዞን፣ በወረዳ፣ በክልል እና ከእምባ ጠባቂ ተቋም ተወካዮች መጥተው ጉዳዩ ውሳኔ አግኝቷል ብለዋል፡፡ 
በአማራም ሆነ በአካባቢው ተወላጆች ያለአግባብና ከመጠን በላይ የተያዘ ካለ ታይቶ መሬት ለሌለው ይሰጣል፤ የተረፈው ወደ መንግስት የመሬት ባንክ ይገባል ያሉት ምክትል መስተዳድሩ፤ “በህገ-ወጥ መንገድ ያልተፈቀደ መሬት ይዘው ከአማራ ክልል ስለመጡ የተበደሉ አድርገው ማቅረባቸው፣ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨትና ለመከፋፈል ሆነ ብለው የሚያደርጉት ነው ብለዋል፡፡ 
Source: Addis Admass

(ካሣሁን ዓለሙ):-
አንዳንድ ጊዜ የግብረ ሰዶማዊነት የዚህን ያህል አሟጋች መሆኑን ሳይና በአለማቀፍ ተቋማት ድጋፍ አግኝቶ እንዲስፋፋ ሲደረግ ስመለከትና ስሰማ ይገርመኛል፤ ግርምቴ ዝም ብሎ የመጣ አይደለም፤ ይልቁንም ግብረሰዶም ከሰው ልጆች ተፈጥሮ ውጭ የሆነ ተግባር መስሎ ስለሚታየኝና የሚሰጠው ጥቅም አልገለጽልህ ቢለኝ ነው፡፡ ስለዚህ የራሴን መሟገቻ ነጥቦች ላቅርብ ፈለግሁ ይህ ጽሑፍም በዚህ ዕይታ የተቃኘ ነው፡፡ መልካም ንባብ!
ለመሟገትም ‹ግብረሰዶማዊነት ተፈጥሮ የሚደግፈው ድርጊት ነው ወይ?› በሚል ጥያቄ መነሣት የግድ ይላል፤ መልሱም ‹ግብረሰዶማዊነት ተፈጥሯዊ ነው› የሚል ከሆነ
ቢያስ መሠረታዊ መሥፈርትን ማሟላት ችሏል ማለት ይሆናል፤ ‹አይ! ግብረሰዶማዊነትማ ከሰው ልጆች ተፈጥሯዊ ጠባያት ውጭ የሆነ ወይም ከስብዕና ተፈጥሮ ጋር የማይስማማ ድርጊት ነው› የሚለው ስምምነት ካገኘም ከተፈጥሯችን ውጭ ያሉ ድርጊቶችን የማከናወን መብት አለን ወይ? በድርጊቱስ የሚገኝ ኅብረተሰባዊ ጠቀሜታ ይኖራል? ጉዳትስ የለውም? ከሁለቱ ውጤቶችስ (ከጥቅሙና ጉዳቱ) የሚበልጠው የትኛው ይመስላል? የሚሉ ጥያቄዎች ፊት ለፊታችን መጥተው ያፈጣሉ፡፡ በእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ብንስማማ እነኳን ሌሎች ጥያቆዎችም መምጣታቸው አይቀርም፤ ለምሳሌ የሞራል ጥያቄዎች፣ የማኅበረሰብ ደኅንነት፣ የመንፈሳዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጉዳይና የመልካምነት ጉዳይ በቀላሉ የሚገፉ ወይም የሚተው አይሆኑም፡፡
እስቲ ከመነሻ ጥያቄያችን እንጀምርና አንዳንድ ነጥቦችን እንመልከት፤ ‹ግብረሶዳማዊነት ከሰዎች ተፈጥሮ ጋር ይስማማል?› የሚለው ጥያቄ ቀላል ቢመስልም ዘመን ወለድ ጥንቃቄን የሚሻ ጥያቄ መሆኑም መረዳት ይፈልጋል፤ ቀላል የሚሆነውም በልምዳችን ስንመልሰው እንጂ የተፈጥሯችንን ውስብስብ ጠባያት ሰንፈትሽና ግረሶዶማዊነት አሁን ያለበትን ደረጃ ተመልክተን ‹ለምን?› የሚል ጥያቄን ስናነሣ አስጨናቂነትን ይላበሳል፡፡ እንዲሁም በቀላሉ ከቋጨነው ምንም አታካራ አያስፈልግም፤ ማለትም ሙግቱን ‹የሰው ልጆችን ተፈጥሮ የሚቃወም ነገር ሁሉ አግባብ ስላልሆነ መቃወም ይኖርብናል፤ ስለዚህ ይህንን ከስብዕናችን ውጭ እንድንሆን የሚያደርገንን ድርጊት ማስወግደና ማጥፋት ያስፈልጋል፤ ስብዕናችንን ከማጥፋት የበለጠ ምን መጥፎ ነገር ሊመጣ? ምንም አይኖርም› ብለን መጠቅለል እንችላለን፡፡ ነገር ግን ጉዳዩ ከዚህ በላይ ማየትን የሚጠይቅ ይመስላል፤ እንዲሁም በቀላሉም በዚህ መልክ ከዘጋነው የነገሩን አሳሳቢነትና ውስብስብነት ሳናስተውለው እንድንቀር ሊያደርገን ይችላል፡፡ ይልቁን በዚህ መልክ ነገሩን ከመደምደም ይልቅ ግብረሰዶማዊነት ከተፈጥሯዊ ጠባያችን ጋር በሚኖረው መስተጋብር በሚፈጥረው ነገር በመመሥረት አንዳንድ ነጥቦችን ለመመልከት እንሞክር፡፡
እንደሚታወቀው የትኛውም የተፈጥሮ ክስተት ዝም ብሎ በዘፈቀደ አልተሠራም፤ አንድ ነገር ወይም ሥራም በሥርዓትና በሕግ ነው ውበት አግኝቶ የሚስበው፣ ጥሞም ለጤናማ ሕይወት የሚጠቅመው፤ በዚያው በተሠራበት መሠረት ሲከወንነው መልካምነት የሚኖረው፡፡ የተፈጥሮ ሥርዓት ከጾታ አንጻር ካየነው ሕይወት ያላቸው ፍጥረታት ሁሉ በሁለት እንደሚመደቡ ይታወቃል፤ መመደባቸው ብቻ አይደለም እርስበራስ እንዲሳሳቡም በተፈጥሯቸው የፍቅር ኃይል ተሠጥቷቸዋል፤ ይህም በየደረጃ የተመደበ ነው፡፡ ለምሳሌ እጽዋት ወንዴና ሴቴ ጾታቸው በተለያየ ሥፍራ ቢያድግም፤ እነሱም መንቀሳቀስ ባይችሉም፤ የሚስቡበት የነፋስ ኃይል አላቸው፤ ነፋስ መኖሩ ብቻ ሳይሆን ወንዴው ተስቦ ሴቴዋም ስባ ተፈላልገው ስለሚገናኙ ሌላ ሕይወትን ለማስገኘት/ዘራቸውን ለማስቀጠል ችለዋል፡፡
ከእጽዋት አልፈን ወደ እንሳሳት ስናድግ በጾታዊ ግንኙነት የመሳሳብ ተፈጥሯቸው በጊዜና በሁኔታ ተገድቦ ግንኙነት እንዲፈጽሙም የተፈጥሮ ጠረንና ስሜት ተሰጥቷቸው በዚያው መሠረት እየተደሰቱና እየተራቡ የመኖር ግደታ አለባቸው፤ ለጫወታ ካልሆነ በስተቀር ወንድ እስሳ ወንዱን፤ ሴት አንሳሳም ሴቷን ፈልገው የመገናኘት ዝንባሌ አይታይባቸውም፤ እንዳውም ከጊዜ ገደባቸው ውጭ ‹ለካ ይህም አለ› በማለት በዝሙት ሲጠመዱ ዐይታዩም፡፡ ይህም ምን ያህል ተፈጥሮ በተፈጥሮ ኃይል የምትሳሳብና በተቃራኒ ጾታ ግንኙነት ሥርዓት የተቃኘች መሆኗን ይመሰክራል፤ የሰው ልጅ ደግሞ ከእንስሳት የበለጠም የዕውቀት ሀብት ስላለው ተፈጥረውን የመጠበቅ ኃላፊነትና ግደታ አለበት፡፡
እንዳው ይሁንና አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት በላይ ግንኙነት ቢያደርግ በተፈጥሮ ሕግ መሠረት ድርጊቱ አግባብ መሆኑን የሚደግፈው መከራከሪ ይኖረዋል፡- ሴቷም እንደዚሁ፤ ምንም እንኳን ይኸ ራሱ አሳማኝነት ቢጎድለው፡፡ ምናልባት እዚህ ላይ ‹ለምን አሳማኝነት ይጎድለዋል? አንድ ወንድ ከብዙ ሴቶች ጋር ወይም አንድ ሴት ከብዙ ወንዶች ጋር ግንኙነት ቢያደርግ/ብታደርግ ከብልቶቻቸው መጠንና ዓይነት አንጻር ችግር አለበት ወይ? ይህስ ማንም ከፈለገው ጋር እንዲገናኝ መፈቀዱን ዐያሳይም?› ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል፤ ነገር ግን በዚህም ላይ ቢሆን ማዕቀብ እንዳለበት መረዳት ቀላል ነው፡፡
ምክንያቱም የአንድ ሰው በብዙ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት እንደፈለገ ማድረጉ አንደኛ የመዋለድ ሕግና ሥርዓትን ይቃወማል፤ ምክንያቱም የመዋለድ ሕግ ልጅ ወልዶ ማሳደግን ይጨምራል፤ ልጅ ወልዶ ለማሳደግም አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ወይም አንዲት ሴት አንድን ወንድ ብቻ አግቦቶ/አግብታ ቤተሰብ መመሥረትን ይፈልጋል (አንዳንድ ልዩ ክስተቶችና ድርጊቶች ቢኖሩም በጠቅላላው ሕግ ይሸፈናሉ፤ ይዋጣሉ ምክንያቱም ልዩ ክስተቶች ከጠቅላላው በማፈንገጥ የሚከሰቱ ናቸው፡- ይህ የሚጠይቀው ልብ ብሎ ማስተዋልን ብቻ ነው)፡፡ ሁለተኛም የሴትና የወንድ የፍቅር ሕግ አስተሳሰብን ወጥሮ የሚያላትመው ከአንድ ሰው ጋር ነው፤ ለዚያም ነው ብዙ ሰዎች ለአንድ ሰው ብለው እራሳቸውን መስዋዕት እስከማድርግ የሚደርሱት፤ እንደዚያ ባይሆን ኖሮ ብዙ ወንዶች አንዲትን ሴት ወይም ብዙ ሴቶች አንድን ወንድ ወይም ‹ሁሉም እንደፈለጉ› ሆነው ማኅበረሰብ ሁሉ አሁን ባለው መልኩ በመሆን ትርጉም አይኖረውም ነበር፤ያ ሳይሆን ግን የዓለም ኅብረተሰብ ሁሉ በተለያየ የባህል ዘይቤ እየኖረ አንድ ለአንድ በመፋቀር ቤተሰብ ወደ መመሥረት ያዘነበለ ነው፡፡ ሦስተኛ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአ ያዕቆብ እንዳስተዋለው የዓለም የሴትና የወንድ ብዛት ተመጣጥኖ የሚገኝ መሆኑ አንድ ወንድ ለአንዲት ሴት የተፈጠረ መሆኑን ይገልጻል፤ በተፈጥሮ በዚህ መልክ ባይመጣጠን ኖሮ ሰው በተፈጥሮው አንዱ ወንድ ከአንዲት ሴት ጋር ብቻ መወሰን አለበት ለማለት ይከብድ ነበር፤ ነገር ግን ወንድና ሴት ተመጣጥነው እየተገኙ ሁለትና ከዚያ በላይ ተቃራኒ ጾታን የሚፈልግ ከልኩ በማለፍ የተፈጥሮን ሥርዓት አፍራሽ ይሆናል፡፡ በዕውቀቱ ሥዩም በአንድ ጽሑፉ ዝሙትን እንደፈለግን እንድንፈጽም ተፈጥሮ እንደማይፈቅድልን ሲገልጽ የጾታ ብልታችን ግንባራችን ላይ ሳይሆን ጉያችን ውስጥ መወተፉ ማሳያ መሆኑን ይጠቅሳል፡፡ ስለዚህ ወንድና ሴት እንኳን ለሚያደርጉት ግንኙነት አንድ ለአንድ እንዲወሰኑ የተፈጥሮ ሕግና ሥርዓት ያስገድዳቸዋል፤ ከታሪክ የተገኘ ልምድም እንደፈለጉ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ማድረግን አይመሠክርም፤ ለምሳሌ አፍላጦን (ፕሌቶ) የማኅበር አኗኗርን ለማስለመድ በካምፕ ውስጥ ልጆች አባትና እናታቸውን ሳያውቁ እንዲወለዱ ለማድረግ ሐሳብ አቅርቦ ነበር፤ በግርክ ምድር እውን ሆኖ ግን አልተተገበረም፤ ምክንያቶች ከሚመስሉኝ አንዱ ከተፈጥሮ ሥርዓት ጋር አለመስማማቱ ነው፡- የአባትና የእናትነትን፣ እንዲሁም የልጅነትን ትርጉም ያሳጣልና፤ ያ እውን ሆኖ በዓለም ላይም ተለምዶ ቢሆንም ልጆች ወላጆች፤ ወላጆችም ልጆች አይኖሯቸውም ነበር፡፡
ከዚህ ባለፈ በግብረ ሰዶማዊያን እንደሚባለውና እንደሚደረገው ወንድ ከወንድ ጋር ወይም ሴት ከሴት ጋር የጾታ ግንኙነት አድርጋለሁ ቢል ግን ከሰዎች ብቻ ሳይሆን ከአጠቃላይ የተፈጥሮ ሥርዓት ጋር መላተም ይከሰታል፤ የሰው ልጅ ባህርያዊ ተፈጥሮና የአኗኗር ዘይቤም ጥያቄ ውስጥ ይገባል፤ ይህም ማለት ግብረሰዶማዊነት የሰውን ልጅ ተፈጥሮ ሙሉ ለሙሉ ይቃረናል፡፡ ምክንያቱም አንደኛ የግብረሰዶማዊ ግንኙነት ምሉዕ ጾታዊ አይደለም፤ የሚከናወነው በጾታአይደለምና (ከወንድነት ወይም ከሴትነት ብልትውጭ ጾታነት አለ እንደ!)፤ ምን ማለቴ ነው ሴት ልጅ ከሴት ጋር ግንኙነት እንድትፈጽምበት የተዘጋጀ ብልት የላትም፤ ወንድም ልጅ እንደዚሁ ያለው ብልት ከወንድ ጋር ግብረ ሥጋ ሊፈጽምበት የሚችል አይደለም፤ ከወንድትና ከሴትነት ብልቶች ውጭ ያለው ደግሞ ጾታነት የለውም፤ ከጾታነት ውጭ በሆነው የጾታ ግንኙነት መፈጸም የተፈጥሮ ሕግን የጣሰ ያደርገዋል፡፡ ሁለተኛም እነዚህ የወንድነትና የሴትነት ጾታዎች የተሠሩበት ተግባርና ዓላማ  አላቸው፤ ተግባራቸው ሴትና ወንድ በፍቅር ተሳስበው ግንኙነት እንዲፈጽሙ ማድረግ ሲሆን ዓለማቸው ደግሞ በመዋለድ ትውልድን ማስቀጠል ነው፤ በተፈጥሮ ደግሞ ሕግና ሥርዓት የሌለውና በዚያም መሠረት የማይከናወን የለምና፤ ከዚህ ውጭ የሚከናወን የዘር ማስቀጠል ተግባር ሁሉ ፀረ-ተፈጥሮ በመሆኑ ከሥርዓት ውጭ ነው፤ ያ ማለት ከሚያመጣው ጥቅምና መልካምነት ይልቅ ጉዳቱና መጥፎነቱ ይበልጣል፤ ስለዚህ ከግብረ-ሰዶማውነት ጋር ተያያዥ የሆኑ የዘር ማስቀጠል አማራጮችና ተግባራቸው አካሄዱውም ውጤቱ በችግር የተተበተበ መሆኑን በፀረ-ተፈጥሮነቱ ብቻ መረዳት ይቻላል፡፡ ሦስተኛ ጾታ በሁለትነት ሳይበዛና ሳያንስ ወይም ጾታ አልባ ሳይኮን በተቃራኒነት ብቻ መፈጠሩና ከእነዚህ ስሜቶች ውጭ የሚፈጸሙ ግንኙነቶችም ተያያዥ ችግሮችና በሽታዎች ያሉባቸው መሆኑ የተፈጥሮ ሕግና ሥርዓት ሰዎችን በሴትና በወንድ የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት ብቻ እንዲወሰኑ የሚያስገድድ መሆኑን ይመሰክራል፡፡ እስቲ ልብ ብለን እናስተው በአንዳንድ የተፈጥሮ መዛነፍ ከሚፈጠር ውጭ ማንም ሰው ከአንድ ጾታ በላይ አማራጭ ጾታ ኖሮት ወይም ጾታ አልባ ሆኖ የሚፈጠር የለም፤ ምናልባት ‹ጾታየን ልቀይር› ቢል እንኳን የተፈጥሮ ማዛነፍ ችግር ሰለባ ይሆናል እንጂ በተፈጥሮው እንዳገኘው ዓይነት መልካምነት አይኖረውም፡፡ ስለዚህ ግብረ ሰዶማዊነት የተፈጥሮን ሕግ በቀጥታ መጣስና ሥርዓቱንም ማዛነፍ ነው፤ የሰው ልጅ ደግሞ በተፈጥሮ ከተሰጠው ሕግና ሥርዓት ውጭ ሊሆን የሚችልበት አቅምና አግባብ የለም፤ ሁሉ ነገሩ መልካምነትና ጠቃሚነት የሚኖረው በተፈጥሮ ሥርዓት መሠረት ሲከናወን ብቻ ነው፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ልብ ብለን ካስተዋልን እንስሳትም ሆኑ እጽዋት የጾታዊ ግንኙነትና የመራባት ተግባራቸውን የሚያከናውኑት በተሰጣቸው የተፈጥሮ ሥርዓት ሕጉን ጠብቀው ነው፡- ምንም እንኳን ማሰብ ባይችሉም፤ የማሰላሰል አቅም ባይኖራቸውም፤ በተፈጥሮ የተሠጣጨውን ሥርዓትን የመጠበቅን ኃላፊነት አያፈርሱም፡፡ የሰው ልጅ ደግሞ ድንዙዝ ከሆኑ እጽዋት፣ የማሰብ አቅማቸው ውስን ከኾነባቸው ከእንስሳት በላይ የማሰብ፣ የተፈጥሮ ሥርዓትን በአግባቡ የመገንዘብና በዚያ ሥርዓት ውስጥ መሥራትና አለመሥራት የሚገባውን ከሚያመጣው ችግር/መልካምነት እያነጻጸረ የማኅበረሰቡንና የትውልድን ቀጣነት ሁኔታ፣ የመኖርን ትርጉምና የኃላፊነትን ድርሻ ይረዳል፤ ይህ ከሆነና ግብረሰዶማዊነት እንስሳትና እጽዋት እንኳን የማይተገብሩት ተግባር ከሆነ፤ ይህንን ግብር ካልፈጸምኩ የሚልባት ምክንያት የልክፍት ሱሰኝነት ብቻ ነው የሚሆነው፤ በዚህ ተግባር በመጠመድም የአዕምሮ ጤነኝነት ይኖራል ማለት አይቻልም፤ ስለዚህ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገራት ሕጋዊ ዕውቅና እንዲያገኝ ማድረግም የሰው ልጆችን የተፈጥሮ አኗኗር በቀጥታ ለማስወገድ የሚደረግ ተግባር ነው፡፡
ሁለተኛው ግብረሰዶማዊነትን የምንቃወምበት ምክንያት ከማኅበረሰባዊ ምሥረታ፣ ግንኙነትና ዕሴቶች ጋር አያይዘን ስናየው አደጋው የከፋ በመሆኑ ነው፡፡ የወንድነትና የሴትነት ብልቶች የጾታ ግንኙነት ለመፈጸም ብቻ አይደለም የተፈጠሩት ተያያዥ የሆኑ ማኅበራዊ ግንኙነት ለመፍጠር ምክንያትም ናቸው፡፡ የወንድና ሴት ግንኙነት የመሳብ ኃይል መነሻነት ነው መልካም ቤተሰብ የሚመሠረተውና የሚሥፋፋው፤ በእነዚህ ግንኙት በመግባባት የባልና ሚስት ግንኙነት ሲዳብር ነው ወደ ኅብረተሰብና ማኅበረሰብ የሚያድገው፡፡ እውነቱን ለመናገር የዓለም ሕዝብ ተግባብቶ በመገናኘት መኖር የቻለው በጾታ ብልቶቻችን መስህብነት በፍቅር እየተጎተተ ነው፡፡ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ግን እነዚህን ሀብቶች ያጠፋል እንጂ አያዳብርም፡፡ እንዳው እንበልና ወንዱና ወንዱ በተፈጠረባቸው የዘመን/የበሽተኛነት ሱስ የተነሳ ተስማምተው ቢጋቡ ከዚያ ቀጥሎ በኅብረተሰብና በቀጣይ ትውልድ የሚያመጡት መልካምነት ምንድን ነው? ማንም ሰው በውስጡ የሚሰማው የአሉታ መልስ ነው፡፡
ግብረሰዶማዊነት የማኅበራዊ እሴቶችንና ግንባታዎችን ያዛንፋል፤ ያጠፋል፡፡ መታወቅ የሚኖርበት ያለፉ ትውልዶች በተከታታይ መጥፎውን ከጥሩው እያነጠሩ በማስወገድ፤ መልካሙ ነገር ለትውልድ በሚጠቅም መልኩ በመገንባት እንዲገለገሉበት አድርገው ለእኛ አስረክበውናል፤ ይህም ካወቅነው ትልቅ ሀብት ነው፤ ምናልባት ‹እነ ሁሉን ዐወቅና የዐዲስ ነገር ዘማዊያን› ያለፉ ትውልዶች ያወረሱን የሥነምግባርና የማኅበረሰብ እሴቶች ኋላ ቀር እንደሆኑ ቢሰብኩንም፤ ካስተዋልናቸው ትልቅ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ያለፉ ትውልዶች ያለፉበትና ያስረከቡን የዕውቀት፣ የሥነምግባርና የባህል ዕሴቶች ናቸው፡፡ ልብ ካልን(አንዳንድ ከልማዶች የተነሣ የተከሰቱና ያሉ ችግሮች ቢኖሩም) መሠረታዊ የተፈጥሮ ሥርዓትን የመጠበቅ ዝንባሌያቸውና የማኅበረሰብ ጠቀሜታቸው የላቀ በሥርዓት የተሠሩ ዕሴቶች አሉን፤ በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያን በዚህ በኩል በጣም ዕድለኞች ነን፡፡ እስቲ እናስተውል የሥነ ምግባር ዕሴቶቻችን፣ የባህላዊ ሕግና ሥርዓት አጠባበቃችን፣ ለመኖራችን የምንሠጠው ትርጉምና አጠቃላይ አኗኗራችን በመልካምነት የተቃኘ፣ በሥነምግባር የተጠበበ፣ ለምንፈጽመው ድርጊት ሰውን የምናፍር እጊዜርን የምንፈራ (በፈለግነውም ብናምን)፣ ነግበኔን የምናውቅና የምንጠብቅ ሕዝቦች ነን፤ ይህ ሁሉ የማኅበረሰብ ሀብት ነው፡፡ ግብረሶዶማነት ግን ይህን የተገነባ የማኅበረሰብ ሥርዓት ከሥሩ ቆርጦ ነው የሚጥለው፤ እንዴት?
አንድኛ ኅበረተሰብ የሚገነባው ከቤተሰብ ምሥረታ ነው፤ ግብረሰዶማዊነት ቤተሰብ የመመሥረት ሥርዓትን ያጠፋል፤ በዚህ የተነሣም የማኅበረሰባችንን ዕሴቶች ለቀጣይ ትውልድ የማውረስና የማስቀጠል ኃላፊነት አናገኝም፤ ምናልባት ወንድ ለወንድ፣ ሴት ለሴት በመጋባት መዋለድ ይቻላል የሚል ካለ ያስረዳን፤ መከራከሪችንን እናስተካክላለን፤ በእውነታው ግን ስለሌለ ግብረሰዶማዊነት ማኅበረሰብን በጣሽ ነው ማለታችን ትክክል ነው፡፡ ሁለተኛም ዕሴቶቻችን የተገነቡት በሴትና በወንድ የጾታ ግንኙነት አስተሳሰብ ነው፤ በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አስተሳሰብ ሲቃኙ ግን ዕሴቶቹ ትርጉም ያጣሉ፤ በመጥፎ ባህልነትም ሊፈርጁ ይችላሉ፤ ይህ ደግሞ የወረሱትን ሀብት በእሳት ማቃጠል ነው (ሞኝ ልጅ!)፤ ዕሴቶቻችን በመጥፎነት ሲፈረጁም አባቶቻችንና እናቶቻችን በእኛ ላይ መጥፎ ነገር እንደጫኑብን አድርጎ መፈርጀ ይከሰታል፤ ይህ ግን አግባብ አይሆንም፡፡ ሦስተኛ የግብረሶዶማዊነት ተግባር አግባብ/ትክክል ከሆነ ሌሎች መጥፎ የምንላቸው ነገሮችና ድርጊቶች ከግብረሰዶማዊነት በልጠው እንዴት መጥፎ ሊሆኑ ይችላሉ? ለምሳሌ አንድ ሰው ከፈለገው ጋር በአደባባይ እንደፈለገ ጾታዊ ግንኙነት ቢያደርግ ለምን መጥፎ ሊባል ይችላል? ከቤተሰብ ጋርና በማኅበር የዝሙት ግንኙነት ማድረግስ መጥፎ ነው ልንል የምንችልበት የሞራል አቅምስ ከምን ልናገኝ እንችላለን? እንዴትስ ግብረሰዶማዊነትን በአግባብነቱ ተቀብለን ከተቃራኒ ጾታ የሚፈጸሙ የዝሙት ግብሮች በመጥፎነት ልንፈርጅ እንችላለን? ግብረሰዶማዊነት መጥፎ የሚሆነው ከሁለት ሰዎች በላይ ግንኙነት ሲፈጽሙ  ነው ልንል ነው ወይስ በተመሳሳይ ጾታ የሚደረግ ግንኙነት ያለ ገደብ ከፈለጉት ሰው ጋር ሁሉ መፈጸም ይቻላል በማለት ልንሟገት ነው? (አውጣን!)…፡፡እነዚህ ጥያቄዎች ሁሉ አግባባዊ መልስን ይፈልጋሉ፤ በቀላሉም እንዳንመልሳቸው መልሱ የበለጠ ጥያቄን እየጎለጎለ ይወሳሰባል እንጂ አይቋጭም፡፡ ስለዚህ ግብረሰዶማዊነት በመልካምነት ከተወሰደ እነዚያ ያልናቸውና የምንጠቀምባቸው የሥነምግባርና የማኅበረሰብ ዕሴቶቻችን ትርጉማቸው ይጠፋል፣ አገልግሎታቸው ይዛነፋል (እነ ይሉኝታ፣ ነግበኔ፣ ሰውን ማፈር፣ እጊዜርን መፍራት … ወደ ቆሻሻ ገንዳ ይጣላሉ)፤ በአጠቃላይ ትውልዱ ዐዲስና ልዩ ማኅበረሰብ መሥርቶ ለመገንባት ይገደዳል፡- ከቻለ፤ የትውልድ ቀጣይነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚሆን ታሳቢ ሆኖ፡፡
ሦስተኛው ግብረሰዶማዊነትን የምንቃወምበት ምክንያት ከሃይማኖት ዕሴቶቻችንና ሥነምግባሮቻችን ጋር ስለማይስማማ ነው፡፡ በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያ አብዛኞቹ ባህላዊ ዕሤቶችቻን ሃይማኖትን መሠረት የሚያደርጉ ናቸው፤በሃይማኖት መጽሐፎቻች ደግሞ የግብረሰዶማዊነት መጥፎነቱ እንጂ መልካምነቱ አልተጠቀሰም፤ አልተነገረም፡፡ ስሙን ራሱ ‹የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት› ከማለት ይልቅ ‹ግብረሰዶም› የተባለው የሰዶም ሰዎች ይፈጽሙት የነበረ ግብር ስለነበርና እነሱንም እግዚአብሔር ተቆጥቶ በእሳት እንዳጠፋቸው ስለምናውቅ ነው፤ በዚህ ድርጊት ያልተባበረውን ሎጥን ግን ከዚያ መአት እንዳዳነው ስለተነገረን ነው፡፡ ስለዚህ ሃይማኖት አለን የምን ከሆነ፣ በሃይማኖታችንም ይህ ድርጊት የተከለከለና ጥፋትን ያስከተለ ከሆነ ግብረሰዶምን የምናከብርበት፣ ድርጊቱንም ሳንቃወም ዝም የምንልበት ምክንያት የለም፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ የሃይማነተኞች ሀገር እንጂ ሃይማኖት አልበኞች የሚፈነጩባት አይደለችም (ይህ ራሱን የቻለ ሌላ አጨቃጫ ርእስ ስለሆነ እንለፈው)፤ ስለዚህ የሃይማኖታችንን ዕሴቶችና ሀገራችንን ለመጠበቅ ስንል ግብረሰዶማዊነትን እንቃወማለን፡፡
በአጠቃላይ ግብረሰዶማዊነት የተፈጥሮ ሕግና ሥርዓትን ስለሚጥስ፣ ማኅበራዊ ዕሤቶቻችን ትርጉም ስለሚያጠፋና ፀረ-ሃይማኖት ድርጊት ስለሆነ በኢትዮጵያም ሆነ በሌላ ሥፍራ እንደሰው መስፋፋቱን ልንቃወመው እንጂ ልንደግፈው ወይም ‹ምን አገባን ብለን› ዝም ልንለው አይገባም፡፡ አሁን የሚሆነው ጥያቄ ‹ግብረሰዶማዊነት ከሰው ልጆች ተፈጥሮ፣ ከማኅበረሰብ ዕሴቶችና ከሃይማኖታዊ ትዛዛት ጋር የማይስማማ ተግባር ከሆነ ለምንና እንዴት በዓለም አቀፍ ደረጃ በኃያላን መንግሥታት ተቀባይነት ሊያገኝና ለታዳጊ ሃገራት ደግሞ የዕርዳታ ለማግኘት እሱ እንደ ቅድመ ሁኔታ ሊወሰድ ቻለ? ኃያላኖቹ መጥፎ ድርጊትን መቃወምና የሚቃወሙትንም መደገፍ ይገባቸዋል እንጂ በተቃራኒው እንዴት ይህን ያደርጋሉ?› በሌላ በኩል ደግሞ የዚህ ተግባር ሱሰኛና ምርኮኛ የሆኑትስ እንዴት ሊሆኑ ቻሉ? ባለማወቅ ነው ወይስ በሌላ ምክንያት? የሚጠቅም ካልሆነስ ለመተው ከመጣር ይልቅ እንዴት ድርጊቱን ለማስፋፋት ይተባበራሉ?የሚሉ ጥያቄዎችመነሣታቸው አይቀርም፡፡
መልሱን ለመስጠትም የግድ መከራከሪያችን ትክክል መሆኑን መመልከትና ምክንያታቸውንም መመርመር ያስፈልጋል፡፡ መከራከሪያዎቻችንም ግልጽ ናቸው፤ የሰውን ልጅ ተፈጥሮ ሥርዓት ይቃወማል ብለናል፤ አለመቃወሙን በተጠየቅ አቅርቦ የሚያሳምነን እስከምናገኝ ድረስ ከላይ እንዳስቀመጥነው ትክክል ስለሆንን ግብረሰዶማዊነት ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፤ በባህርያችን ተወስኖ የተሰጠንን የተፈጥሮ ገደብና ተግባር አልፎ መሄድ ይቻላል ከተባለም፤ መከራከሪያቸው ከሰው ልጅ ስብዕና ውጭ መሆን መቻልን ስለሚገልፅ ከሰውነት ወይም ሰው መኖር ከሚችለው በላይ ሄደው ይኑሩ እንጂ የእኛን መብት አይጻረሩ እንላለን፡፡ ከድርጊቱና ከሚያመጣው ውጤት ተነሥተን ስንገመግመው የምንረዳው ማኅበረሰባዊ ዕሴቶችን ስለሚያጠፋ ግብረሰዶም አደገኛና ጠንቀኛ ተግባር ነው ብለናል፤ ይህንን የሚያፈርስ መከራከሪያ ሲያቀርቡ ደግሞ አይታዩም ይልቁንም ‹ሰው በተሰጠው ገላው እንደፈለገ የመሆንና የማድረግ መብት አለው› ነው የሚሉት፤ ነገር ግን  መታወቅ የሚኖርበት አንደኛ ግብረሰዶማዊነት የአንድ ሰው ድርጊት ብቻ አይደለም፡- ከሌላ ሰው ጋር የሚፈጸም ድርጊት ነው፡- ይህም ወደ ቤተሰባዊነትና ማኅበረሰባዊነት ያድጋል፤ ሁለተኛ መከራከሪያው በአንድ ሰው መብት ተጠግቶ ማኅበረሰብን የመረፍረፍና የማጥፋት ግብ ያለው ይመስላል፤ ነገር ግን አንድ ሰው ያለ ኅብረተሰብ አይፈጠርም፤ ኅብረተሰብና ማኅበረሰብም ያለ ግለሰቦች ድምር አይኖሩም፤ ስለዚህ ግብረሰዶማዊነት ማኅበረሰባዊነትን የሚንድና የሚያጠፋ ከሆነ፤ ማኅበረሰባዊ ኃላፊነት ያለበት ሁሉ በአንድ ሰው መጥፎ ድርጊት እንዳይጠፋ የመጠበቅ ኃላፊነት ይኖርበታል፤ ደግሞስ ድርጊቱን የሚፈጽመው አካል መብት ከተከበረለት ‹ይህ ድርጊት ለእኔ በኅበረተሰቤ፣ በሃይማኖቴና በሥነልቦናዬ ላይ ችግር ይፈጥርብኛል› የሚለው የብዙዎች መብትስ አይታይም ወይ? ኅበረተሰቡ እኮ በግብረሰዶማዊነት ባህል ሳይሆን በተቃራኒው የተገነባ ነው፤ ይህ ከሆነ ግበረሰዶማዊነትን የሚያስፋፋው አካል ለምን የሌላውን ሀብት ለማጥፋት መብት ያገኛል?ሃይሞኖት እኮ የግበረሰዶማዊነት ተቃራኒው እንጂ ተባባሪው አይደለም ታዲያ ለምን ሃይማኖት የገነባውን ማኅበራዊ ተቋም ለማፍረስ ግብረሰዶማዊነት መብት ያገኛል? የማኅብረሰቡ ሥነልቦና ግብረሰዶማዊነት የሚቀፈው ከሆነ እንዴት ግድ ተባበር ተብሎ የማይፈልገው ነገር ይጫንበታል? ስለዚህ ከላይ የጠቀስናቸውን መከራከሪያዎች የሚያፈርስ መከራከሪያ አያቀርቡም፤ ይህ ከሆነም መቃወማችን ትክክል ነው፡፡ ሆኖም ‹ለምን ይህን ያደርጋሉ?› የሚለው ጥያቄ ግን አልተመለሰም፤ ጥያቄውን በአግባቡ ለመመለስም አስቸጋሪ ይመስላል፤ ስለዚህ በመጠርጠር የተመሠረተ መላምት ለመስጠት እንገደዳለን፡፡ እንጠርጥር!
አንደኛው ጥርጣሪያችን ‹በዓለም የተለየ እኛ የማነውቀው የሻጥር (የሤራ) ዕቅድ ይኖራቸው ይሆን?› ብለን ለመጠየቅ ያስገድደናል፡፡ ይህን ስንጠይቅ ደግሞ ከጥርጣሪያችን ጋር የተያያዙ የምሥጢር ማኅበራት ዓላማ፣ ዕቅዳቸውና ዓለም የመቆጣጠሪያ ስልቶቻቸው ለጥርጣሪያችን አጋዥ በመሆን ይመጣሉ፡፡ የምሥጢር ማኅበራቱ ዕቅድና የዓለም መቆጣጠሪያ ስልቶች ውስጥ ደግሞ አንዱ የአንድን ማኅበረሰብ ጠንካራ ዕሴቶች ማፍረስና እነሱ በሚፈልጉት መንገድ ውስጥ ማስገባት ዋናው መሆኑን ስናይና ስንረዳ ጥርጣሪያችን ይጨምራል፤ በተለይ ደግሞ ጠንካራ ዕሴቶችን ለማፍረስ ሃይማኖትን ማረካስና ማጥፋት፣ ከዚያም የራሳቸውን በመተካት በዐዲስ መልክ መገንባት መሆኑን ስንመረምር መጠርጠራችን ትክክል ነው እንላለን፤ ለዚህም ከሚያገለግሉት የዕሴቶች ማፍረሻ መዶሻዎች (ለምሳሌ የሕዝብ ብዛት ቅነሳ፣ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋችነት፣ የሃይማኖት አይጠቅሜነትና ትርጉም አልባነት፣…) መካከል አንዱ ግብረሰዶማዊነት መሆኑን ስንረዳ ‹ታዲያ በግብራቸው እየነገሩን አይደለም ወይ?› ማለታችን ስህተት አይሆንም፡፡ ስህተት የሚሆነው እንዳውም አለመጠርጠራችን ይሆናል፡፡ ያ ካልሆነ ለምን ከሰው ልጆች ስብእና ውጭ ለሆነ ነገር ገንዘብ መድበው፣ ኃይላቸውን ተጠቅመው ጥብቅና ይቆማሉ? እንዳውም እንዲስፋፋና ዓለምን እንዲቆጣጠር በትጋት ቆርጠው ይሠራሉ? ስለዚህ ሻጥር እንዳለባቸው መጠርጠራችን ካለመጠርጠራችን የተሻለ መልስ ነው፡፡ ያ ባይሆን ኖሮ ‹ከግብረሰዶማዊነትና ከአሸባሪነት የትኛው የባሰ መጥፎ ሆኖ ነው አሸባሪነትን በዓለም ላይ ለመቆጣጠርና ለማጥፋ ሌት ተቀን እንሠራለን እያሉ ግብረሰዶማዊነትን ግን በጀት መድበው የሚያስፋፉት?› እናስ ‹የሆነ ሻጥር› እንዳለባቸው መጠርጠራችን አይሻልም፡፡ ባይሆን የጥርጣሬ መከራከሪያችን ካለረካ የግደይ ገ/ኪዳንና የተክሉ አስኳሉን ‹ህልም አጨናጋፊዎቹ› የሚለውን መጽሐፍ መመልከት ወይም ‹ሉላዊ ሤራ› የሚለውን የግደይን ጦማር (ብሎግ) መጎብኘት፤ ተጨማሪ ማስረጃ ይሆኑናል በሚል ጥቁምታ ወደ ሁለተኛው የጥርጣሬ መልሳችን እንለፍ፡፡
ሁለተኛው ጥርጣሬያችን ሊሆን የሚችለው ‹ምናልባት የሠይጣን እጅ ይኖርበት ይሆን እንዴ?› የሚል የሃይማኖታዊ ሰው ፍርሃት ነው፤ ምክንያቱም አንደኛ ‹ግብረ ሰዶማዊነት የሃይማኖት ዕሴቶችን ይቃረናል (ይቃወማል) ባልነው መሠረት፤ ሠይጣን ደግሞ በሃይማኖት ጋር ከሚገናኘው እግዚአብሔር ጋር ፀበኛ ስለሆነና የሰውና የአምላክን ግንኙነት ለመበጠስ ስለማይተኛ በእነዚህ ኃያላን መንግሥታት ላይ አድሮ እየተቆጣጠረ ዓለም እያጠፋ ይሆን ወይ?› የሚል ጥርጣሬ ስለሚያሳድርብን ነው፤ ሁለተኛም ከላይ ከጠቀስናቸው ከምሥጢር ማኅበራት ጋር ተያይዞ ‹ዓለምን በሠይጣን ሃይማኖት ለማስገዛት እንቅስቃሴ አለ፤ ለዚህም የተወሰኑ ሰዎች የዓለምን ተቋማት፣ ሚዲያዎች፣ ትምህርትና ሌሎች ነገሮችን በመቆጣጠር ሠይጣን የሚመለክበት ሥርዓት ተነድፎ ይተገበራል፤ ለዚህም አንዱ የግብረሰዶማዊነት ተግባር ነው› የሚል ሐሜት ስለሰማን እንጠረጥራለን፡፡ እንዲሁም 666 የሚባለው የሠይጣን ምልክትና እሱንም ለማስፋፋት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ስለምንመለከት ጥርጣሬያችን ይጨምራል እንጂ አይቀንስም፡፡ ለጥርጣሬያችን አጋዥ የሆነን ደግሞ የጠቀስናቸው ‹ኃያላን መንግሥታት› የዓለምን ሀብት፣ የጦር አቅምና የዕውቀት አውታር ተቆጣጥርው ‹ይህንን ተግባር ካላስፈጸማችሁ ሽራፊ ሣንቲም ወይ ቅምሽ!› ማለታቸው ነው፤ እና ካለመጠርጠራችን መጠርጠራችን አይሻልም እንደ?
ሦስተኛም በአፍሪካዊነታችንና በጥቁርነታችን የምንጠርጥራቸው ግምቶችም ይኖሩናል፤ ይህም ዝም ብሎ የመጣ አይደለም፤ ይህን ተግባር እንድንቀበል ተጽዕኖ የሚያደርጉብን አካላትና የሚቆጣጠሯቸው፤ አፍሪካን ማዳከምና ጥቁር ሕዝብ እየተርመጠመጠ እርስ በራሱ እየተባላ እንዲኖር፤ በዚህም የሞራል መላሸቅና የስብእና መበላሸት እንዲፈጠርበት እንጂ በራሱ ቀና ብሎ ሞራሉን በመገንባት መበልፀጉን የማይፈልጉ አካላት ያሉባቸው መሆኑን ከታሪክና ከሚታዩ የተጽዕኖ አዝማሚያዎች ስለምንረዳ ነው፡፡ ያ ካልሆነ ለምን በተለየ በአፍሪካ በብድርና በዕርዳታ ስም በማስፈራራት፣ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችም ግብረሰዶምን ለማስፋፋት ዕንቅልፍ አጥተው ይሠራሉ? በተለይ የታላላቅ ፈላስፋዎቻቸው (ዓማኑኤል ካንትንና የሔግልን የመሳሰሉ) የ‹ጥቁር ሙሉ ሰው አይደለም› አስተሳሰብ በአንዳንድ ነጮች ላይ የፈጠረውን ተፅእኖ የሚያስተውል በሞኝነት በባዶ እጁ ‹እሳት እየተጫወተ ተቃጥሎ› ማሰብ አለመቻሉን መመስከር የለበትም፤ ይህ ከሆነም በዚህ መልክም ቢሆን መጠርጠራችን አይከፋም፡፡ ያ ካልሆነ እንዴት ግብረሰዶምን በአፍሪካ ለማስፋፋት በጀት መድበው በማማለል እንቢ ስንል ያስፈራሩናል? ሁልጊዜ ‹የእነሱ የሠገራ ቤት መሆን አለብን እንዴ? › በአጠቃላይ ካለመጠርጠራን መጠርጠራን ሳይሻል አይቀርም በሚል መልሳችን እንዝጋው፡፡ ለዚህም ቢሆን ዶክተር ሥዩም አንቶኒዮስ Africa say no for Homosexuality በሚል ያቀረቡትን ዶክመንተሪ ፊልም ከእንተርኔት ላይ መመልከት ጠቃሚ ይሆናል፡፡
ይህንን በዚህ መልክ ጠርጥረን ብንዘጋም ሌላው ጥያቄ ግን አፍጦ ይጠብቀናል፡- ከላይ የጠየቅነው ‹ለግብረሶዶማዊነት ተግባር ሰለባ የሆኑ ግለሰቦች ጉዳይስ? ለምን ግብራቸውን ከመተው ይልቅ ለማስፋፋት ይጥራሉ? ያለማወቅ ነው ወይስ ሌላ ምክንያት አላቸው?› የሚሉት ጥያቄዎች መልስ አምጡ ማለታቸው አይቀርም፡፡ ማለትም ‹ግብረሰዶማዊነት ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ጋር የማይስማማ ከሆነ፣ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ሰዎች እንዴት ተስማምቷቸው ድርጊቱን ከመተውና መጥፎነቱን ከማስረዳት ይልቅ ተግባሩ እንዲስፋፋ ምክንያት ይሆናሉ?› መባሉ የማይቀር ነው፤ መልሱም አስቸጋሪነት ይታይበታል፡፡ በግብረሰዶም መጥፎ ግብርነትና ለሰው ተፈጥሯዊ ባህርይ ተቃራኒ በመሆኑ ከተስማማን ግብሩን መተው አለባቸው ማለታችን ትክክል ይሆናል፤ ከሰውነት ውጭ የሆነ ሥራን መሥራት መልካም አይደለምና፡፡ ለመተው እንዲችሉም ይህንን ተግባር እንዳይተው ምክንያት የሆኗቸው፣ እንዳውም ድርጊቱን እንደመልካም ነገር ለማስፋፋትና ተቀባይነት እንዲያገኝ መሥዋዕትነት ለመክፈል የሚጥሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ምክንያት ከሚመስሉን መካከል ማሰያ የሚሆኑ ነጥቦችን እንጥቀስ፡፡
አንደኛ እነዚህ ሰዎች ወደውት በመፈለግ የገቡበት ተግባር አይደለም፤ አንድም ሳያውቁ በመታለል፣ በመደፈር፣ በገንዘብና በተለያዩ ምክንያቶች በመደለል ነገሩን ለጊዘው ብንፈጽም ምንም አይደል በሚል ሞኝነት ጀምረውት ከዚያም እንደልማድ ስለሆነባቸው ነው ለዚህ የበቁት፤ ከዚያም ተለማምደውት መልካም ተግባር መስሎ እስከመታየት አድርሷቸዋል፤ አስከፊነቱና የሚያመጣው ተጽዕኖ አልተገለጠላቸውም፡፡ ስለዚህ እንደሌላው ወይም እንደተቃራኒ ጾታ ግንኙነት መስሎ ስለሚሰማቸው የሚያመጣው አስከፊ ገፅታ አልተስተዋላቸውም፤ እንዳውም ‹ከአፈርኩ አይመልሰኝ› በማለት መብታቸው እንደሆነ እስከመቁጠር ደርሰዋል፤ ሌሎችም ሲያጣጥሏቸው ‹መብታችን› በሚለው ሰበብ እራሳቸውን ለመከላከል ይጥራሉ፤ አዕምሯቸው እንደሚወቅሳቸው ግን ከተሠሩ አንዳንድ ‹ዶክመንተሪ› ሥራዎች መረዳት ይቻላል፡፡
ሌላው ምክንያት ሊሆን የሚችለው ሰለባ የሚያደርጓቸው አካላት ተፅዕኖ ይሆናል የሚል ጥርጣሬ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ አካላት ይህንን ተግባር ለማስፋፋት በገንዘብና በሌሎች መሣሪያዎች ተፅእኖ ያደርጋሉ ካልን እጃቸውን በእነዚህ በተጠቂ ሰዎች ጀርባ ደብቀው ተግባሩ እንዲበረታታና እንዲስፋፋ አያፋፍሙም ማለት አይቻልም፡፡ ለምሳሌ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነን ስለሚሉ እንሱ የሚያራምዱት ነገር ሁሉ መልካም ሊመስላቸው ይችላል፡- የተለከፉት ሰዎች፤ በዚህ የተነሣ ‹ማንኛውም ሰው በገላው እንደፈለገው ማዘዝና መሆን ይችላል› የሚለው ስብከት ችግር የሌለበትና አግባባዊ መከራከሪያ ሊመስላቸው ይችላል፤ ይህም ማለት እነሱ ሱስ የሆነባቸውን ነገር መፈጸማቸውን እንጂ ከዚያ ጋር ተያይዞ የሚመጠው ችግር አይገለጽላቸውም፡፡ እንዲሁም ከዘመኑ የአኗኗር ሁኔታና ተፅእኖ አንጻር ለመኖር የሚያስፈልጋቸውን በእነሱ በኩል የሚያገኙበትን መንገድ ስለሚያመቻቹላቸው፤ መጥፎ መሆኑን ቢያውቁና ተግባራቸው ቢያስዝናቸውም ኑሮን ለማሸነፍ ሲሉ በእንደዚህ ዓይነት ተግባር ውስጥ ሊሠማሩ ይችላሉ፤ ይህንን ከሴተኛ አዳሪዎች ሕይወት ጋር አያይዞም መገንዘብ መልካም ነው፡፡ እንዲሁም ተጽዕኖ የሚያደርጉ አካላት እጃቸው ሰፊና መረባቸው ብዙ ነው፤ በመሆኑም ሚዲያውን ተቆጣጥረው፣ ምሁራንን ተጠቅመው የሚያደርጉት ስብከት ‹ጥቁሩን ነጭ ነው፤ ነጭንም ጥቁር ነው› በማለት የማሳመን ኃይል አለው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሰዎችንም ሰለባቸው ካደረጓቸው በኋላ በተለያየ ስልት በመጠቀም ተግባሩን እንዲስያስፋፉ ያድርጋሉ እንጂ በቀላሉ አይተዋቸውም፤ እንዲሁም በሠለጠኑ ሀገራት የተግባሩን መፈጸም እንደ ጀብዱ አድርገው በመውሰድና ያንንም በማራገብ ‹እነሱ ይህንን የሚያደርጉት ችግር ባይኖርበት ነው› የሚል አስተሳሰብ በውስጣቸው እንዲሰርፅ አድርገው የቀረጽዋቸው ይመስላሉ፡፡ በአጠቃላይ የግብረሶዶም ተጠቂ የሆኑ ሰዎች ብዙ ተጽዕኖዎች እንደሚኖሩባቸው ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡
እነዲሁም ግብረሰዶማዊነት ሠይጣናዊ የሆነ ልክፍት አይኖርበትም በማለት መደምደም አይቻልም፤ ከላይ ‹ግብረሶዶምን በዓለም ላይ እንዲስፋፋ እያደረገው ያለው ሠይጣን ነው› ባልነው መሠረት፤ ድርጊቱን በማስፋፋት ሥራ ሠይጣን እጁ አለበት ማለት ነው፤ ይህ ከሆነም ‹በእዚህ ተግባር የተጠቁ ሰዎች በሱሰኝነት ተግባር እንዲጠሙዱና አገልጋዮቹ እንዲሆኑት አያደርጋቸውም› ልንል አንችልም፤ ይህ ከሆነም እነዚህ ሰዎች ከአቅማቸው በላይ የሆነ አካል (ዐውቀውም ይሁን ሳያውቁት) ስለሚቆጣጠራቸውና ከእግዚአብሔር ስለሚለያቸው እሱን ለማስደሰትና የሰው ልጆችን ለማጥፋት ይሠራሉ ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ደግሞ ከመንፈሳዊ አስተምህሮ አንጻር ከተመለከትነው አበው ሰባቱ ዐበይት ሐጢያት ከሚሏቸው አንዱ የ‹ግብረሰዶም መስፋፋት› ነውና በትንቢት መልክ የተገለፀው በእውን እየተተገበረ መሆኑን ይመሰክራል፤ ይህም ምን ያህል አስቸጋሪ ወቅት ላይ እንደሆንን ያስረዳናል፡፡ የሠይጣን ሥራን ደግሞ መቃወም ግድ ይለናል (ሰዎቹን አይደለም ተግባሩን ነው ያልኩት)፤ ሠይጣን እንደመሣሪያ የሚጠቀምበት ግብረሰዶማዊነት የመልካም ነገርና የሰው ልጆች ጠላት ነውና፡፡
በአጠቃላይ የዚህ ድርጊት አራማጆቸ  ወደውም ይሁን ሳይወዱ ከላይ በጠቀስናቸው ምክንያቶች የተነሣ ተግባሩን እንደሱስ ለምደውት ሊያስፋፉት ይችላሉ፤ በተጽእኖ የተነሣም የድርጊቱ ተባባሪና ፈጻሚ ሆነው ሊሆን ይችላል፤ በሠይጣን ልክፍትና ቁጥጥርም የድርጊቱ አከናዋኝ ለመሆን ተገደው ይሆናል ወይም ሌሎች ችግሮችም (ምክንያቶችም) ሊኖሯቸው ይችላሉ፡፡ በማንኛውም ምክንያት ያከናወኑት ምንም ዓይነት ችግር ይኑርባቸው ድርጊቱን ማስፋፋታቸው አደገኛ መሆኑን ግን ዐሌ ማለት አይቻልም፤ ምክንያቱም ግብረሰዶማዊነት መጥፎ ድርጊትና የስብዕና ተቃራኒ ተግባር ነውና፡፡ ስለዚህ የችግር መዓት መደርደራችንን ትተን፤ ተጠቂዎቹን መውቀሳችንን አቀዝቅዘን ‹‰ረ! ምን ይሻላል?› ማለት ይኖርብናል፤ ዋናው ቁም ነገር ችግሩን ማስወገዱ እንጂ በችግሩ ላይ ማለዛን አይደለም፡፡ እናም ‹ለዚህ ችግር መፍትሔው ምንድን ነው?› ብለን መጠየቅ ግድ ይለናል፤ መፍትሔው ደግሞ ከችግሩ እንደሚነሳ ግልፅ ነው፡፡
ከችግሩ በመነሣት ልብ ብለን ካስተዋልነው የ‹ግብረሰዶማዊነት ወረራ› ከቅኝ ግዛት ይበሳል እንጂ የተሻለ አይደለም፤ ምክንያቱም ሀገርን ወሮ በመንጠቅ ብቻ የሚመለስ አይደለም ይልቁንም የትውልድን መንፈስ መጦ በማውጣት የሰው ልጅን ማንነትና የትውልድን ቀጣይነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው፡፡ ስለዚህ ‹ሳይቃጠል በቅጠል!› ማለት እዚህ ላይ ነው፤ ትውልዱን ለመጠበቅ፣ ሀገርን ከዚህ ጥፋት ለመታደግም ‹ጦርነት› ሊታወጅበት ይገባል፤ ያለበለዚያ ችግሩ ተቆጣጥሮን ልጆች እንዳያሳጣን፣ በሀገራችን ተንሠራፍቶ መንቀሻቀሻ እንዳናጣ ያሰጋል፤ ለዚህ ለዚህማ የመውለድ ትርጉሙስ ምን ሊሆን ነው? ስለዚህ ግብረሰዶማውነትን እንደቀላል ነገር እንዳናየው፤ ‹ልጆቻችንን አስጨርሰንም› በጸጸት እያለቀስን እንዳንሞት ከአሁኑ ማጤን ይኖርብናል፡፡
እንደሰማሁነት ከሆነ ግብረሰዶማውያ በሀገራችን የሕግ ድጋፍ እንዲሠጣቸውም ጠይቀዋል ይባላል፤ ለምሳሌ የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ ላይ ‹ጋብቻ ሁለት ወንድና ሴት የሆኑ ሰዎች በፈቃደኝነት የሚፈጽሙት ተግባር ነው› (በቀጥታ የተጠቀሰ አይደለም) የሚለውን አንቀጽ ‹ሁለት ሰዎች በፈቃደኝነት ሚፈጽሙት ተግባር ነው› በሚል ይስተካከል ብለው ጠይቀዋል ተብሏል፤ ይህም ምን ያህል ስልታዊ እንደሆኑ ያሳየናል፡፡ ስለዚህ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ በሕግ ማዕቀፍ ተደግፈው በአደባባይ ወጥተው እንዳይቆጣጠሩን እያንዳንዷን እንቅስቃሴቻውን ቢቻል እንዳያከናውኑ ማድረግ፤ ከልተቻለም ተቃውመን ለማስቀረት መሞከር ይኖርብናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ጓደኛየ ስለዚህ ጉዳይ ስናወራ ስጋቱን ሲገልጽልኝ ‹ከዐሥር ዓመት በኋላ በሕገ-መንግሥት የተደገፈ መብት እንዳይኖራው ያሰጋል› ብሎኛል፤ ስጋቱ እንደማይደርስ ማረጋገጫ የለንም፡፡ ስለዚህ በሕግ ተደግፈው እንዳይቆጣጠሩን አስፈላጊውን ጥንቃቄና ክትትል ማድረግ ያስፈልገናል፤ በተለይ ደግሞ የመንግሥት ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ጉዳዩ በቀላሉ የመብት መጠበቅና የዕርዳታ ማግኛ ስልት አድርገው በንዝህላልነት እንዳያሰወሩሩን መጠንቀቅ አለባቸው፡፡
በግልፅም ይሁን በስውር በዕርዳታና በመያዶች ስም የሚከናወኑ ተግባራትንም ማየት ያስፈልጋል፤ በተለይ በሀገራችን ግብረሰዶማዊነት የሚስፋፋው አንድም በዕርዳታና በብድር ስም ገንዘብ ለማግኘት ሲባል በሚፈጠር ተፅዕኖ ነው፤ ሌላም በትምህርትና በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር ውጭ ወጥተው የሚመለሱ ሰዎች የድርጊቱ ሰለባ ሆነው ስለሚመጡ በሱስኝነት ድርጊቱን ስለሚቀጥሉበት ነው፤ አንድም ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር ተያይዞ በመመሳሰል በሚፈጠር የማታለልና ተመሳሳይ ጾታን የመድፈር፣ የማስለመድና የማስፋፋት እንቀስቃሴ ነው፤ ወይም ለዚህ ድርጊት ማስፋፊያ በጀት የመደቡ አካላት በሚነድፉት የውስጥ ለውስጥ እንቅስቃሴ ይሆናል፡፡ በየትኛውም ይሁን ወይም ሌላ መንገድ ይኑራቸው የእኛ ዋናው ጥያቄ ‹እንዴት እንቆጣጠረው?› የሚል ነው መሆን ያለበት፤ በተለይ ደግሞ የሀገራችን ድህነት በመጠቀም ዕርዳታ እንስጣችሁ በሚል ሰበብ መያዶችን እያደራጁ ለቀውብናል ወደፊት ይብሳል እንጂ መቀነሱ ያጠራጥራል፤ በዕርዳታና በብድር ስምም መንግሥትን አፉን ሊዘጉት ይሞክራሉ እንጂ ዝም አይሉም፤ ከአሁን በፊትም ይህንን እንዳደረጉ ባለፈው የሃይማኖት አባቶች ለመቃወም ሊያደርጉ የነበረውን ስብሰባ በማገድ ተንፀባርቋል፡፡ ስለዚህ ‹በእዚህ በኩል ያሉትን የማነቂያ ስልቶች እንዴት ልንቋቋማቸው እንችላለን?› ብለን ራሳችንን መጠየቅ ግድ ይለናል፤ በዚህ በኩል የሚመጡ ዕርዳታዎችንና የብድር መደራደሪያዎችን ‹በአፍንጫችን ይውጣ!› ብለን መቃወም ይኖርብናል፡፡ ለዚህ የዚህ ጉዳይ አሳሳቢነት የሚሰማቸው የመንግሥት ኃላፊዎች ያስፈልጉናል፤ ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የመንግሥት ኃላፊዎች ያላቸው ጠንካራ አቋም ወሳኝ ይሆናል፡፡
ሌላውና ዋናው የችግሩን አሳሳቢነትና በሀገራችን የሚያመጣውን ችግር በመነጋገርና በመከራከር ለኅበረተሰባችን ማሳወቅ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ይሆናል፡፡ በዚህ ሐሳብ ላይ በአግባቡ ከተሔደበት ኅበረተሰባችን ግብረሰዶማዊነትን ቀድሞውንም የሚጠየፈው ተግባር ስለሆነ በቀላሉ የዚህን ተግባር መስፋፋት ለመቆጣጠርና ሰለባ የሆኑትንም በተለያየ መንገድ ተንቀሳቅሶ መመለስ ይቻላል፡፡ ለዚህ ደግሞ የሃይማኖት ተቋማትም ሆኑ የተለያዩ ኃላፊዎነት የሚሰማቸው መንግሥታዊም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ድርጅቶች ትልቅ ሚና መጫዎት ይችላሉ፤ መገናኛ ብዙሃንም ትልቅ ኃላፊነትን በመውሰድ ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ምክንያቱም ችግሩ ሁሉን የሚመለከት፣ ሀገራችን ይዛቸው የኖረቻቸውን ዕሴቶች ትርጉም የሚያሳጣ ኃይልና አዝማሚያ ያለው ነውና፤ የሀገራችንና የማኅበረሰባችንን ዕሴቶች ደግሞ የመጠበቅና የማስቀጠል ኃላፊነት የሁሉም አካላት ድርሻ መሆን ይኖርበታል፤ ችግሩን ለማስወገድ መረባረብ አለባቸው፤ ሁላችንም እንደዚሁ በግልም ሆነ በኅብረት ጉዳዩ ይመለከተናል ብለን ማኅበረሰባችንም ለመታደግ መሥራት ይኖርብናል፡፡
ለማንኛውም ከእንስሳት ብቻ አይደለም ከእጽዋትም ከሚያሳንስ ከዚህ ከግብረሰዶማዊነት ተግባር ፈጣሪ ይጠብቀን! አሜን!
Source: http://kassahunalemu.wordpress.com/
 

በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የሰፈረው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል!

-መንግሥት አካውንታቸው ተጠልፏል እያለ ነው::
የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በትዊተር ማኅበራዊ ገጻቸው ላይ፣ ‹‹በተወዳጇ አፍሪካዬ ውስጥ ጥላቻና መገለል ቦታ የላቸውም፡፡
የአለባበስ ሥርዓት ወይም የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም፤›› በሚል የወጣው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ መንግሥት ግን የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን ገልጾ፣ ይህ መልዕክት የሚኒስትሯንም ሆነ የመንግሥትን አቋም አይወክልም ሲል አስተባብሏል፡፡ 

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኡጋንዳ የፀደቀውን ፀረ ግብረ ሰዶማዊያን ሕግ በመቃወም በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የተጻፈው ይህ መልዕክት፣ በዓለም ዙሪያ ባሉ የግብረሰዶማዊ መብቶች አቀንቃኞች አድናቆት ተችሮታል፡፡ ሆኖም ግን የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዓብይ ኤፍሬም፣ ‹‹መልዕክቱ በማይታወቁ ሰዎች የተጻፈ ሲሆን፣ የእሳቸውንም ሆነ የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ ነው፤›› ብለዋል፡፡ 
አቶ ዓብይ አክለው፣ ‹‹ሚኒስትሯ ይህን የማኅበረሰብ ሚዲያ የሚጠቀሙት ሕዝቡ በቀጥታ ሊያገኛቸው የሚገቡ መልዕክቶችን ለማስተላለፍ አዋጭ ሚዲያ በመሆኑ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የትዊተር ገጻቸውን የሚያንቀሳቅሱት ራሳቸው ወይዘሮ ዘነቡ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዓብይ፣ በገጻቸው ላይ በጠላፊዎች በተላለፈው መልዕክት ሚኒስትሯ ማዘናቸውን አስረድተዋል፡፡ 
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን አረጋግጠው፣ ‹‹የሚኒስትሯን አካውንት ጠልፈው በመግባት የእሳቸውንና የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ
መልዕክት ያስተላለፉት ግለሰቦች ጉዳይ ከተጣራ በኋላ፣ አስፈላጊው ዕርምጃ ይወሰዳል፤›› ብለዋል፡፡
የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መቼ እንደተጠለፈ በውል ባይታወቅም፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን ግብረ ሰዶማዊያን እኩል መብት ይኑራቸው የሚል መልዕክታቸው፣ ጥር 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በአካውንታቸው በድጋሚ ትዊት ተደርጓል፡፡ ሚኒስትሯ በዚህ የትዊተር ገጻቸው የተላለፉት መልዕክቶች በእሳቸው እንዳልተጻፉ ገልጸዋል፡፡ 
በአገሪቱ የተሻሻለው የወንጀል ሕግ ከአንቀጽ 629 እስከ 631 ድረስ በሰፈረው መሠረት የግብረ ሰዶም ወንጀል አሥራ አምስት ዓመት ድረስ በእስራት ያስቀጣል፡፡   
ሚኒስትሯን በትዊተር ገጽ ላይ የሚከተሏቸው 1,600 ሰዎች የነበሩ ሲሆን፣ ማክሰኞ ምሽት ላይ ይህ ቁጥር 1,837 ደርሶ ነበር፡፡ እሳቸው ደግሞ የሚከተሏቸው 99 አካውንቶች ሲኖሩ፣ እስከ ማክሰኞ ምሽት ድረስ 672 የትዊተር መልዕክቶችን በገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡ 
 Source: Reporter
በዩጋንዳ ትናንት ጀምሮ ግብረ ሰዶማዊነት የሚቃወም ህግ ተደንግጓል ። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዩጋንዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግብረ ሰዶማዊነትን በመቃወም ባለፈው ታህሳስ ያሳለፈውን ህግ ትናንት በፊርማቸው አፅደድቀዋል ። ህጉ የፀደቀው በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ግብረሰዶማዊነትን በሚቃወሙ ወገኖች መካከል ለዓመታት ከተካሄደ ትግል በኋላ ነው ። በአዲሱ ህግ የሰዶማዊነት ተግባር በእድሜ ልክ እሥራት ያስቀጣል ። አዲሱ ህግ ከመፅደቁ በፊት ብዙ ጊዜ ወስዷል ።
እጎአ በ2009 ነበር ግብረ ሰዶማዊነትን የሚቃወም ረቂቅ ህግ ለዩጋንዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ። የያኔው ረቂቅ ህግ በተደጋጋሚ የግብረ ሰዶም ተግባር ሲፈፅም በተገኘ ሰው ላይ እስከ ሞት ቅጣት የሚደርስ ብይን እንዲተላለፍ የሚደነግግ ነበር ። ይህም በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ ። በመጨረሻም መቀመጫውን ካምፓላ ያደረገው የሃገሪቱ ፓርላማ ባለፈው ታህሳስ ቅጣቱን ወደ እድሜ ልክ እስራት ዝቅ ያደረገውን ህግ አሳለፈ ። ዩጋንዳ በብሪታኒያ
ቅኝ አገዛዝ ሥር ከነበረችበት ጊዜ አንስቶ በወንጀለኛ መቅጫ ደንብ ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያስቀጣ አንቀፅ ሰፍሮ ይገኛል ። የአሁኑ ህግ ግን ከዚያም በላይ የጠነከረ ነው ። የግብረ ሰዶማውያንን ጥቅሞች የሚያስጠብቁ ወይም ግብረ ሰዶማዊ ባህርይ ያላቸውን ሰዎች የማያጋልጡም በእስራት ሊቀጡ ይችላሉ ። የስደተኞች ህግ ፕሮጀክት የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ባልደረባ ለሆኑት ለሲራንዳ ጀራልድ ብላክስ ይህ አስደንጋጭ መልዕክት ነው ።
«ይህ ረቂቅ እጆችን በሙሉ የሚያስር ነው ። ህጉ ሁላችንንም ችግር ውስጥ ይከታል ። ከግብረ ሰዶማውያን የሚሠሩ ወይም የሚኖሩ ቤት አከራይም ይሁኑ አለያም ሃኪሞች ብቻ እነዚህን ሰዎች የሚያውቁ ለፖሊስ የማመልከት ግዴታ አለባቸው ። ያን ካላደረግን ልንታሰር እንችላለን ። »
ሙሴቬኒ ህጉን ወዲያውኑ አላፀደቁም ከዚያ በፊት ሳይንሳዊ ምክር እንደሚፈልጉ አሳወቁ ። አጋጣሚውን በመጠቀም የዩጋንዳ የህግ ባለሞያዎችና የመበት ተሟጋቾች ረቂቅ ህጉ አድሎአዊና ኢህገመንግሥታዊ ነው ሲሉ ስጋታቸው ለፕሬዝዳንቱ ገለፁ ። ዓለም ዓቀፍ ሃኪሞች ችግሩን በማሳወቅ ለፕሬዝዳንቱ ደብዳቤ ሲፅፉ ከ60 በላይ የሚሆኑ ድርጅቶች ተወካዮችም ህጉ የሚያስከትላቸውን መዘዞች በመዘርዘር አሳወቁ ።እነዚህ ወገኖች ከሁሉ በላይ ግብረ ሰዶማውያን ህክምና ከተነፈጋቸው HIV ኤድስን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ላይ ተፅእኖ ያሳድራል የሚል ስጋት አላቸው ። በዚህ ኦመት መጀመሪያ ላይ የናይጀሪያው ፕሬዝዳንት ጉዳድላክ ጆናታን ሰዶማዊነትን የሚቃወም ህግ በፊርማቸው ካፀደቁ ወዲህ ሙሴቬኒ በዚህ የተደፋፈሩ አስመስሏቸዋል ። የጠበቀ የክርስትና እምነት ያላቸው ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ራሳቸው ከሳይንቲስቶች ከሃኪሞችና ከፖለቲከኞች የመለመሏቸው 11 ሰዎች የሚገኙበት ኮሚሽን የግብረ ሰዶማዊውያንን ተፈጥሮ አጥንቶ የሚያቀርበውን ውጤት በመጠባበቅ ላይ ናቸው ። በመሃሉ ግን የካቲት 3 ቀን 2006 ሃላፊነት ያለበት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ውጤቱን በማቅረብ ሳይንሳዊ የተባለ አቋም ወስዷል ። በዚህ ውጤት መሠረት ግብረሰዶማዊነት ተጨባጭ በሆነ ዘረ መል የሚከሰት በሽታ እንዳልሆነ ገልጿል ። አሁንም ቢሆን ተጨማሪ ምርምር ያስፈልጋል ። ኮሚሽኑ ግን እስካሁን በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨባጭ የሆነ ምክር አልሰጠም ። ይሄ ዜና የደረሰው የሙሴቬኒ ፓርቲ አብይ ጉባኤ ላይ ነበር ። በዚያኑ እለትም የ69 ዓመቱ ሙሴቬኒ ለ2016 ምርጫ ራሳቸውን በእጩ ተወዳዳሪነት አቅርበዋል ።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የደረሰበትን ውሳኔ ፕሬዝዳንቱ ተቀብለው ሆኖም ግብረሰዶማዊነት በተፈጥሮ የሚወረስ ሳይሆን ከመጥፎ ማህበራዊ መስተጋብር የሚመጣ ነው የሚል ውሳኔ ላይ ደርሰዋል ። ታዛቢዎች የፕሬዝዳንቱን ውሳኔ ሥልጣን ለመቆየት የተጠቀሙበት ስልት ነው ሲሉ ተችተዋል ። ከጀርመን የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት አንድሪያ ኬምፕፍ
«ይህን ናይጀሪያን በመሳሰሉ ሌሎች አገራትም የምንታዘበው ነው ። ከልምድ እንደምገነዘበው ይህ ከምርጫ ጋር የተያያዘ ነው ። እጎአ በ2009 ህጉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ በ2011 ምርጫው ተካሄደ ።»
ሙሴቬኒ በግብረ ሰዶማውያን ላይ የወሰዱት እርምጃ ከዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ በኩል ጠንካራ ትችት አስከትሏል ። የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ እርምጃው ዩጋንዳ ለሚገኙ ግብረ ሰዶማውያን አደጋ መሆኑን ለኡጋንዳውያንም ወደ ኃላ እንደመጓዝ የሚታይ እንደሆነ ተናግረዋል ። የጀርመን መንግሥት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ክሪስቶፍ ሽትራሰር ደግሞ ውሳኔው እንዳስደነገጣቸው አስታውቀዋል ። ከ54 ቱ የአፍሪቃ ሃገራት በ38 ቱ ግብረሰዶማዊነትን በህግ ያስቀጣል ። ከመካከላቸው በሞሪቴንያ በሱዳንና ሶማሊያ በሞት የሚያስቀጣ ድርጊት ነው ።
 Source: www.dw.de

በቦሌ ዋናው መንገድ ከሚሊኒየም አዳራሸ ማዶ በሚገኘው የሕብረት ባንክ አክሲዮን ማኅበር ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማራው ወጣት፣ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እየተናገረ ለጥበቃ በያዘው ጠመንጃ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ ራሱን አጠፋ፡፡
ወጣቱ የጥበቃ ሠራተኛ በሱፈቃድ በጋሻው በኪሱ ውስጥ ከተገኙት የተለያዩ መታወቂያዎች መረዳት እንደተቻለው፣ አጋር የጥበቃ ሠራተኞች ማሠልጠኛ ተቋም ተቀጣሪ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጅ ተማሪ መሆኑን በሚገልጸው መታወቂያ ላይ እንደሠፈረው ከሆነ፣ በ1982 ዓ.ም. የተወለደና የ24 ዓመት ወጣት ነው፡፡ በምን ምክንያት ከፖሊስ ባልደረባነት እንደለቀቀ ባይታወቅም፣ የ13ኛ ኮርስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባል እንደነበር በቅርብ ከሚያውቁት ወዳጆቹ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በባንኩ አሠራር አንድ የጥበቃ አባል 24 ሰዓት ሠርቶ 24 ሰዓታት የሚያርፍ በመሆኑ፣ ሟች በሱፈቃድም የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት አዳሪ ጓደኛውን ከቀየረ በኋላ፣ ባንኩን ለመጠበቅ የቻለው ለ24 ሰዓታት ሳይሆን ለሰባት ሰዓታት ብቻ ነው፡፡ ወጣቱ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እያማረረ እያለ በመሀል የያዘውን ጠመንጃ ቃታ በመሳብ አንድ ጊዜ ወደ ላይ ሲተኩስ፣ አብረውት የነበሩ ሴት ፈታሽና ሌሎች የባንኩ ተጠቃሚዎች በመደናገጥ ወደ ውስጥና ወደ ውጭ ሽሽት ይጀምራሉ፡፡ ሁለተኛውን ጥይት በመተኮስ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ በኩል በፍጥነት መራመድ መቀጠሉን በሥፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ 
ሦስተኛውን ጥይት ወደ ላይ ከተኮሰ በኋላ አራተኛውን አንገቱ
ሥር በመደገን ተኩሶ፣ ራሱን ማጥፋቱን የዓይን እማኞቹ አስረድተዋል፡፡
ሟች በሱፈቃድ ተወልዶ ያደገው በጉለሌ አካባቢ እንደሆነ፣ አሁንም ከቤተሰቡ ጋር እየኖረ እንደሚገኝ፣ ጊዜውን ባይጠቅሰውም በተወለደበት አካባቢ ነዳጅ የጫነ ተሳቢ ፍሬን ተበጥሶ ከሞት ማምለጡን፣ መሞት ካለበት ደግሞ ራሱን በራሱ ማጥፋት እንዳለበት መወሰኑን የሚገልጽ ደብዳቤ ጽፎ በኪሱ መገኘቱም ተሰምቷል፡፡
Source: Reporter
 
ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደንበኞች ቀንን በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ባከበረበት ወቅት፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም በመቶዎች ለሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ደንበኞች አየር መንገዱ ስለደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዝርዝር ማብራሪያ ሲሰጡ ነበር፡፡
የአገር ባህል ልብስ ለብሰው ፈገግታ ሳይለያቸው የአየር መንገዱን ስኬት ሲያስረዱ ‹‹ዋካ ዋካ›› በሚለው በሻኪራ ተወዳጅ ዜማ ታጅበው ነበር፡፡ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪና የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት አብዱሰላም አቡበከር፣ ታዋቂ ባለሀብቶችና ዲፕሎማቶች በተገኙበት በዚህ ደማቅ ሥነ ሥርዓት ላይ አቶ ተወልደ የአየር መንገዱን ስኬት በኩራት አስረድተዋል፡፡

በእርግጥም አየር መንገዱ ባለፉት አምስት ዓመታት በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር 79 አድርሷል፡፡ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ደግሞ ወደ 63 አሳድጓል፡፡ እጅግ ዘመናዊ የሚባለውን ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን እጁ በማስገባት ከአፍሪካ አንደኛ፣ ከዓለም ሦስተኛው አየር መንገድ ለመሆን በቅቷል፡፡ ገቢውን በሰባት እጥፍ በማሳደግ 2.1 ቢሊዮን ዶላር አድርሷል፡፡
የዚያን ዕለት በአየር መንገዱ ስኬት ሲፍነከነኩ የነበሩትን አቶ ተወልደን ለተመለከታቸው ሰው፣ ከአንድ ቀን በኋላ አስደንጋጭ ዜና ይነገራቸዋል ብሎ በፍፁም ሊያስብ አይችልም ነበር፡፡ የሆነው ግን እንደዚያ ነው፡፡
እሑድ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ሌሊት ለሰኞ አጥቢያ 202 መንገደኞችንና የአውሮፕላኑን ሠራተኞች አሳፍሮ ከአዲስ አበባ
ወደ ሮም ይጓዝ የነበረው ቦይንግ 767-300 አውሮፕላን፣ ከአንድ ሰዓት በረራ በኋላ የሱዳን አየር ክልል ውስጥ እንደገባ በረዳት አብራሪው ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ተጠልፎ ወደ ጄኔቭ ስዊዘርላንድ እንዲጓዝ ተደረገ፡፡ ዋና አብራሪው ጣሊያናዊው ካፒቴን ፓትሪዚዮ ባርቤሪ ወደ መፀዳጃ ቤት ሲሄዱ ጠብቆ የበረራ መቆጣጠሪያ ክፍሉን በር ከውስጥ ቆልፎ አውሮፕላኑን በቁጥጥሩ ሥር ያደረገው ኃይለመድኅን (ቤተሰቦቹ ታዴ ብለው ነው የሚጠሩት) አውሮፕላኑን በጄኔቭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም አሳርፎ እጁን ለስዊዘርላንድ ፖሊስ ሰጥቷል፡፡
ኃይለመድኅን በአገሩ የመኖር ዋስትና እንዳጣ በመግለጽ የስዊዘርላንድ መንግሥት ጥገኝነት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡ ፖሊስ በኃይለመድኅን ላይ ምርመራ በማካሄድ ላይ ሲሆን፣ የስዊዘርላንድ መንግሥት ጠበቃ አቁሞለታል፡፡ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሁሌም የአውሮፕላን ጠለፋ በውጭ ሰው የሚከናወን በመሆኑ የኃይለመድኅን የበረራ ቁጥር ‹‹ET 702›› በረዳት አብራሪው መጠለፉ አስገራሚ አድርጐታል፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ በመላው ዓለም የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ ድርጊቱ የጤና ነው ወይ የሚል ጥያቄም አስነስቷል፡፡ በረዳት አብራሪው የአዕምሮ ጤንነት ላይ ጥያቄ መሰንዘር ተጀምሯል፡፡ 
የኃይለመድኅን ታናሽ እህት ትንሳኤ አበራ በፌስቡክ ገጿ ላይ ባስነበበችው ጽሑፍ ወንድሟ መጠነኛ የሆነ የአዕምሮ መታወክ ገጥሞት እንደነበር ይፋ አድርጋለች፡፡ ከቤተሰብና ጓደኞቹ ራሱን ማግለል፣ ሊያጠቁት የፈለጉ ማንነታቸው የማይታወቅ ሰዎች እንደሚከታተሉት በማሰብ በሥጋት መኖር፣ ወንድሟ ካሳያቸው የተለዩ ባህሪያት መካከል ይገኙበታል፡፡ ኃይለመድኅን እርሱ በሌለበት ቤቱ እንደሚበረበር በማሰብ በቤቱ ውስጥ የቅኝት ካሜራ እስከመስቀል እንደደረሰ ትንሳኤ ተርካለች፡፡ ከሪፖርተር ጋር ቃለ ምምልስ ያደረጉት ታላቅ ወንድማቸው ዶ/ር እንዳላማው አበራ ወንድማቸው የአዕምሮ ጤንነት ችግር ገጥሞታል ብለው እንደሚጠረጥሩና እህቶቹ ኃይለመድኅን የሥነ አዕምሮ ሐኪም ዘንድ እንዲሄድ እንደመከሩት ተናግረዋል፡፡
የኃይለመድኅን ጐረቤቶች በበኩላቸው ዘወትር ብቻውን የሚታይ፣ ዝምተኛና ሰላምተኛ ሰው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ኃይለመድኅን የሚኖረው ኢምፔሪያል ሆቴል አካባቢ ሳሚ ሕንፃ ጀርባ ከሚገኘው ኮንዶሚኒየም ብሎክ ሰባት በመጀመሪያ ፎቅ ከሚገኝ ባለ አንድ መኝታ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ጠለፋው ከተፈጸመ በኋላ ቤቱ በፖሊስ የተፈተሸ ሲሆን፣ አሁንም ድረስ በፌዴራል ፖሊስ አባላት የሚጠበቅ በመሆኑ ማንም ወደ ቤቱ ውስጥ መግባት አይፈቀድለትም፡፡ ከመርማሪ ፖሊሶች በስተቀር፡፡
የኮንዶሚኒየሙ አንድ የጥበቃ አባል ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኃይለመድኅን በግቢው ውስጥ ለአምስት ዓመታት ተከራይቶ ኖሯል፡፡ ኃይለመድኅን ወደ ቤቱ ሲገባና ሲወጣ ከሰው ጋር አይታይም፡፡ ጓደኛም ይዞ አይመጣም፡፡ ‹‹ሲገባና ሲወጣ ሰላምታ ይሰጠናል፡፡ ከዚያ ውጪ ከሰው ጋር ክፉም ሆነ ደግ ሲነጋገር አይተነው አናውቅም፤›› ያሉት የጥበቃ አባል፣ ኃይለመድኅንን መጨረሻ ያዩት እሑድ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ‹‹እንደተለመደው ቲሸርትና ቁምጣውን አድርጐ በግቢው ደጃፍ ከሚገኘው አነስተኛ የገበያ አዳራሽ (Mini Market) ዕቃ ገዝቶ የተለመደውን ሰላምታ ሰጥቶን አልፏል፡፡ ከዚያ በኋላ አላየሁትም፤›› ያሉት ጥበቃው በወቅቱ የተለየ ነገር እንዳላዩበት ተናግረዋል፡፡ 
በሳሚ ሕንፃ ወደ ውስጥ በተነጠፈው ኮብልስቶን መንገድ በስተግራ በኩል ባለው የኮንዶሚኒየም ግቢ ደጃፍ ምግብ ቤት፣ ኢንተርኔት ቤት፣ ግሮሰሪና አነስተኛ የገበያ አዳራሽ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ንግድ ቤቶች አንዱ በሆነው ተክሌ ግሮሰሪ ውስጥ ተቀጥራ የምትሠራው ወጣት መቅደስ፣ ኃይለመድኅንን ለአራት ዓመት ያህል ታውቀዋለች፡፡ ‹‹ስሙ ኃይለመድኅን መሆኑን ያወቅነው ከሚዲያ ነው እንጂ እኛ ታዴ በሚል ስም ነው የምናውቀው፤›› ያለችው መቅደስ፣ ኃይለመድኅን ብዙ ጊዜ ቁርስ ለመመገብ ወደ ተክሌ ግሮሰሪ እንደሚመጣ ተናግራለች፡፡ እንቁላል ፍርፍር ወይም እንቁላላ በሥጋ አዘውትሮ ለቁርስ እንደሚመርጥ የምትናገረው መቅደስ፣ ኃይለመድኅን ዝምተኛና ብቸኛ ሰው እንደሆነ ታስረዳለች፡፡
ወደ ግሮሰሪው የሚመጣው ብቻውን እንደሆነና መጠጥ ሲጠጣ አይታው እንደማታውቅ ገልጻለች፡፡ ‹‹በጣም ሰላማዊ ሰው ነው፡፡ ምን ዓይነት ነገር እዚህ ውስጥ እንደከተተው እግዚአብሔር ይወቅ፤›› ብላ፣ ዓርብ ዕለት የወሰደውን የአንድ ጠርሙስ ጉደርና እሑድ ዕለት የወሰደውን ሁለት ጠርሙስ ማልታ (አልኮል የሌለው የሜታ ምርት) ሒሳብ እሑድ ከሰዓት በኋላ ሰጥቷት እንደሄደ በትካዜ ታስታውሳለች፡፡
በተክሌ ግሮሰሪ በአስተናጋጅነት ለሦስት ዓመት ያህል የሠራው ጐሳዬ የተባለው ወጣት፣ የኃይለመድኅን ሽርክ እንደሆነ በሠፈሩ ይነገራል፡፡ ጐሳዬ ኃይለመድኅንን የሚያውቀው በተክሌ ግሮሰሪ ተቀጥሮ ሲሠራ እንደሆነ ለሪፖርተር ገልጿል፡፡ ኃይለመድኅን ዕረፍት በሆነባቸው ቀናት በስልክ የሚፈልገውን ምግብ፣ ለስላሳ መጠጦች፣ የሞባይል ካርድ የመሳሰሉትን እንዲያመጣለት እንደሚያዘውና የጠየቀውን በፍጥነት እንደሚወስድለት ተናግሯል፡፡ 
‹‹ፀባዩ ይመቸኛል፡፡ በጣም ዝምተኛ ነው፡፡ ሲበዛ ጥሩ ሰው ነው፡፡ ከአፉ ክፉ ነገር አይወጣም፡፡ ከስንቱ ጋር በሒሳብ ስጨቃጨቅ እርሱ ግን አንድም ቀን ተከራክሮኝ አያውቅም፡፡ ያዘዘኝን እወስድለታለሁ ሒሳቡን አስቦ ከነጉርሻው ይሰጠኛል፡፡ አጋጣሚ ሳይከፍለኝ ወደ ሥራ ከሄደ ከበረራ ሲመለስ ራሱ ደውሎ ናና ሒሳብህን ውሰድ ይለኛል፤›› ያለው ጐሳዬ፣ ኃይለመድኅን ቤት ውስጥ ገብቶ እንደማያውቅ፣ የጠየቀውን ዕቃና ገንዘብ የሚለዋወጡት ቤቱ በር ላይ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ ኃይለመድኅንን ባገለገለገባቸው ሦስት ዓመታት አንድም ጊዜ ከሰው ጋር አይቶት እንደማያውቅ ጐሳዬ አስረድቷል፡፡
‹‹ዕረፍት ከሆነ ከቤቱ አይወጣም፡፡ ያዘዘኝን ላደርስ ቤቱ ስሄድ ፊልም ሲመለከት ነው የማገኘው፡፡ እቤቱ ቤተሰብም ሆነ ጓደኛ  አይቼ አላውቅም፤›› ብሏል፡፡ ኃይለመድኅንን በፀባዩ በጣም እንደሚወደውና በገጠመው ነገር በጣም ማዘኑን የሚናገረው ጐሳዬ፣ በቅርቡ ነጭ መኪና መግዛቱን ተናግሯል፡፡ 
የኃይለመድኅን ጐረቤቶች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ከሰላምታ ያለፈ ከእነርሱ ጋር ቅርርብ የለውም፡፡ ይልቁንም ኃይለመድኅን በዕረፍቱ ቀናት (በረራ ሳይኖረው) ረዥም ጊዜ የሚያሳልፈው መሲ ቢዝነስ ሴንተር በተባለው ቤት ኢንተርኔት በመጠቀም እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡
መሲ ቢዝነስ ሴንተር የሚገኘው በኮንዶሚኒየሙ ግቢ በውጪ በኩል ጥግ ላይ ነው፡፡ የቢዝነስ ሴንተሩ ባለቤት ወ/ሮ መሠረት ከሪፖርተር ጋር አጭር ቆይታ አድርጋለች፡፡ መሠረት ኢንተርኔት ቤቱን ከከፈተች ሰባት ወር እንደሆናት፣ በዚህም ጊዜ ኃይለመድኅን ዋና ደንበኛዋ እንደሆነ ገልጻለች፡፡ ‹‹ዕረፍት ከሆነ እኛ ጋር ይመጣል፡፡ ለረዥም ሰዓት ይቀመጣል፡፡ በኢንተርኔት የሚከታተለው የውጭ ፊልም አለ፡፡ አስቂኝ ፊልም ሳይሆን አይቀርም ፊልሙን እያየ ይስቃል፤›› ብላለች መሠረት፡፡ 
‹‹የሚመለከተው ነገር ከፖለቲካ ጋር ግንኙነት ያለው አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም የሚቀመጥበት ቦታ ማንም ሰው ከኋላው ወይም በረንዳው ላይ እንኳ ሆኖ ሊመለከተው ይችላል፤›› የምትለው መሠረት፣ ኃይለመድኅን ዝምተኛና መልካም ፀባይ ያለው ሰው እንደሆነ ትመሰክራለች፡፡ 
ሳሚ ሕንፃ ፊት ለፊት ጫማ ከሚጠርጉት ሊስትሮዎች መካከል አንዱ የሆነው አሸናፊ በቀለ ኃይለመድኅን ደንበኛው እንደሆነ ተናግሯል፡፡ የ15 ዓመት ታዳጊ የሆነው አሸናፊ የኃይለመድኅን ጫማን ቀለም በቀባ ቁጥር ስድስት እስከ አሥር ብር እንደሚሰጠው ይናገራል፡፡ ክሬም ጫማ ለመቀባት የሚያስከፍለው ስድስት ብር ቢሆንም ኃይለመድኅን አሥር ብር እንደሚሰጠው በፈገግታ ያስታውሳል፡፡
የአካባቢው ሰዎች ኃይለመድኅንን የሚገልጹት በተመሳሳይ ዓረፍተ ነገር ነው፡፡ ዝምተኛ፣ ብቸኛና ሰላማዊ ሰው ነው በማለት፡፡ ኃይለመድኅን የአዕምሮ ጤንነቱ እንደታወከ በሥነ አዕምሮ ሐኪሞች ማረጋገጥ ከተቻለ ከፍርድ ነፃ ሊወጣ እንደሚችል ያነጋገርናቸው የሕግ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንደዚህ ያሉ ድርጊቶችን በትክክል በአዕምሮ ጤና መታወክ የተፈጸሙ መሆኑን ፍርድ ቤትን ማሳመን የሕግ ባለሙያዎችን የሚፈትን ከባድ ሥራ እንደሆነ የሕግ ባለሙያዎቹ ያስረዳሉ፡፡ 
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን በአውሮፕላን ጠለፋው ዙሪያ ባለፈው ማክሰኞ ከሰጡት መግለጫ ውጪ የምጨምረው የለም ሲል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዝምታን መርጧል፡፡ 
አቶ ሬድዋን የረዳት አብራሪውን የአዕምሮ ጤንነት በተመለከተ ተጠይቀው አየር መንገዱ እስከሚያውቀው ድረስ ግለሰቡ ጤነኛ ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 
ሪፖርተር ያነጋገራቸው አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ አብራሪዎች በየጊዜው ሙሉ የጤና ምርመራ እንደሚደረግላቸው ገልጸው፣ የምሥለ በረራ ሥልጠና በሚወስዱ ጊዜ ጭንቀትን (Stress) የመቋቋም ብቃታቸው ይታያል ብለዋል፡፡ ‹‹እኛ የምናውቀው አቶ ኃይለመድኅን ብቁ (Qualified) አብራሪ መሆኑን ነው፤›› ብለዋል፡፡
አየር መንገዱ በርካታ ስኬቶችን እያስመዘገበ ባለበት ወቅት በተፈጠረ አንድ ክስተት ምክንያት የገነባው መልካም ስምና ዝና ሊናድ አይገባም ሲሉ ያስረዳሉ፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 8,000 ሠራተኞች ሲኖሩት፣ 651 አብራሪዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል 100 ያህሉ የውጭ ዜጐች ናቸው፡፡ ‹‹ስምንት ሺሕ ሠራተኞች ባሉበት ኩባንያ ውስጥ አንድ ሰው ባደረገው ድርጊት ሁሉም ነገር በዜሮ ሊባዛ አይችልም፣ አይሆንምም፤›› ብለዋል፡፡
Source: Reporter
 
“የተሳፋሪው ፍላጎት የሆነ መሬት ላይ ማረፍ ብቻ  ነበር”
በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ ኬሮ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተወልዶ ያደገው ወጣት ምህረቱ ገብሬ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በቀድሞው ሀዋሳ ኮምቦኒ የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ነው የተከታተለው። የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና የመሰናዶ ትምህርቱንም በቅዱስ ዳንኤል ኮምቦኒ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ት/ቤት አጠናቋል። ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2001 ዓ.ም በሲቪል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ካገኘ በኋላም፤ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በመምህርነት አገልግሏል፡፡ በመቀጠልም ነጻ የትምህርት ዕድል በማግኘት፣ ወደ ጣሊያን አምርቶ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡

በቅርቡ ለእረፍት ወደ አገሩ የመጣውና በሃዋሳ ቆይቶ ወደ ጣሊያን ለመመለስ አውሮፕላን የተሳፈረው ምህረቱ፣ ባለፈው ሰኞ በረዳት አብራሪው ተጠልፎ ጄኔቭ እንዲያርፍ በተደረገው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ውስጥ ከነበሩት 200 ገደማ ተሳፋሪዎች ውስጥ አንዱ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት በጣሊያን የሚገኘው ምህረቱ፣ የጠለፋውን አጋጣሚ በተመለከተ ጋዜጠኛ አንተነህ  ይግዛው በኢ-ሜይል ለላከለት ጥያቄዎች የሰጠውን ምላሽ  እንደሚከተለው አጠናቅረን አቅርበነዋል፡፡

የጉዞው አጀማመር ምን ይመስል ነበር?
አርፍዶ ወደ አውሮፕላን ጣቢያ መምጣት የሚያደርሰውን ጣጣ ስለማውቀው፣ አውሮፕላኑ ከሚነሳበት 50 ደቂቃ ያህል ቀድሜ ነበር የተገኘሁት፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ማለት ነው፡፡ ያው ጉዞው ሲጀመር እንደሌላው ጊዜ ሁሉ ስርአቱን የጠበቀና ሰላማዊ ነበር።  አውሮፕላኑ ከበራራ ሰዓቱ ሰባት ደቂቃ ያህል ዘግይቶ ነበር የተነሳው።
አውሮፕላኑ ውስጥ አቀማመጥህ እንዴት ነበር? የት አካባቢ ነው የተቀመጥከው?
የመቀመጫዬ ቁጥር 27F ነበር። የተሳፈርንበት ቦይንግ 767 በርዝመቱ ትይዩ 7 የመቀመጫ መደዳዎች አሉት። ሁለት ሁለት መደዳዎች በሁለቱም ጥጎች እና ሶስት መደዳዎች መሃል ላይ። እኔ የተቀመጥኩት ከመሃል ሶስቱ መደዳዎች የመሃለኛዋ ወንበር ላይ ነበር። ከበስተግራዬ ያለችው ወንበር ላይ የተቀመጡት ሪካርዶ የተባሉ የ85 አመት የዕድሜ ባለጸጋ ጣሊያናዊ ነበሩ፡፡ በቀኜ በኩል እንዲሁ በግምት በስድሳዎቹ ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሌላ ጣሊያናዊ ተቀምጠው ነበር፡፡ ተዋውቀን ነበር፣ አሁን ግን ዘንግቼዋለሁ። ኢትዮጵያን ተዟዙረው እንደጎበኟት እያጫወቱኝ ነው ጉዞውን የጀመርነው፡፡
ጉዞውስ  እንዴት ነበር?
እንደማስታውሰው ጉዞው ሲጀመር ሰላማዊ ነበር። ከፓይለቱ ጋርም ግንኙነት (ኮሙኒኬሽን)  ነበረን፡፡ እኔ ድካም ስለተሰማኝ ወዲያው አሸለብኩ፡፡ በረራው ከተጀመረ በግምት ከ1 ሰዓት በኋላ የሱዳን አየር ክልል ውስጥ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ. . . መብራት ሲበራ ከእንቅልፌ ነቃሁ፡፡ የምግብ ሰዓት መድረሱ ገብቶኛል። ወደ ፊት አሻግሬ ሳይ ሆስተሶቹ እያስተናገዱ ከእኔ ፊት 4ኛ ይሁን 5ኛ ረድፍ ደርሰዋል። ሁሉም ተዘገጃጅቶ እየተጠባበቀ ነበር። በዚህ መሃል የፕሌኑ ፍጥነት ሲጨምር ይታወቀኛል፡፡ ከፍታዉም ሲጨምር በጆሮዬ ላይ በሚሰማኝ ስሜት አስተዋልኩ። በተሳፋሪዎች ፊት ላይ የመረበሽ ስሜት ሲፈጠር አየሁ። እኛ  ኢኮኖሚ ክላስ ስለነበርን ከፊት ምን እየተካሄደ እንደነበር አላየንም። በኋላ ስሰማ ከፊት የነበሩትም የቢዝነስ ክላስ ተሳፋሪዎች ምንም መረጃ አልነበራቸውም፡፡
ከዚያም በድምጽ ማጉያው የሆነ ድምጽ ተሰማ፡፡ የረዳት አብራሪው ድምጽ ነበር።
“ተሳፋሪዎች ከ 12 ደቂቃዎች በኋላ ሚላን እናርፋለን” አለ ረዳት አብራሪው፡፡ ጥቂት ቆይቶም፣ “ስለተፈጠሩ አንዳንድ መጉላላቶች ይቅርታ እንጠይቃለን” ሲል አከለ-በእንግሊዝኛና በአማርኛ ቋንቋ። የረዳት አብራሪውን ንግግር ተከትሎ የተወሰኑ ተሳፋሪዎች ማጉረምረም ጀመሩ፡፡ አንዳንዶችም ጮክ ብለው ሲያወሩ ይሰሙ ነበር፡፡ ከኔ በስተግራ በኩል ሶስት አራት መደዳዎችን አልፎ ከፊቴ ተቀምጦ የነበረ አንድ ወፍራም ሰው፣ በጣሊያንኛ ቆጣ ብሎ እየጮኸ ተናገረ - “መጀመሪያ ሚላን ሳይሆን ሮም ነው ማረፍ ያለብን ፣ ወደ ሮም ውሰዱን!” በማለት። ሌሎችም የሰውየውን ሃሳብ ደገፉ፡፡ ምክንያቱም አብዛኛው ተሳፋሪ ወደ ሮም ነበር የሚጓዘው። ረዳት አብራሪው ሚላን ላይ እንደምናርፍ መናገሩ ብዙዎችን አበሳጭቶ ነበር፡፡
እውነቱን ለመናገር፣ እኔ ግን ሚላን እንደምናርፍ ስሰማ ደስ ብሎኝ ነበር፡፡ ምክንያቱም እኔ ሚላን ወራጅ ነኝ፡፡ ረዳት አብራሪው የነገረን አስራ ሁለቱ ደቂቃዎች እየተገባደዱ መሆናቸው ሲገባኝ፣ ከአውሮፕላኑ ለመውረድ መዘገጃጀትና ጓዜን መሸካከፍ ሁሉ ጀመርኩ። ሆኖም  አስራ ሁለቱ ደቂቃዎች አልፈውም አውሮፕላኑ አላረፈም፡፡ ካሁን አሁን ሚላን አውሮፕላን ማረፊያ ደረስን እያልን ስንጠባበቅ፣ ሌላ አስራ ሁለት ደቂቃዎች አለፉ፡፡ አሁንም ሌላ አስራ ሁለት ደቂቃዎች---
ተሳፋሪው ሁሉ ግራ በመጋባት ሰዓቱን ደጋግሞ መመልከትና እርስ በርስ በጥርጣሬ መተያየት ጀመረ። ከአስራ ሁለት ደቂቃዎች በኋላ ሚላን ላይ ያርፋል የተባለው አውሮፕላን፣ ከአንድ ሰዓት ተኩል በላይ በአየር ላይ ቆየ፡፡ የሚገርመው ያን ያህል ጊዜ አየር ላይ መቆየቱ ብቻ አይደለም፡፡ አበራረሩ የተለየ ነበር፡፡ አንዴ ፍጥነቱን ጨምሮ ይከንፋል፣ ከዚያ ደግሞ ፍጥነቱን ይቀንስና ተረጋግቶ ይበራል፡፡ እንደገና ይፈጥናል፣ እንደገና ይረጋጋል፡፡ ግራ ገብቶን እያለን፣ ከመቅጽበት አውሮፕላኑ ማረፊያው ላይ ደርሶ ማኮብኮብ ጀመረ፡፡ ያንን ያህል ግዙፍ አውሮፕላን፣ በዚያች ጠባብ ቦታ ላይ ያለችግር ማሳረፍ መቻሉ፣ የረዳት አብራሪውን ብቃት ያሳያል፡፡ ለማንኛውም አውሮፕላኑ በሰላም አረፈና እኛም እፎይ አልን፡፡
አውሮፕላኑ ካረፈ በኋላ የተሳፋሪዎች ስሜት ምን ይመስል ነበር?
የሚገርመው ነገር፣ አውሮፕላኑ እንዳረፈ በተሳፋሪው ፊት ላይ ከታየው ደስታና እፎይታ በተጨማሪ፣ ተሳፋሪው ለረዳት አብራሪው የሰጠው አድናቆት ነበር፡፡ አብዛኛው ተሳፋሪ ስለረዳት አብራሪው ችሎታ ነበር ተደንቆ የሚያወራው፡፡ በከፍተኛ የአድናቆት ስሜት ተውጠው፣ ለረዳት አብራሪው ያላቸውን አድናቆት በጭብጨባና በፉጨት የገለፁም ነበሩ፡፡ እኔም በደመነፍስ ሳጨበጭብ ነበር፡፡ ሚላን ምድር ላይ በሰላም እንዲያሳርፈኝ ለፈጣሪዬ ያደረስኩትን ጸሎት የማውቀው እኔ ነኝ፡፡
ሚላን እንዳረፋችሁ ነበር የምታውቁት ማለት ነው?
የሚገርመው እኮ እሱ ነው!... አውሮፕላኑ መሬት ከነካ በኋላ ሁሉ፣ ተሳፋሪው በሙሉ ጣሊያን ሚላን እንዳረፈ ነበር የሚያውቀው፡፡ ሚላን እንደምናርፍ ነው ረዳት አብራሪው የነገረን፡፡ ትኬት ከፍለን የተሳፈርነውም ወደ ጣሊያን እንጂ ወደ ስዊዘርላንድ ለመሄድ አልነበረም። በዚህ ቅጽበት ጄኔቭ የምትባል ከተማ በምን ተአምር እንሄዳለን ብለን እናስብ?
ጄኔቭ መሆናችሁን ያወቃችሁት እንዴት ነው?
አውሮፕላኑ በሰላም ካረፈ በኋላ ተሳፋሪው ከጭንቀቱ ተገላግሎ መረጋጋት ጀመረ፡፡ አንዳንዶች ሞባይል ስልኮቻቸውን አውጥተው መነካካት ያዙ። በሞባይላቸው የኢንተርኔት መስመር በመጠቀም ጎግል ማፕ የተሰኘውን የአገራትና የከተሞች ካርታ የሚያሳይ ድረገጽ፣ ጂ ፒ ኤስ ከሚባለው አቅጣጫ ጠቋሚ ቴክኖሎጂ ጋር አያይዘው ሲመለከቱ፣ ፊታቸው ላይ ድንገተኛ መደናገር ሲፈጠር አየሁ፡፡ አንዱ ተሳፋሪ ሞባይሉ ላይ ያየውን መረጃ በመጠራጠር፣ የሌላኛውን ሞባይል ማየት ጀመረ፡፡ “የት ነው ያለነው?” ለሚለው ጥያቄ እርግጠኛ የሆነ መልስ የሚሰጥ ጠፋ፡፡ ግማሹ “ ኦስትሪያ ነን!” ሲል፣ ገሚሱ “የለም ፈረንሳይ ነን!” ብሎ ይመልሳል፡፡ አንዳንዱ “ጀርመን ውስጥ ነው የምንገኘው!” ይላል፡፡ ሌላው “ስዊዘርላንድ ጄኔቭ ነው ያረፍነው!” እያለ ይናገራል፡፡ ጭንቀትና ውጥረት የፈጠረው መደናገር ሊሆን እንደሚችል ያሰብኩት በኋላ ነው፡፡
 ጄኔቭ ማረፋችሁንና አውሮፕላኑ መጠለፉን ያወቃችሁት እንዴት ነበር?
እያንዳንዱ ተሳፋሪ አውሮፕላኑ ያረፈበትን አገርና ከተማ በተመለከተ የየራሱን መላምት እየሰነዘረ ግራ ተጋብቶ ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡ በዚህ መሃል ነው፣ ድንገት የአውሮፕላኑን ዋና አብራሪ ድምጽ የሰማነው። በረራው ከተጀመረ አንስቶ የዋና አብራሪውን ድምጽ ስንሰማ ለመጀመሪያ ጊዜያችን ነበር፡፡ ዋና አብራሪው በጣሊያንኛ ቋንቋ ነበር የሚያወሩት፡፡ በጣሊያን ቆይታዬ የቀሰምኳት ቋንቋ ብዙም የምታወላዳ አልነበረችምና፣ ደቂቃዎችን ከፈጀው የአብራሪው ንግግር የተወሰነችዋን ተረድቼ፣ ቀሪውን ከጎኔ ከተቀመጡት ጣሊያናውያን ጠይቄ ለመረዳት ሞከርኩ፡፡
አብራሪው  ወደመጸዳጃ ቤት ሲወጡ ረዳት አብራሪው በር እንደዘጋባቸው፤ አውሮፕላኑን ለሰዓታት ሲያበር የቆየው ረዳት አብራሪው እንደነበር፤ አውሮፕላኑ ያረፈው ጄኔቭ መሆኑን፤ በተፈጠረው ነገር ማዘናቸውን መግለጻቸውን እንዲሁም እያንዳንዱ ተሳፋሪ የስዊዘርላንድ ፖሊሶች ለሚያደርጉት ምርመራ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ማስተላለፋቸውን ነገሩኝ፡፡ ተሳፋሪው ስለ ጠለፋው ያወቀው በዚህ ጊዜ ነው፡፡
ተጠልፋችሁ ያላሰባችሁት ቦታ እንዳረፋችሁ ስታውቁ ምን ተሰማችሁ?
እውነቱን ለመናገር በወቅቱ የሁሉም ተሳፋሪ ጸሎትና ምኞት በረራው በሰላም መጠናቀቁና አውሮፕላኑ አደጋ ሳያጋጥመው ማረፉ ብቻ ነበር፡፡ የተሳፋሪው ፍላጎት የትም ይሁን የት፣ ብቻ የሆነ መሬት ላይ ማረፍና ከጭንቀት መገላገል ነበር፡፡ አስበው እስኪ… ከአብራሪውም ሆነ ከሆስተሶቹ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት በሌለበት አደናጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው ለሰዓታት የበረርነው፡፡ ከዚያ ደግሞ… ሮም የማረፍ ዕቅዱ ተሰርዞ፣ ከ12 ደቂቃዎች በኋላ ሚላን እንደምናርፍ ድንገት ተነገረን፡፡ ይሁን ብለን ተቀብለን፣ አስራ ሁለቱን ደቂቃ በጉጉት ስንጠባበቅ ደግሞ፣ ለተጨማሪ አንድ ሰዓት ተኩል ያህል ጊዜ በረራው ቀጠለ፡፡ በዚያ ላይ በረራው ጤነኛ አልነበረም፡፡ አንዴ የሚፈጥን፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚረጋጋ ምቾት የማይሰጥ በረራ ነበር፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ያለ ተሳፋሪ፣ የትም ቢሆን ማረፍን እንጂ፣ማረፊያ ቦታውን አይመርጥም፡፡ እኔም ሆንኩ ሌሎች ተሳፋሪዎች ጉዳዩን ያወቅነው፣ ጠለፋው ከተጠናቀቀና አውሮፕላኑ ጄኔቭ ውስጥ በሰላም ካረፈ በኋላ ዋና አብራሪው ሲነግሩን በመሆኑ እምብዛም አልተደናገጥንም፡፡
ከአውሮፕላኑ ስትወርዱ የነበረው ሁኔታ ምን ይመስላል?
አውሮፕላኑ ጄኔቭ ካረፈ በኋላ በግምት ለአንድ ሰአት ያህል በሩ ሳይከፈት ቆሞ ቆየ፡፡ ዋና አብራሪው ሁሉንም ነገር በግልጽ ከነገሩን በኋላ፣ ከእግር ጣታቸው እስከ ራስ ጸጉራቸው የብረት ጭንብል የለበሱ ሰዎች፣ በሩን በርግደው በፍጥነት ወደ ውስጥ ገቡ። አገባባቸውና መላ ሁኔታቸው አክሽን ፊልም የሚሰሩ ነበር የሚመስሉት፡፡ ሁኔታው እጅግ ያስጨንቅ ነበር፡፡ በመካከል አንደኛው ፖሊስ በእጁ በያዛት አነስተኛ የድምጽ ማጉያ ፈረንሳይኛ በሚመስል እንግሊዝኛ መናገር ጀመረ።
“ዚስ ኢዝ ኤ ፖሊስ ኦፔሬሾን። ዶንት ሙቭ!... ፑት ዩር ሃንድስ ኦን ዩር ሄድ!... ዶንት ሜክ ሙቪ ባይ ሞባይል (በሞባይል አትቅረጹ ማለቱ ነው)” ሲል ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ ሁሉም እጆቹን አናቱ ላይ ጭኖ ድምጹንም አጥፍቶ አቀረቀረ፡፡ ተሳፋሪው በፖሊሶቹ መሪነት አንድ በአንድ ከአውሮፕላኑ እየወረደ፣ ሁለት ሁለት ጊዜ ተበርብሮ ተፈተሸ፡፡
ፍተሻው እንደተጠናቀቀም በትላልቅ ሽንጣም አውቶብሶች እየጫኑ ወደ ተርሚናሉ ወሰዱን፡፡ ተርሚናሉ ላይ ስንደርስ የሚገርም አቀባበል ተደረገልን፡፡ የምንበላው ቁርስና ሻይ ቡና እንዲሁም ለብርዱ ብርድልብስ ተዘጋጅቶ ጠበቀን፡፡ የህክምና ባለሙያዎችና የስነልቦና ባለሙያዎች እርዳታ ሊሰጡን እየተጠባበቁ ነበር፡፡ አስገራሚ አቀባበል ነው የተደረገልን።
ኢትዮጵያውያንስ አላገኛችሁም?
ተርሚናሉ ዉስጥ ገብተን ትንሽ እንደቆየን አንድ ኢትዮጵያዊ ወደ እኛ ሲመጣ ተመለከትን፡፡ ለጊዜው ስሙ ትዝ አይለኝም። ከኢትዮጵያ ኤምባሲ እንደመጣ ነገረንና ስለሁኔታው ጠየቀን። “አይዟችሁ!... ደርሰንላችኋል!...” የሚል መንፈስ ያለው ማበረታቻ ሰጠን፡፡ ከዚያም የግል ሞባይሉን ከኪሱ አውጥቶ አገር ቤት ያሉ ቤተሰቦቻችን ጋ ደውለን ደህንነታችንን እንድናረጋግጥ ራሱ እየደወለ ያገናኘን ጀመር፡፡ 
በዚህ ጊዜ ነው፣ በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር የመጡት፡፡ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበርን ኢትዮጵያውያንን አነጋግረው አረጋጉን፡፡ በስተመጨረሻም ከተርሚናሉ እንዲወጡ ስለታዘዙ የማስታወሻ ፎቶግራፍ አብረውን ተነሱና ጉዳያችንን በቅርብ እንደሚከታተሉ ነግረውን አበረታቱንና ሄዱ፡፡ ሌሎች ሁለት የኤምባሲው ባልደረቦችም፣የሚፈቀድላቸው ቦታዎች ላይ ሁሉ እየተገኙ ድጋፍ በማድረግ እስከመጨረሻው አብረዉን ነበሩ።
በእለቱ ስለተከሰተው ሁኔታ ምን ትላለህ?
እናቴ እንደነገረችኝ፣ በህፃንነቴ የወራት ዕድሜ ላይ እያለሁ፣ የሆነ ቀን ከታላቅ ወንድሜ መላኩ ገብሬ ጋር ከጎማ ላስቲክ የተሰራ አልጋ ላይ ተኝቼ ነበር። ቡና ስታፈላ ምንጊዜም ዕጣን ማጨስ እማትዘነጋው እናታችን፣ ያጨሰችዉን እጣን እኛ የተኛንበት አልጋ አጠገብ አስቀምጣው ኖሮ፣ እሷ ጎረቤት ደርሳ ስትመለስ ቤቱ በጭስ ተሸፍኖ ጨልሞ ጠበቃት። ጩኸቷን ለቀቀችው። ጩኸት ሰምቶ የመጣ ጎረቤት ነው አሉ ፈልጎ አግኝቶኝ በመስኮት ወደ ውጭ የወረወረኝ። ምህረቱ የተባልኩትም በዚያ ምክንያት ነው። እንዳጋጣሚ እሳቱ ቀድሞ የተያያዘው ወንድሜ በተኛበት በኩል ስለነበር እሱን ማትረፍ አልተቻለም።
የፈጣሪ ምህረት ዛሬም አልተለየኝም፡፡ በአውሮፕላኑ ላይ ሊደርስ ከሚችለው አሰቃቂ አደጋ አትርፎኛል። እንደትላንትናው ሁሉ ነገዬም በፈጣሪ እጅ እንደሆነች አምናለሁ። እርሱ ይሁን ያለው ሁሉ መልካም ነው። ቸርነቱ አይለየኝና ፍቃዱ ሆኖ ለነገ ካበቃኝ ለልጆቼ የምነግረው ተጨማሪ ታሪክ አግኝቻለሁ።
ደህና ነኝ እንኳን ብላት የማታምነኝ እናቴ ብርሃነማርያም ኪአን፣ እጮኛዬ ዮዲት ቦርሳሞን፣ ወንድሞቼን፣ ብቸኛዋን እህቴን፣ አክስቶቼን ከነቤተሰቦቻቸው፣ ጓደኞቼን፣ስለደህንነቴ የሚጨነቁልኝን ሁሉ ደህና መሆኔን ንገርልኝ። ከሁሉ አስቀድሞ ስለሆነውም ስለሚሆነዉም ክብር ሁሉ የእርሱ ነውና ፈጣሪ የሚገባዉን ክብር እና ምስጋና ይውሰድ።
Source: Addis Admass
 
ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል። 
ሂዉማን ራይትስ ዎች፤ ኢትዮጵያ፤ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቦችን ጎዳ በሚል ዛሬ ባወጣዉ ዘገባ፤ አዳዲስ ከሳተላይት የተገኙ ምስሎች በታችኛዉ ኦሞ ሸለቆ አካባቢ ነባር ማኅበረሰቦች ይጠቀሙበት የነበረዉን መሬት ለስኳር ልማት በስፋት መመንጠሩን ማሳየታቸዉን አመልክቷል። ላለፉት አምስት ወራትም 7,000 የሚሆኑ የቦዲ ጎሳ አባላት ጋ በቂ ምክክር ሳይደረግ ተግባሩ መከናወኑን ዘርዝሯል። የድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳይ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮ፤ ድርጅታቸዉ በUNESCO በዓለም ቅርስነት
በተመዘገበዉ አካባቢ ለበርካታ ዓመታት የሚከናወነዉን እንደሚከታተል በማመልከት፤
«የኢትዮጵያ መንግስት በርካታ ግድቦችን በኦሞ ወንዝ አካባቢ በመገንባት ላይ ይገኛል። የወንዙ ዉሃም ለስኳር ተክሉ ወደግድቦች ለመስኖ ተቀልሷል። እናም ባጠቃላይ እነዚህ ሁሉ እንቅስቃሴዎች በኦሞ ሸለቆ በሚገኙ ነባር ኗሪዎች ህይወት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አስከትለዋል። እዚያ ወደሁለት መቶ ሺህ ሰዎች ይኖራሉ። አብዛኞቹም እዚያ መሬታቸዉ ሲመነጠር አይተዋል፤ ወደሌላ ስፍራ አንዳንዴም ወደመንደሮች ተወስደዉ በግዳጅ እንዲሰፍሩ ተደርገዋል። እናም የኑሯቸዉ ሁኔታ እጅግ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ነዉ።» 
ዘገባዉ እንደሚለዉ የመሬት ምንጠራዉ የኢትዮጵያ መንግስት በኦሞ ሸለቆ ያቀደዉ ሰፊ የልማት ተግባር አካል ነዉ። የግድብ ግንባታዉን ጨምሮ፣ የስኳር ተክል ልማቱም ሆነ ለገበያ የሚዉል የእርሻ ምርት ማምረቻዉ በኦሞ ወንዝ የሚገኘዉን አብዛኛዉን ዉሃ ይጠቀማል የሚል ስጋትም አለዉ። ይህም በአካባቢዉ በኢትዮጵያም ሆነ በጎረቤት ኬንያ የሚገኙና ዉሃዉን ለኑሯቸዉ የሚጠቀሙ ወገኖች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እንደሚጎዳ አመልክቷል። ዘገባዉ የኢትዮጵያ መንግስት መሬቱንና የተፈጥሮ ሃብቱን ማልማት እንደሚችል ያ ግን በአካባቢዉ የሚኖሩ ማኅበረሰቦችን መብት በጠበቀ መልኩ እንዲሆን ያስገነዝባል። እንዲህ ያሉ የልማት ተግባራት ሲከናወኑ የሚከተል የጎንዮሽ ችግር አይጠፋም እና ይህ እንዴት ይታያል ለሚለዉ፤ ሌቭኮቭ ችግሩ የሚከናወንበት መንገድ ነዉ፤ ነዉ የሚሉት፤
«እርግጥ ነዉ የኢትዮጵያ መንግስት እንደማንኛዉ መንግስት ለኤኮኖሚ እድገት ዉሃዉንም ሆነ የተፈጥሮ ሃብቱን ማልማት ይችላል። ችግሩ የሚከወንበት መንገድ ነዉ። በኦሞ ሸለቆ የሚገኙ አብዛኞቹ ማኅበረሰቦችም በአካባቢዉ እንደሚገኝ ነባርና ይህን መሬት ለበርካታ መቶ ዓመታት ሲጠቀም እንደኖረ ዜጋ መብት አላቸዉ። የሚያሳዝነዉ ነገር በመከናወን ላይ ያለዉ ሂደት የእነሱን መብት ከግምት ያላስገባ መሆኑ ነዉ። አብዛኞቹ ሰዎች አልተጠየቁም፤ ካሳ አላገኙም፤ የኗኗራቸዉ ሁኔታ ዳግም በማይመለስ መልኩ በፍጥነት ሲለወጥ ነዉ የሚያስተዉሉት።»
ከዚህም ሌላ ይኸዉ ምክንያት ጎረቤት ኬንያ ዉስጥ የሚገኙ ማኅበረሰቦችንም ህይወት እየጎዳ እንደሚገኝም አመልክተዋል። የኦሞ ወንዝ የቱርካና ሃይቅ ዋነኛ ምንጭ መሆኑን በመግለፅም ወደ300,000 የሚሆኑ እና ኑሯቸዉ በቱርካና ሃይቅ ላይ የተመሠረተ ወገኖች መጎዳታቸዉን ዘርዝረዋል። ሂዉማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ የተለያዩ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ይህን ጉዳይ ደጋግመዉ ማንሳታቸዉና ዘገባዎችን ሲያቀርቡ ይታያል። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ ዘገባዎቹ ከእዉነት የራቁና የተዛቡ መሆናቸዉን ነዉ የሚገልፀዉ። የልማት ተግባራቱን የሚያከናዉነዉ የማኅበረሰቡን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል መሆኑንም ይናገራል። ሌስሊ ለፍኮዉ ማኅበረሰቡም እንዲህ ባሉ ተግባራት ሃሳቡን የመስጠት መብቱ መከበር አለበት ባይ ናቸዉ፤
«ችግሩ እንዲህ ባሉ ልማቶች ማኅበረሰቡም የራሱን ሃሳብ የመስጠት መብት አለዉ፤ መንግስት የእነዚህ በሁኔታዉ በጣም የሚነኩ እና የሚጎዱ ወገኖችን አስተያየት፣ ሃሳብና ግብዓት ሙሉ በሙሉ ይህን ችላ ብሏል፤ ይህ ደግሞ ከባድ ችግር ነዉ። ሰዎች መሬታቸዉ ሲነጠቅ፤ ሌላ አዲስ ስፍራ ለመስፈር ሲገደዱ እንዴት ህይወታቸዉን ማቆየት እንደሚችሉ ይቸገራሉ። ምክንያቱም በአኗኗራቸዉ ላይ ፍፁም ለዉጥ ነዉ። ለዚህ ደግሞ አልተዘጋጁም።» 
እናም ሁኔታዉ በከፍተኛ ግፊት በአካባቢዉ በሚኖሩ ወገኞች ላይ መጫኑንም አያይዘዉ ጠቅሰዋል። አንዳንድ ዘገባዎች ኢትዮጵያ አፍሪቃ ዉስጥ ከሚገኙ የዓለማችን 10 ድሃ ሃገራት አንዷ መሆኗን ይጠቅሳሉ። መንግስት የሚያከናዉናቸዉ የልማት እንቅስቃሴዎች ሀገሪቱን ወደመካከለኛ ገቢ ወዳላቸዉ ሃገራት ተርታ ያደርሳሉ ባይ ነዉ። እንዲህ ያሉት ተግባራት የጎንዮሽ ችግር ማስከተላቸዉ እየታየ ከሆነ ድርጅቱ የሚያቀርበዉን ዘገባ መንግስት ከግምት እንዲያስገባ ማድረግ የሚቻልበት መንገድ ይኖር ይሆን? ሌስሊ ሌፍኮዉ፤
«ይኖራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፤ ማለቴ በዘገባችን ምን ለማቅረብ እንደፈለግን የተሻለ ግንዛቤ ይኖራል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ልማትንም ለማከናወን የተሻለ መንገድ መኖሩን ይገነዘባሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። በመንግስት አስተዳደር ዉስጥ የሚገኙ ሰዎችም ዘገባዎቹን በጥንቃቄ በመመልከትና በማንበብ ለሁሉም የሚጠቅም ልማትን ለማከናወን አቅጣጫቸዉን ይለዉጣሉ ብዬ በጣም ተስፋ አደርጋለሁ። በተለይ በፕሮጀክቱ ኑሯቸዉ በቀጥታ ተፅዕኖ የሚያርፍበትን ወገኖች።» 
Source: DW
 

ቦሌ መሰናዶ ትምህርት ቤት ውስጥ መምህራንና ተማሪዎች በመማር ማስተማሩ ሒደት ለመምከር ተሰባስበዋል፡፡
የ‹‹ትምህርት ለሁሉም›› 2013/14 ሪፖርት ይፋ መሆንን ተከትሉ ውይይቱን ለማድረግ ለተወከሉት ተማሪዎች ሴራሊዮናዊው አወያይ ቼርኖር ባህ ‹‹መምህር መሆን የሚፈልግ አለ?›› ሲል ጥያቄውን ሰነዘረ››፡፡ ከደቂቃዎች ዝምታ በኋላ አንድ ተማሪ ‹‹እኔ መሆን እፈልጋለሁ፡፡ አንድ ጥያቄ ለመምህራኑ እንድጠይቅ ግን ፍቀድልኝ›› አለች፡፡ ሚስተር ባህ መድረኩን ሰጣት፡፡ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከማላዊና ከፓኪስታን ለተወከሉት መምህራን ‹‹ከእናንተ ውስጥ ልጁ መምህር እንዲሆን የሚፈልግ አለ?›› ስትል ጠየቀች፡፡ አንድም መምህር አዎ ሲል አልተደመጠም፡፡ 

ቤተሰብ በልጁ ላይ ከሚፈጥረው የ‹‹መምህር አትሆንም›› ተፅዕኖ በተቃራኒ ልጁ መምህር እንዲሆንለት የሚፈልግ እንዲሁም በፍላጐት ወደ ዘርፉ የሚቀላቀሉ አሉ፡፡ ሆኖም ዛሬ ዓለም እያስተናገደች ያለችው ከፍተኛ የመምህራን እጥረትና ፍልሰትን ነው፡፡ በየትምህርት
ቤቶችም ውስጥ ክፍተት እየተፈጠረ መሆኑንና አገሮች እ.ኤ.አ. እስከ 2030 ድረስ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚያስፈልጓቸውን መምህራን እንኳን ሊያሟሉ እንደማይችሉ የ‹‹ትምህርት ለሁሉም›› 2013/14 ሪፖርት ያሳያል፡፡ አገሮች መምህራንን በብሔራዊ ደረጃ እያሠለጠኑ ቢሆንም መምህራኑ በዘርፍ የማይቀጥሉበት ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ አዲሰ አበባም የችግሩ ተቋዳሽ ሆናለች፡፡

ቦሌ መሰናዶ ትምህርት ቤት በአገሪቱ ካሉ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች በመማር ማስተማሩ ሒደት ባስመዘገበው ጥሩ ደረጃ የዓለም አቀፍ ሚዲያ ሽፋን አግኝቷል፡፡ በ2005 ዓ.ም. በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናም ከመንግሥት ትምህርት ቤቶች ከአዲስ አበባ 1ኛ፣ በብሔራዊ ደረጃ 2ኛ ወጥቷል፡፡ ከዚህ ጐን ለጐን ደግሞ በመምህራን ፍልሰት ከሚቸገሩ የከተማዋ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱ የለቀቁ መምህራን እስኪተኩ ድረስ በቀሩት መምህራን ትብብር ክፍት ክፍለ ጊዜዎችን እየሸፈነ ለውጤት ቢበቃም የመምህራኑ ፍልሰት ለአስተዳደሩም ሆነ ለመምህራን ፈተና ሆኗል፡፡
የትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር አቶ ዳንኤል መኰንን እንደሚሉት፣ ከመስከረም 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ከ20 በላይ መምህራን ለቀዋል፡፡ መምህራን እንደለቀቁ ወዲያው ምትክ ማግኘቱም ቀላል አይደለም፡፡ ትምህርት ቤቱ ለክፍለ ከተማው አሳውቆ ክፍለ ከተማው መምህር እስኪመድብ በሚኖረው የሳምንትና የሁለት ሳምንት ክፍተት ሌሎች መምህራን በሳምንት ከሚያስተምሩት የትምህርት ክፍለ ጊዜ በላይ ተጨማሪ ይሰጣቸዋል፡፡ መምህራኑ በእሺታ ክፍተቱን ለመሙላት የሚሠሩ ቢሆንም በመሰናዶ ትምህርት ደረጃ መምህሩ ላይ ጫና መፍጠር የትምህርት ጥራቱን ያስጠብቃል ወይ? የሚለው ለመምህራኑም በጥያቄ የሚቀመጥ ነው፡፡ ሆኖም ተማሪዎቹ እንዳይጐዱና ከሌሎች ተማሪዎች ወደ ኋላ እንዳይቀሩ ያግዛል በሚል ቀሪ መምህራን ደርበው እንዲሠሩ ይደረጋል፡፡ በትምህርት ቤቱ ደረጃ የመምህራን ፍልሰቱ የሚፈጥረውን ክፍተት ለመሙላት ቢጥሩም ዘላቂ መፍትሔ እንደማይሆን ግን አቶ ዳንኤል ይናገራሉ፡፡ 
በከተማዋ ከሚገኙ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ባንዱ በርእሰ መምህርነት የሚያገለግሉትና ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ መምህር፣ መምህሩ የተሻለ ገቢ ፍለጋ ከሥራው የሚለቅበትን ምክንያት ያስቀመጡት የሳቸውን ደመወዝ ዋቢ በማድረግ ነው፡፡ ከ25 ዓመት በላይ በመምህርነት ያገለገሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት ደመወዛቸው ከታክስ በፊት 2,800 ነው፡፡ 300 ብር ለቤት ኪራይና 100 ብር ለወንበር አላቸው፡፡ ከገጠር እስከ ከተማ ከሁለት አሠርት በላይ ቢያስተምሩም፤ ከሚወጡት ኃላፊነት አንፃር የሚያገኙት ገቢ እዚህ ግባ የሚባል አለመሆኑን ይናገራሉ፡፡ ከዓመት በፊት ለቤት ኪራይ 1,800 ብር ይከፍሉ እንደነበር የሚያስታውሱት መምህር የባለቤታቸው 1,400 ብር ደመወዝ ተጨምሮም ‹‹ለኪሴ›› የሚሉት ገንዘብ ተርፏቸው እንደማያውቅ፣ ሙያውን ስለሚወዱት ግን እስካሁንም እንደሚያገለግሉ ይናገራሉ፡፡ ‹‹መምህርነት ጊዜያዊ መጠለያ የሆነበት ዋናው ምክንያት ተመጣጣኝ ደመወዝ ስለማይከፈል ነው›› ይላሉ፡፡ 
እንደ እሳቸው ከአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ለመምህሩ የሚከፈለው ደመወዝ አግባብ ቢመስልም መምህሩ በሚያገኘው ገቢ ደስተኛ አለመሆኑን ሥራውን በመልቀቅ እያሳየ ነው፡፡ አብዛኞቹ መምህራን ወደ ሌላ ሥራ ሊያሰማራቸው በሚችል የትምህርት ዓይነት በየዩኒቨርሲቲዎች በማታው ክፍለ ጊዜ ይማራሉ፡፡ እንደተመረቁ ሥራቸውን ይቀይራሉ፡፡ ሥራ መቀየር ምርጫ ቢሆንም መምህርነት፣ በመምህርነት ሥልጠና ለመግባት ያለውን የቅበላ መስፈርት ከፍተኛ ከማድረግ ጀምሮ ደመወዙና የሚያገኘው ጥቅማ ጥቅም ተወዳዳሪ ቢሆን መምህርነት በፍላጐት የሚመጣበት ዘርፍ ይሆን ነበር ይላሉ፡፡ የቅበላ መስፈርቱንም ‹‹ሞራል የሚነካ›› ሲሉ ይገልጹታል፡፡ 
የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የወቅቱ የመሰናዶ መግቢያ 2.4 ቢሆን በ2.00 እና በ2.4 መካከል ያመጡ ተማሪዎች በመምህርነት በዲፕሎማና ሠርተፊኬት መሠልጠን ይችላሉ፡፡ በተቃራኒው በሕክምናና በምሕንድስና የመሳሰሉና በኅብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ ስፍራ በተሰጣቸው የትምህርት ዘርፎች ለመግባት ለመሰናዶ የሚያበቃ ውጤት ከማምጣት ባለፈም የ12ኛ ክፍልን ብሔራዊ ፈተና በከፍተኛ ውጤት ማለፍ ግድ ነው፡፡ ይህም ትውልድ ለሚቀርጸው የመምህርነት ሙያ የተሰጠውን ዝቅተኛ ግምት ያሳያል፡፡ ዘርፉ ‹‹የማይፈለግ›› ወይም ‹‹ትኩረት የተነፈገው›› መሆኑ የሚጀምረውም ከቅበላ መስፈርቱ ነው ይላሉ፡፡
አንድ ዓመት ያህል በመንግሥት ትምህርት ቤት አገልግለው መንግሥታዊ ባልሆነ ድርጅት የተቀጠሩት አቶ ቴዎድሮስ ተሾመ ከመምህርነታቸው የለቀቁት በሦስት ምክንያቶች እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ አንደኛው በመምህሩና ተማሪው መካከል ያለው ግንኙነት መስመር የለቀቀና ተማሪው ለመምህሩና ለሥነ ሥርዓት የማይገዛ መሆኑ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ደመወዙ ነው፡፡ በሌላ በኩል መምህርነትን ሥራ ለማግኘት እንጂ መርጠውት ስላልገቡ በዘርፉ ሊቆዩ አልቻሉም፡፡ ‹‹እኔ እስከማውቀው ጓደኞቼ ሁሉ መምህርነትን ፈልገውት አልገቡም፡፡ ከገቡም በኋላ እየለቀቁ በተለያየ ሙያ ተሰማርተዋል፤›› ይላሉ፡፡ 
እንደ አቶ ቴዎድሮስ ትውልድን የሚቀርፀውን መምህር በሥራው ለማቆየትና ፍልሰትን ለመቀነስ ዘርፉ በከፍተኛ ውድድር የሚገባበት፣ ከፍተኛ ደመወዝ የሚከፈልበት መሆን ይገባዋል፡፡ እሳቸው በተማሩባቸው በ1980ዎቹ እንኳን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወደመምህርነት ዘርፍ የሚመድባቸው ተማሪዎች መጀመርያ ዓመት ላይ ከመባረር የተረፉ ግን ዝቅተኛ ውጤት ያላቸውን ነው፡፡ ይህ ልማድ ዛሬም በቅበላ ላይ ይታያል፡፡ ‹‹ክብር ባልተሰጠው ሙያ ማንስ መቆየት ይፈልጋል?፡፡ በፍላጐቱና በጥሩ ውጤት ለገባው መምህርም ቢሆን ክብር ያሳጣል፡፡››
ለአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች መምህራን የሚያሠለጥነው ኮተቤ መምህራን ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ነው፡፡ የኮሌጁ ዲን አቶ ተፈሪ በለው የመምህራን ቅበላ መስፈርት በመምህራን ፍልሰት ላይ ያለው ተፅዕኖ በጥናት ባይረጋገጥም እንዲሻሻል ሁሌም የሚያነሱት ጥያቄ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡
ወደዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በዲፕሎማ ደረጃ የሚገቡ ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ መምህር የሚሆኑ ሲሆን በዲግሪ ደረጃ ከሚሠለጥኑት ደግሞ መምህር መሆን የሚፈልጉት ብቻ ተጨማሪ አንድ ዓመት ሠልጥነው ወደሙያው እንዲገቡ ይደረጋል፡፡ 
በዲግሪ ደረጃ ያለው ፖሊሲ ፍላጐትን ያማከለ ነው፡፡ በዲፕሎማ ደረጃ የሚሠለጥኑት መምህራን ግን ሥራ ከያዙ በኋላ በሌላ የትምህርት ዘርፍ የማታ እየተማሩ ሥራ ሊቀይሩ የሚችሉበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ ሆኖም በዲፕሎማ ደረጃ አዲስ አበባ ላይ የመምህራን ችግር እንደሌለ ይናገራሉ፡፡ 
አቶ ተፈሪ እንደሚሉት ለመምህራን ፍልሰት እንደምክንያት የሚነሳውን የደመወዝ ማነስ አገሪቱ ካለችበት ደረጃና ከሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ሲነፃፀር ደህና የሚባል ነው፡፡ ሆኖም ከተሸከመው ኃላፊነት ጋር ሲነፃፀር አይሄድም፡፡ 
በአዲስ አበባ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚታየውን የመምህራን ፍልሰት በተመለከተ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ዋና የሥራ ሒደት አቶ አማኑኤል ኤሮሞ ‹‹የመምህራን ፍልሰት ጉዳይ የሁላችንም ጭንቀት ነው፡፡ ይህን ሁሉ ተማሪ ትምህርት ቤት አስገብተን ያለ መምህር ዋጋ የለውም›› በማለት የመምህራን ፍልሰት አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለአብነት ያህልም ከ2006 ዓ.ም. መስከረም ወዲህ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 50፣ በነፋስ ስልክ ላፍቶ 57 መምህራን መልቀቃቸውን አውስተዋል፡፡  
የመምህራን ፍልሰት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአሜሪካም መሆኑን የሚገልጹት አቶ አማኑኤል፣ ለመምህራን ፍልሰት ምክንያቶች የተለያዩ ቢሆኑም ሚዛን በሚደፉት በደመወዝ ጭማሪ ጥያቄና በሙያው ፍላጐት ዙርያ በአዲስ አበባ ደረጃ ጥናት ሊደረግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 
እንደ መፍትሔም በትምህርት ቤት መልካም አስተዳደርና ምቹ አገልግሎት እንዲኖር እንዲሁም ከደመወዝ ጭማሪ አኳያ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየተወያዩ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
Source: Reporter


[By Ayele Bekerie, PhD]:-
Mekelle, Ethiopia (TADIAS) – In 1896, eleven years after the Berlin Conference, the Ethiopian army decisively defeated the Italian military at the Battle of Adwa. It was a resounding victory because it aborted Italia’s ambition to establish a colonial foothold in Ethiopia. On March 2, 1896, The New York Times reported with a headline: “Abyssinians Defeat Italians; Both Wings of [General] Baratieri’s Army Enveloped
in an Energetic Attack.” On March 4, 1896, The New York Times featured another story about “Italy’s Terrible Defeat.” NYT also stated “three thousand men killed, sixty guns and all provisions lost.” It further indicated how high the defeat’s impact has reached by referring to the Pope who “is greatly disturbed by the news.”

“The terrible defeat” sent shock waves throughout Europe and the colonized world. It was the first time that a non-white people had defeated a European power. According to Teshale Tibebu, the victory the Ethiopians had achieved over Italy was different than other battles won by African forces. This was permanent.
While Europeans saw the defeat as a real threat to their vast colonial empires in Africa, Asia, the Americas and the Caribbean, the colonized subjects in these territories understood the event as the beginning of the end of colonialism. Adwa as Davidson aptly puts it has become a prelude to decolonization in Africa. Clearly the victory at the Battle of Adwa lends itself to multiple meanings and interpretations, depending upon perspectives and stances in relation to colonialism. The purpose of this piece is to look into the interpretations of the event from the perspectives of the colonized and how the victory brought about the idea of global Ethiopia. It can be argued that the Battle has further enhanced the symbolic significance of Ethiopia in Africa, the Americas and the Caribbean. Ethiopia has become a symbol of the anti-colonial movements throughout the world. The Battle may have also given geographical and historical certitude to Ethiopia. The Battle of Adwa is another significant symbol in the imaginary of the idea of Ethiopia. This paper looks into the symbolic importance of Adwa in the conception and development of pan-African solidarity and identity.
Ethiopia at the time of the Battle was a highly traditional empire-state where kings and nobilities ruled over a predominantly agrarian people. Modes of rules were not only dictated by customs and personal whims, they were also exploitative. Adwa then ushered a new paradigm to alter or reform the tradition, to replace it with a modern system of centralized and unified government. While the symbolic significance of the Battle successfully echoed the call for freedom and independence and an end to colonial domination abroad, the full meanings of Adwa have yet to be fully realized within Ethiopia. Adwa suggests the power of indigenous multiple voices voluntarily cooperating to defeat and challenge the European colonial order.
Virtually all the regions, religions, linguistic groups, aristocrats and peasants pulled their resources together to formulate and execute a strategy of victory. By their actions the Ethiopians were not only affirming the power and immense possibilities of unity in diversity, but they were placing issues of freedom and internal reform at the top of the national agenda. Adwa necessitates a new set of directions interspersed with broader definition and application of freedom so that all those who participated in the Battle would be able to participate in the affairs of their country. As Maimre puts it, “from the perspectives of the thousands who participated in the campaign of Adwa, the resistance to the Italian invasion embodies the aspiration for freedom, equality and unity as well as the rejection of colonialism.”
Adwa reminds the Shoan nobility to let freedom ring from northern highlands to the rift valleys, the river basins, the plain lush fields of Arussi and the salty Danakil depressions. Adwa presents a unique opportunity to reconfigure the empire-state. Unfortunately, absolutism and imperial glory overshadowed and undermined the emancipatory route suggested by the historic event of Adwa. Adwa presses on the monarchy to modernize and to let the people involve in the political process through constitutional means. Unfortunately, the leaders resisted internal reform or introduced ineffective and nominal elements of modernity. Absolute monarchy, imitative and nominal modernization and detached and non-transformative tradition were pursued and, to this date, insist on clinging to the status quo. The status quo is the cause of immense poverty and disenfranchisement for the vast majority of the people in the country.
Adwa’s magnificent victory is a model in as far as people of various cultures, religions and languages willingness to assemble for a purpose. 100,000 Ethiopian troops took positions on the fields and mountains of Adwa to encircle and defeat the enemy. The multi-cultural army paid the ultimate sacrifice when about nine thousand of its soldiers died at the Battle. With their sacrifice, they set the stage for the birth of a new Ethiopia where the reach of freedom, politically and economically, would be more egalitarian. The model, unfortunately, was not pursued in post-Adwa Ethiopia. The model of voluntary cooperation and coexistence has yet to be implemented in the twenty first century Ethiopia. The model has yet to break the cycle of poverty and endless violent conflicts in the Horn of Africa.
While the victory is certainly a major milestone in Ethiopian history, Menelik and his successors failed to fully appreciate and adopt the new reality that emerged (locally and internationally) as a consequence of the victory. The meaning and reach of freedom hampered by intolerance to internal criticism and resistance to reform the monarchy. Internationally, most historians agree that Adwa opened the way for the ultimate demise of colonialism in Africa and elsewhere.
Adwa is significant because it disturbed the colonial order in the world. Colonial subjects interpreted Adwa as a call to resist and defeat colonialism and racial oppressions through out the world. With Adwa, they have a permanent symbol and a constant reminder that colonialism was wrong and it ought to be defeated. No system is just in as long as it treats human beings as objects and fodders to exploitative and profitable economic systems. Citizen subject is a right that cannot be denied and that should be exercised if at all freedom is a universal right of peoples and communities. Adwa, to most historians, is an African victory. The 1884-85 Berlin Conference was convened to divide up the entire continent of Africa and assign colonial territories to European powers. The Europeans allocated the Horn of Africa to Italy. Italy’s unsuccessful military push in Ethiopia was a part of the European colonial order in Africa.
In preparation for this essay, I conducted field and library research in Ethiopia and abroad. I visited the town of Adwa in September 2006 and March 2012. Adwa is only 25 miles west of the ancient city of Aksum. I made the journey to Adwa in search of memorial markings, to participate in the 116th Battle of Adwa Anniversary, to pay tribute to the war heroes and heroines, to converse with residents and to visit relevant institutions and museums. The Battle of Adwa is known locally as 1886, the Ethiopian calendar year for 1896.
I also had a chance to examine archival documents in the Institute of Ethiopian Studies at Addis Ababa University and the National Archive in Addis Ababa, Ethiopia. The National Archive has, among other books, manuscripts and papers written in local languages and scripts, a rich collection of documents encompassing the 18th, 19th and early 20th centuries of the Common Era in Ethiopian history. I particularly read and copied relevant documents from the archival collections of Belata Mersea Hazen Wolde Qirqos, Doctor Dejazemach Zewde Gebre Selassie, Dejazemach Kebede Tessema, and Aleqa Taye Gebre Mariam. Recent publications of memoirs in Amharic by former palace officials or associates, such as Fitawrari Tekle Hawariat Tekle Mariam and Dejazemach Zewde Retta, have also helped a great deal to elucidate historic events. Tsehafe Tezaz Gebre Selassie’s Tarike Zemen Ze Dagmawi Menelik Neguse Negest Ze Ethiopia (Historical Period of Emperor Menelik II of Ethiopia) is a useful source of the Battle. Gebre Selassie served as a personal chronicler of the Emperor.
The collection donated to the National Archive by Belata Merse Hazen Wolde Qirqos includes a critical essay entitled Atse Menelikena Ethiopia (Emperor Menelik and Ethiopia) written by a great Ethiopian scholar, Gebre Hiwot Baykedagn. His essay criticizes Ethiopian historians for failing to engage in critical interpretations of the past. He also points out the achievements and failures of Emperor Menelik II. Another scholar who was trained in Europe, Afeworq Gebreyesus wrote the biography of Emperor Menelik. The work is regarded as serious and fruitful. Gebre Hiwot Baykedagn criticizes the book for lack of balance in the appraisal of the leadership of Emperor Yohannes II in comparison to Emperor Menelik. In addition, almost ten years ago, I participated in a book project to celebrate the centennial anniversary of the Battle of Adwa. The book, One House: The Battle of Adwa 1896-100 Years, edited by Pamela S, Brown and Fasil Yirgu, has contributors, such as the Late Laureate Tsegaye Gebre Medhin, Richard Pankhurst, and Teshale Tibebu. My contribution is entitled “How Africa Defeated Europe.”
Menelik’s (Abba Dagnew) success at the Battle of Adwa may be attributed to the following factors: One, he surrounded himself with great advisors, such as Empress Taitu Bitul, Fitawarari Habte Giorgis Dinegde (Abba Mechal) and Ras Mekonnen, a nephew and father of Emperor Haile Selassie.
Menelik was a popular leader, skillful diplomat, and good listener. Menelik believed in reconciliation. Those who revolted against him once defeated they were immediately pardoned and allowed, unfortunately, to retain their original privileged position. Menelik was keenly aware of the colonial expansionist ambition of the French, British and Italians in the region. As a result, he actively sought and acquired modern weapons from Europe. He even bought a large quantity of weapons from the Italians. He also fully exploited the rivalries among the three colonizers. More importantly, out of a long war experience, together with his ministers, regional kings, he developed a winning war plan.
Menelik’s war declaration was widely heeded and welcomed throughout the country, a clear affirmation of his popularity. Menelik’s declaration is an important literary document in the context of preparation, the will to fight and become victorious at the Battle of Adwa. Menelik appealed to love of family, religion and country. He reminded Ethiopians that the intention of the enemy is to take away the core values and traditions cherished by the people. Menelik declared (translation mine):
“Up until now, through the grace of God, who permitted me to live by destroying my enemies and expanding the territorial boundaries of our country. It is also through the grace of God that I am ruling. Therefore, I have no fear of death. More importantly, God has never let me down and I am confident that he will let me be victorious again.”
“At this time, another enemy has entered our territory by crossing our God given sea. His objective is to destroy the country and to change the religion. As a result of a major cattle disease that devastated a large number of our livestock and brought great sufferings to our farmers and pastoralists in the last few years, I remained quiet and patient to numerous hostile provocations. And yet the enemy continued to dig dipper in the ground like a hog.”
“Now God willing or with God’s help, I will not surrender my country. My fellow country folks, I do not believe that I disappointed you in the past. You have not also disappointed me. If you are strong, then help me with your strength to fight the enemy. If you are not strong, I seek your moral support for the sake of your children, wife and religion. If, on the other hand, you seek lame excuse not to join the national campaign against our enemy, I will be upset and I will not have mercy on you, I will punish you. My campaign begins in October, and I expect volunteers from Shoa to gather in Woreilu by mid October.”

This article is well-referenced and those who seek the references should contact Professor Ayele Bekerie directly at: abekerie@gmail.com.
About the Author:
Ayele Bekerie is an Associate Professor at the Department of History and Cultural Studies at Mekelle University.
Source: Tadias Addis
| Copyright © 2013 Lomiy Blog