ጊዚያዊ ጥቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት የሩሲያ ጦር በሳቸዉ አገላለጥ ለክሪሚያ «ገንጣይና ከፋፋዮች» ከለላ መስጠቱ እዉነት ነዉ።የዚያኑ ያክል ያዜንዩክና ጓዶቻቸዉ በዩናይትድ ስቴስና በተባባሪዎችዋ እቅፍ ዉስጥ መሆናቸዉም ሐቅ። 
የኪየቭ-አዲስ መሪዎች የትንሽ ግዛታቸዉን ትንሽ ጠላቶቻቸዉን ትተዉ የትልቅ ጎረቤታቸዉን ትልቅ ጠላታቸዉን እያወገዙ ደግሞ በተቃራኒዉ እንደራደር ይላሉ።የበርሊን-ለንደን-ፓሪስ መሪዎችና ተከታዮቻቸዉ ኪየቮችን ለፍጥጫ እያጃገኑ፤ ሞስኮዎችን ለመቅጣት እየዛቱ ከኪየቮች ጋር ተወያዩ ይላሉ።ኪየቭ-ብራስልሶችን የሚመሩት የዋሽግተን መሪዎች ሞስኮዎችን የሚያስፈራራ ጦር እያዘመቱ፤ ሞስኮዎችን እየቀጡ፤ ለተጨማሪ ቅጣት እየዛቱ ከሞስኮዎች ጋር ይደራደራሉ።የሞስኮ ጠላቶች የሌሉ ያክል የዘነጓቸዉ  የክሪሚያ የሞስኮ ታማኞች ትንሺቱን፤ ጥንታዊቱን ሥልታዊ ግዛታቸዉን ለሞስኮዎች ለማስረከብ ወሰኑ።ሩሲያዎች አስወሰኑ።የጦር ዘመቻ፤ የቅጣት እርምጃ ፉከራዉ ገቢር ይሆን-ይሆን? ላፍታ አብረን እንጠይቅ።

    በሩሲያ የሚደገፉት የዩክሬንዋ ትንሽ-ልሳነ ምድር ግዛት የክሪሚያ ራስ-ገዝ መስተዳድር ጠቅላይ ሚንስትር ስርጌይ አክሲየኖቭ፤ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ቭላድሚር ኮንስታንቲኖቭ ከየካቲት ማብቂያ ጀምሮ-ካቢኔ ምክር ቤታቸዉን እንዳስወሰኑ፤ እንደዛቱ፤ እንደፎከሩት በርግጥም አደረጉት።
የትንሺቱ ሥልታዊ ምድር ሕዝብ ግዛቲቱ ከሩሲያ ጋር ዳግም እንድትዋሐድ በድምፁ ወሰነ።ሲምፌሮፖል-ትናንት።«ወደ ሩሲያ እንኳን ደሕና መጣሽ።»እስከ ትናንት ከክሪሚያ ትናንሽ ጠላቶቻቸዉ ይልቅ-የሞስኮ ጠንካሮችን ሲያወግዙ ሲወነጅሉ የከረሙት የኪየቭ አዲስ መሪዎች ትናንት እኒያን የትንሽ ግዛታቸዉን መሪዎች አስታወሱ፤ ወነጀሉ፤ ሊቀጡ- ሊያስቀጡ ዛቱም።ጊዚያዊ ጠቅላይ ሚንስትር አርሴኒ ያዜንዩክ።
«የዩክሬን መንግሥት እኒያን በሩሲያ ወታደሮች የተከለሉትን የዩክሬንን ነፃነት ለማጥፋት የሚንቀሳቀሱ የመገንጠልና የመከፋፈል ቀለበት መሪዎችን እንደሚይዛቸዉ ምንም ጥርጥር የለዉም።ዓ,መት፤ ሁለት ዓመት ይወስድ
ይሆናል ግን ሁሉንም እናገኛቸዋለን።ለፍርድ እናቀርባቸዋለን።በዩሬንና በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች እንከሳቸዋለን።የቆሙባት ምድር ታጋያቸዋለች።»
የያዜንዩኒክን-ዉንጀላ፤ ጠላቶቻቸዉን የማጥፋት መቅጣት ማስቀጣት ቃል-ዕቅድን ገቢራዊነት ለማየት-መስማት ሲያንስ አንድ ሲበዛ ሁለት ዓመት መጠበቅ ይኖርብናል።ጊዚያዊ ጥቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት የሩሲያ ጦር በሳቸዉ አገላለጥ ለክሪሚያ «ገንጣይና ከፋፋዮች» ከለላ መስጠቱ እዉነት ነዉ።የዚያኑ ያክል ያዜንዩክና ጓዶቻቸዉ በዩናይትድ ስቴስና በተባባሪዎችዋ እቅፍ ዉስጥ መሆናቸዉም ሐቅ።
USS ትራክስተን የተሰኘችዉ የዩናይትድ ስቴትስ ሚሳዬል ደምሳሽ አዉሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ጥቁር ባሕር ደቡባዊ ጠረፍ መሕለቋን ከጣለች-ትናንት አስረኛ ቀኗ።መርከቢቱ የጫነችዉ ሰወስት መቶ ባሕር ወለድ ጦር ከሩሜንያና ከቡልጋሪያ ባሕር ኃይል ባልደረቦቹ ጋር የሚያደርገዉን የዉጊያ ልምምድም ትናት አገባደደ።
ከጥቁር ባሕር በስተሰሜን ክሪሚያ ጠረፍ የሰፈረዉ የሩሲያ ጦርም ልክ እንደአሜሪካኖቹ ሁሉ በምድር በባሕር ዉጊያ ልምምድ ተጠምዶ ነዉ የሰነበተዉ።ከጥቁር ባሕር ሰሜንና ደቡብ የተፋጠጡት የሁለቱ ኃያልን ፈርጣማ ወታደሮች ባሕር ምድሩን  በልምድ ተኩስ ሲያተረማሱት ሰማዩ የተረጋጋ መስሎ ነበር።ብዙ ግን አልቆየም።
ዩናይትድ ስቴትስ ያዘመተቻቸዉ አስራ-ሁለት F-16 ዘመናይ ተዋጊ ጄቶች ከሪሚያ ልሳነ ምድርን ወደ ደቡብ ትተዉ  የስማዩን  ሠላም እያደፈረሱ ፖላድ አላማዉ ፤ታዛቢዎች እንደሚሉት፤ ክሪሚያ የሰፈረዉን የሩሲያ ጦር ከደቡብ በባሕር ሐይል ከሰሜን በአየር ሐይል አጣብቆ ሞሶኮዎች በጀመሩት እንዳይቀጥሉ ለማስፈራራት ነበር።ግን ቢያንስ ለጊዜዉ አልሆነም።
የዩናይትድ ስቴትስ የጦር አዉሮፕላኖች ፖላንድ ሲሰፍሩ ሩሲያ ዘመናይ የጦር አዉሮፕላኖችዋን ፖላንድ ምሥራቃዊ ጥግ  ቤሎ ሩስ ዉስጥ አሰፈረች።ቆጵሮስ አጠገብ መሕልቋን የጣለችዉ የሩሲያ አዉሮፕላን ተሸካሚ መርከብ የተሸከመቻቸዉ ዘመናይ የጦር አዉሮፕላኖችም በሜድትራኒያን ባሕር ሰማይ ላይ በአየር ላየር ዉጊያ ስልት «ይደንሱ» ገቡ።
የፖለቲካና የወታደራዊዉ ጉዳይ ታዛቢዎች የጦር ዘመቻ-ዝግጅቱ ጡንቻን ከማሳየት ባለፍ ወደ ዉጊያ ይቀየራል የሚል ሥጋት የላቸዉም።ተራዉ ሰዉ ግን ዩናትድ ስቴትስ የሚኖሩት ዩክሬንያዊት ወይዘሮ እንደሚሉት መስጋቱ አልአረም።
«ሥጋቱ ተጨማሪ ደም መፋሰስ እንዳይኖር ነዉ።» የዩክሬኑ ጊዚያዊ ጠቅላይ ሚንስትር ያዜንዩክ የአሜሪካኖችን ቱፍታ-ምርቃት ለመቀበል ወደ ዋሽንግተን ያቀኑት ወታደራዊዉ ፍጥጫዉ በጋመበት፤ ተራዉን ሰዉ ባሰጋበት መሐል ነበር።ባለፈዉ ሳምንት ሮብ። ራሳቸዉም ጓዶቻቸዉም የኪየቭን ቤተ-መንግሥት የተቆጣጠሩት በአደባባይ ሰልፍ-ግጭት፤ ሩሲያና ተባባሪዎቻቿ እንደሚሉት ደግሞ በ«ሕገ-ወጥ» መንገድ ቢሆንም ዋይት ሐዉስም፤ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤትም የሐገር መሪነት ሙሉ ክብርና ማዕረግ አላጓደሉባቸዉም።
ዲፕሎማሲያዊ አሰጥ አገባ ኒዮርክ ሆነዉ ሐገራቸዉ ጥግ የሰፈረዉን ጦር ቃታ ሊያሰብ ወደሚችል ዛቻ አናሩት።«ጦርነት ትፈልጋላችሁ-ብለዉ ጠየቁ ሩሲያዎችን»-ጦርነት እፈልጋለሁ ብሎ-የሚዋጋ ያለ ይመስል።
«ለሩሲያ ፌደሬሽን ልናገር።ጦርነት ትፈልጋላችሁ።እንደ ዩክሬን ጠቅላይ ሚንስትር ጦርነት የምትፈልጉ አይመስለኝም።»
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሩሲያዉ አምባሳደር ቪታሊ ቹርኪን መመለስ ያለባቸዉን የዚያኑ ዕለት ለያዜንዩክ መልሰዉላቸዋል።«ጦርነት አንፈልግም።» ብለዉ።ጦርነት የለም፤እፈልጋለሁ የሚልም አይኖርም-የለምም።የዩናይትድ ስቴትስና የሩሲያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ባለፈዉ አርብ ለንደን ዉስጥ ያደረጉት ዉይይትም ጦርነትን ሳይሆን-ፍጥጫዉን ለማስቀረት ከሆነ ደግሞ የክሪሚያን ሕዝበ ዉሳኔ ለማሰረዝ ወይም ለማዘግየት ነበር።
በማዕቀብ ቅጣት፤ ዛቻ ፉከራ የታጀበዉ ዉይይት ከዉይይቱ በፊት ብዙዎች እንደጠበቁት ያመጣዉ ዉጤት የለም።ዉግዘት ዛቻዉ፤ ዲፖሎማሲያዊ ፍትግዉ አልተቋረጠም።የክሪሚያ መሪዎች ከሕዝበ ዉሳኔዉ በፊት የሩሲያን ባንዲራ ሲምፌሮድ አደባባይ ሠቅለዉ ሕዝባቸዉ የሚሹትን እንዲያደረግ ሲያግባቡ-ዩናይትድ ስቴትስ ከሕዝበ ዉሳኔዉ በፊት የመጨረሻ ዲፕሎማሲያዊ ጥይቷን ከኒዮርክ ተከሶች።
የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት የክሪያሚያ ህዝበ ዉሳኔን አለያም በዉሳኔዉ መሠረት ግዛቲቱ ከሩሲያ መቀላቀሏን እንዲያወግዝ ዩናትድስቴት ለምክር ቤቱ ረቂቅ-የዉሳኔ ሐሳብ አቀረበች።አደተጠበቀዉ ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣን ያላት ሩሲያ ረቂቁን ዉድቅ አደረገችዉ።ቻይና ድምጿን አቀበች።
የዩናይትድ ስቴትሷ አምባሳደር ሳማንታ ፓወር ግን እንደ ገና ሩሲያን አወገዙ ዛቱም። «ሩሲያ ሕገወጥ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቷን ለመደገፍ ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣኗን ተጠቅማለች።ልክ የዛሬ ሰባ ዓመት ወረራን በመቃወም በተዋጉ ሐገራት ላይ የተሰጠዉ አይነት ድምፅን በድምፅ የመሻር ዉሳኔ ነዉ።ያም ሆኖ ሩሲያ ይሕን በማድረግና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን በመጣስ የሚደርሰዉን አፀፋ መቋቋምም ሆነ የወደፊቱን እዉነትኛ ጉዞ መቀልበስ አትችልም።የክሪሚያን ይዞታም መለወጥ አትችልም።ክሪሚያ ዛሬ የዩክሬን አካል ናት።ነገም የዩክሬን አካል ናት።በሚቀጥለዉ ሳምንትም የዩክሬን አካል ናት።ወደፊትም የዩክሬንና የዓለም አቀፍ ሕግ በሚፈቅደዉ መሠረት ይዞታዋ እስካልተቀየረ ድረስ የዩክሬን አካል እንደሆነች ትኖራለች።»
የዛሬ ሰባ ዓመት።ሶቭት ሕብረትን በመቃወም ያንገራገሩ የምሥራቅ አዉሮፓ ሀገራት ፖለቲከኞችን ጥያቄ የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት እንዲደግፍ ምዕራባዉያን ሐገራት ያቀረቡትን ረቂቅ ሶቬት ሕብረት ዉድቅ አድራጋዉ ነበር።
ከሰባ ዓመት በፊት ግን የያኔዉ የሶቬት ሕብረት ገዢ ጆሴፍ ስታሊን ክሪሚያ ዉስጥ አብላጫ ቁጥር የነበራቸዉን ታታሮችን እያጋዙ ሳይቤሪያ በረዶ ላይ ሲጥሏቸዉ ለሰብአዊ-መብት፤ ለሕዝብ ነጻነት እንቆረቆራለን የሚሉት የአዉሮጳ-አሜሪካ መሪዎች ከቁብ አልቆጠሩትም ነበር።
አምባሳደር ፖውር የዛሬ ሰባ ዓመቱን ታሪክ ባስታወሱበት ንግግራቸዉ ነገ-ባሉት ትናንት ድምፁን የሰጠዉ የክሪሚያ ሕዝብ ግዛቲቱ ከሩሲያ ጋር እንድትዋሐድ ወስኗል።በከዘጠና ስድስት ከምቶ ድምፅ።የሕዝበ ዉሳኔዉ አስተባባሪዎች እንዳሉት ድምፅ መስጠት ከሚችለዉ ሕዝብ ከሰማንያ ከሰወስት የሚብልጠዉ ድምፁን ስጥቷል።እሳቸዉ አንዱ ናቸዉ።
«ሕይወቴን በሙሉ የምመኘዉን ደግፌ ነዉ ድምፄን የሰጠሁት።ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ነፃ መሆን እንፈልጋለን።አሁን የተሳካልን ይመስለኛል።አሁን እዚሕ የሆነዉና የምናየዉ የምንፈልገዉ ነዉ።»
ስታሊን ከክሪሚያ ካጋዙዋቸዉ በሕዋላ የግዛቲቱ አናሳ ነዋሪዎች የሆኑት ታታሮች ግዛታቸዉ ባያት-አባቶቸቸዉ ላይ ግፍ በፈፀመችባቸዉ ሞስኮ ስር መተዳደሯን አልተቀበሉትም።የድምፅ መስጪያዉ ካርድ ግዛቱቱ ከሩሲያ ጋር ትዋሐድ ከሚለዉ ሌላ ያለዉ አማራጭ የ1992 (ዩክሬን ከሶቬት ሕብረት የተገነጠለችበት) ሁኔታ እነደነበረ እንዲቀጥል ትፈልጋለሕ የሚል ነዉ ያለዉ።እሳቸዉ ታታር ናቸዉ። ግዛቱቲ ከዩክሬን ጋር መቆየቷን ቢደግፉም ሁለተኛዉ አማራጭ አልገባቸዉም።
«በድምፅ መስጫዉ ካርድ ያለዉን ሁለተኛ ጥያቄ ከመመለስ በስተቀር ሌላ ምርጫ የለኝም።ክሪሚያ የዩክሬን አካል እንደሆነች ትቀጥል የሚል ምርጫ የለም።በዚሕም ምክንያት ይሕን ሕዝብ-ዉሳኔ አላዉቅም።ሌሎቹ የክሪሚያ ታታሮችም እንደኔዉ ናቸዉ።»
አብዛኛዉ ሕዝብ ግን ወስነ።ሴትዮዋ እንዳሉት ተደሰተም። «ተስፋ እንዳደረግ ነዉ የሩሲያ አካል በመሆናችን በጣም ደስ ብሎናል።ይሕ በመሆኑ ከመጥፎ ታሪክ እንወጣለን።እዚሕ ለበርካታ አመታት ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም።አሁን ግን ወደ ጥሩዉ አቅጣጫ መራመድ ጀምረናል።ዛሬ በሕይወታችን በጣም አስደሳቹ ቀን ነዉ።»
ሲምፌሮፖል-ሥትቦርቅ የምዕራባዉያን የቅጣት ዱላ ተሰነዘረ።ብራስልስ። የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች በሃያ-አንድ የሩሲያ፤ የዩክሬንና የክሪሚያ ተባባሪዎችዋ ባለሥልጣናት ላይ የጉዞና ገንዘብ የማንቀሳቀስ ማዕቀብ ጣሉ።ዛሬ።ዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማም በአስራ-አንድ ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዋል።
ደግሞ በዚያ ላይ ምዕራባዉያን ሐገራት ከሩሲያ ጋር አሁንም ድርድር ይላሉ።የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ግንኙነት የበላይ ካትሪን አሽተን ቀዳሚዋ ናቸዉ።
«ሁል ጊዜ እንዳደረግሁት ሁሉ፤ ሩሲያ ከዩክሬን መሪዎች ጋር እንድትደራ,ደር፤ ከዓለም ከቀፉ ማሕበረሰብ ጋር መወያየቷን እንድትቀጥል፤ ሁኔታዉን ለማብረድ ፖፐቲካዊ መፍትሔ እንድትከተል እጠይቃለሁ።በመጨረሻ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር መልካም ግንኙነት መመሥረት ትፈልጋለች።የአዉሮጳ ሕብረት፤ ሌላዉ ዓለምም እንደዚሁ።»
የጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ቫልተር ሽታይንማየር ግን-ሩሲያ ያሻትን ስታደርግ አርፈን አንቀመጥም አሉ።
«ፍጥጫዉን አልፈለግነዉም።እንዲያዉም በተቃራኒዉ ከዚሕ ቀዉስና አስጊ ሁኔታ የምንወጣበትን ሁኔታ ላለፉት ተከታታይ ቀናት ሥናፈላልግ ነበር።ያቀረብናቸዉ ሐሳቦች ሰሚ አላገኙም።ሥለዚሕ አሁን እዚሕ (ብራስልስ) የምንገኘዉ የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ሐሳብ ለመለዋወጥ ሳይሆን በግልፅ እንደሚታወቀዉ ምላሽ ለስጠት ነዉ።»
ምላሹ? ማዕቀብ።ዋሽግተኖችም፤ብራስልሶችም የጣሉት ማዕቀብ ግን ክሪሚያ ከሩሲያ እንድትቀየጥ በግንባር ቀደምትነት ያስወሰኑትን ወይም ፍጥጫዉን በበላይነት የሚዘዉሩትን ቭላድሚር ፑቲንና ከፍተኛ ሹማምንቶቻቸዉን አይነካም።ድንቅ-ነዉ።የሩሲያ አፃፋ ምን-ይሆን? ነጋሽ መሐመድ ነኝ ለዛሬ ይብቃን።
Source: www.dw.de
 

ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም የተሰበሰቡት የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሩስያ ጦሯን ከዩክሬን ካላስወጣች ከሩስያ ጋር የተጀመረው ንግግር እንደሚቋረጥ እንዲሁም ማዕቀቦች እንደሚጣሉባት አስጠንቅቀዋል ። 
«አውሮፓ የበርሊኑ ግንብ ከፈረሰ ወዲህ ያለ አንዳች ጥርጥር እጅግ ከባድ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች ። ቀዝቃዛው ጦርነት ካበቃ ከ25 ዓመት በኋላ የአውሮፓ አዲስ የመከፋፈል አደጋ እውን ሆኗል » የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ትናንት በዩክሬን ቀውስ ላይ የተነጋገረው የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አስቸኳይ ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድሞ የሰጡት አስተያየት ነበር ። በርግጥም ሽታይናማየር እንዳሉት አውሮፓ ከባድ ችግር ውስጥ ነው ያለችው ። በአንድ በኩል በእጇ
ልታስገባት በምትፈልገው በዩክሬን የጦርነት ስጋት መስፈኑ በሌላ በኩል በዚሁ ምክንያት ንግድን ጨምሮ በልዩ ልዩ መስኮች ከምትቀራረበው ከሩስያ ጋር ያላት ግንኙነት የመበላሸቱ ስጋት እጅግ አሳሳቢ ሆኗል ። ይህ መነሻ ሆኖ የህብረቱ አባል ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው በዩክሬን ውጥረቱን በማባባስ በወቀሷት በሩስያ ላይ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ አስጠንቅቀዋል ። 28 ሃገራትን በአባልነት ያቀፈው የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ካትሪን አሽተን ሩስያ በደቡብ ዩክሬንዋ በክሪምያ ግዛት ወታደሮቿን ማዝመቷን አውግዘዋል ። የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ወታደሮችንን ለማስፈር የሩስያ ምክር ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ተጠቅመው ጦራቸውን መላካቸው አሽተን እንዳሉት የአውሮፓ የደህንነትና የትብብር ድርጅት ደንቦችን ጨምሮ ዓለም ዓቀፍ ህግንም የጣሰ እርምጃ ነው ። እንደተቀሩት የህብረቱ አባል ሃገራት የዩክሬን ሉዓላዊነት መከበር አለበት ሲሉ ያሳሰቡት አሽተን ሩስያ ጦሯን ከክሪሚያ ካላስወጣች እንዲሁም በዩክሬኗ ክሪሚያ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ

እርምጃዎችን ካልወሰደች የአውሮፓ ህብረት ሩስያን እንደሚቀጣ ዝተዋል እንደ አሽተን ህብረቱ በሩስያ ላይ ለመውሰድ ካሰበው እርምጃ እንዱ ለሩስያ ዜጎች የቪዛ አሰጣጥ ደንብን ለማማላት ከሩስያ ጋር የሚያካሂደው ንግግር ለጊዜው እንዲቋረጥ ማድረግ ነው ። በሩስያ ላይ ማዕቀቦችንም የመጣልም አቅድ አለ ።
«የአውሮፓ ህብረትና ሩስያ በቪዛ ጉዳዮች ላይና በአዲስ ስምምነትላይ የሚካሂዱትን ንግግሮች ስለማቋረጥ ተወያይተናል ።በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ያነጣጠሩ እርምጃዎችንም ለመውሰድ እናስባለን ። »
የአውሮፓ ህብረት በሩስያ ላይ ሊወስድ ያቀዳቸው እርምጃዎች እነዚህ ቢሆኑም ከህብረቱ አባል ሃገራት በተለይ በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት በሶቭየት ህብረት ጎራ ስር የነበሩት የምሥራቅ አውሮፓ ሃገራት በሩስያ ላይ ቅጣቱ እንደጠነክርና እንዲፋጠንም ነው የሚሹት ። ሊትዌንያ ፖላንድና ቼክ ሪፐብሊክ ለምሳሌ የሩስያ ዋነኛ ፖለቲከኞች የጉዞ እገዳ እንዲጣልባቸው የባንክ ሂሳቦቻቸውም በአስቸኳይ እንዳይንቀሳቀሱ እንዲደረግ ነበር ፍላጎታቸው ። ይሁንና ህብረቱ ይህን መሰሉንም ሆነ ሌላ የማዕቀብ እርምጃ ተግባራዊ አያደርግም ። ወደዚህ እርምጃ የሚሸጋገረው ሩስያ ወታደራዊውን ውጥረት ለማርገብ ፈጣንና ተዓማኒ የሚሆን አስተዋጽኦ ከማድረግ ከተቆጠበች ነው ። ሌሎች ጠንከር ያሉ እርምጃዎች ማለትም የባለሥልጣናት ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግና የመሳሰሉት ደግሞ ከነገ በስተያ የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት መሪዎች ጉባኤ ላይ ሊወሰን ይችል ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ። የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ጃኖስ ማርቶኒ በትናንቱ ስብሰባ ላይ በዩክሬን ሰሞኑን የደረሰው ሃገራቸው እጎአ በ1956 በሶቭየት ህብረት ከተፈፀመባት ወረራ ጋር አመሳስለውታል ። ይህን ንፅፅር በሶቭየት ህብረት ዘመን የተሰቃዩት የሌሎች የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት ተወካዮችም ይጋሩታል ። ዩክሬንም በክሪሚያ የተፈፀመብን ህገ ወጥ ድርጊት ነው ስትል አቤቱታዋን ለዓለም አቅርባለች ። ጠቅላይ ሚኒስትር አርስኒ ያትሴንዩክ
«ዛሬ ክሪምያ የሚገኙት ህገወጥ... እደግመዋለሁ በክርሚያ ህገወጥ ኃይልን ነው የሚወክሉት ። የዩክሬኖችን ሃብት  ለለመውሰድ ሞክረዋል ፤ የዩክሬኖችን ንብረት ለመውረስም ሞክረዋል ፤ የዩክሬንን ጦር ትጥቅ ለማስፈታት ሞክረዋል ። ለዚህ ድርጊታቸውም በሃገር ውስጥ ና በዓለም ዓቀፍ ህግ ለፍርድ ይቀርባሉ ። ይህን ማወቅ አለባቸው ።»
ሩስያ ግን አሁንም ጦሯን ክሪሚያ ማስገባቴ ህጋዊ እርምጃ ነው ስትል መከራከሯን እንደቀጠለች ነው ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሩስያ አምባሳደር ቪታሉ ሹርኪን እንደሚሉት መንግሥታቸው በዚያ የሚገኙ ዜጎቹን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰደው ይህ እርምጃ ህጋዊ ነው ።
«በዩክሬን በተፈጠረው የተለየ ሁኔታ ፣ በጓዶቻችን ላይ ፣ በሩስያ ዜጎች ላይ ፣ በተደቀነው የአደጋ ስጋት በሩስያ ህግ መሰረት እርምጃው ሙሉ በሙሉ ህጋዊ ነው »
የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዛሬ በሰጡት መግለጫ የአምባሳደራቸውን ማብራሪያ በሌላ አባባል ተናግረውታል «በዩክሬን የተካሄደው የመንግስት ለውጥ ኢ-ህገመንግሥታዊ መፈንቅለ መንግሥት ነው ሞስኮም የሩስያውያንን ደህንነት ለማስጠበቅ ጦሯን የመጠቀም መብት አላት አሁን ግን እስከዚያ መድረስ ላያስፈልግ ይችላል ሲሉ ። በፑቲን አባባል የምዕራባውያኑ እርምጃ ዩክሬን ወደ ስርዓተ አልበኝነት እንድታመራ አድርጓታል ። ሩስያ በዩክሬን በምትወስደው እርምጃ ምክንያት ምዕራባውያን የሚጥሉት ማንኛውም ማዕቀብ ደግሞ በራሳቸው ላይ መልሶ ችግር የሚያስከትል ሊሆን እንደሚችልም አስጠንቅቀዋል ።
የዩክሬኑ ቀውስ ለመፍታት ጀርመን በምታደርገው ጥረት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሽትይናሚር ዛሬ ጄኔቫ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ከሩስያው አቻቸው ሰርጌይ ላቫሮቭ ተወያይተው ነበር ። ከውይይቱ በኋላ እንደተናገሩት ግን ለዩክሬኑ ቀውስ በቅርቡ ሊገኝ የሚችል መፍትሄ የለም ነው ያሉት ።እንደ ሽታይንማየር በአሁኑ ሁኔታ ዩክሬንና ሩስያ እንዲነጋገሩ ማድረግ እንኳን አልቻሉም ። ይህ ደግሞ እንደርሳቸው ወደ መጥፎ ውሳኔ ሊያመራ ይችላል ። እናም መፍትሄ ሊያመጡ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ እርምጃዎችን ሁሉ መሞከር እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት ።
« በዩክሬን ውጥረቱ ቀጥሏል ። ሁኔታውም በጣም የተረበሸ ነው ። በየቀኑ በየሰዓቱ ጭምጭምታዎች ይሰማሉ ። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሰዎች ራሳቸውን መቆጣጠር ያለመቻላቸው ስጋት ሊጨምር ይችላል ። ይህ ደግሞ ፖለቲካዊውን ግጭት ወደ አዲስ ደም ማፋሰስ ሊቀይረው ይችላል ። በዩክሬን ብጥብጥ እንዳይከሰት ለመከላከል ሁሉንም አማራጮች መፈተሽ ጠቃሚ ነው ። »
ይህን ማሳካቱ ግን እንዲህ ቀላል እንዳልሆነ የተናገሩት ሽታይንማየር ዛሬ ጄኔቫ የተገኙበት ምክንያት ይህንኑ ጫፍ ለማድረስ መሆኑን አስረድተዋል ። ምንም እንኳን ሩስያ አሁን ከያዘችው አቋም የምትለሳለስ ባይመስልም ሽታይንማየር እንዳሉት ሩስያም የችግሩን ከባድነት ተረድታለች ።
«ከውይይቱ የተረዳሁት ነገር ቢኖር ሩስያዎች የሁኔታውን ከባድነት ተገንዝበዋል ። በዩክሬን ሉዓላዊ ግዛት ውስጥ ምንም ዓይነት የኃይል እርምጃ እንደማይወስዱ ለተናገሩትም ይህ ሩስያውያን በሚወስዷቸው እርምጃዎች መታየትና ተመዝግበውም መቀመጥ እንደሚገባቸው ተንግያለሁ ። እኛ አሁን የምናየው ከእነርሱ ጋር የሚሄድ አይደለም ።»
ሩስያ ጦሯን ወደ ደቡብ ምሥራቅ ዩክሬኗ ግዛት ክሪሚያ ካስገባች ወዲህ ምዕራባውያን ዛቻና ማስጠንቀቂያቸውን ማዥጎድጎድ ቀጥለዋል ። የአውሮፓ ህብረትና ሌሎችም የሩስያ እርምጃ ተቃዋሚ ምዕራባውያን ሩስያ በክሪምያ ወረራዋን ብታራዝም ወይም በሩስያና በዩክሬን መካከል ጦርነት ቢነሳ ምን እንደሚያደርጉ ግን ያሉት ነገር የለም ። የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እንደሚለው ሩስያ የአውሮፓ ህብረት ሶስተኛው ትልቅ የንግድ አጋር ናት ። በአውሮፓ ህብረትና በሩስያ መካከል 300 ቢሊዮን ዩሮ ወይም 413 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የንግድ ልውውጥ ያካሄዳል ። የአብዛኛዎቹ የዩክሬን ምርቶች ገበያ አውሮፓ ነው ። ሃገሪቱ የሚያስፈልጋት የኃይል አቅርቦት በተለይ የነዳጅ ዘይት ና የተፈጥሮ ጋዝ ፍጆታዋ በአብዛኛው የሚገኘው ከሩስያ በመሆኑ የዚያች ሃገር ጥገኛ ናት ። 25 በመቶ የተፈጥሮ ጋዝ ከሃገር ውስጥ ስታገኝ ፣35 በመቶውን ከሩስያ የተቀረውን 40 በመቶው በሩስያ በኩል ከመካከለኛው እስያ ሃገራት ታስገባለች ። በሌላ በኩል ሩስያ ለምዕራብ አውሮፓ ከምታቀርበው የተፈጥሮ ጋዝ 85 በመቶው የሚያልፈው በዩክሬን በኩል ነው ። ይህ ርስ በርሱ የተሳሰረ የንግድ ግንኙነት አሁን በተፈጠረው ውጥረት ምክንያት አደጋ ላይ ወድቋል ። በአሁኑ ውዝግብ ምክንያት የንግድ ማዕቀብ ቢጣል ሁለቱንም ወገን የሚጎዳ ነው የሚሆነው ። ህብረቱ ማዕቀብ ቢጥል ሩስያም አፀፋውን መመለሷ እንደማይቀር የህብረቱ ኮሚሽን አባላት ጠንቅቀው የሚረዱት ጉዳይ ነው ። ከዚህ ሌላ በማናቸውም ንግድ ላይ የሚጣል ማዕቀብን ተግባራዊ ማድረጉም ሩስያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል በመሆኗ የተለያዩ ደንቦች በሚያደርጉላት ጥበቃ ምክንያት ቀላል አይሆንም ። የአውሮፓ ህብረት ከሩስያ በሚመጣው ነዳጅ ጥገኛ በመሆኑ ይህኛው እርምጃ የሚያዋጣው አይደለም ። ሩስያም ብትሆን የደንበኛዋን የአውሮፓ ህብረት ጥገኛ ናት ። ይህን ገበያ ማጣት አትፈልግም ።አንድ ዓለም ዓቀፍ ጥናት እንደጠቆመው ከሩስያ የውጭ ንግድ ገቢ የ 2/3 ተኛው ምንጭ ከኃይል ሽያጭ ነው የሚገኘው ። ርበርሱ የተሳሰረው የአውሮፖ ህብረት የይክሬንና የሩስያ የንግድ ግንኙነት አሁን በተፈጠረው ቀውስ ምክንያት እንዳይጎዳ የአውሮፓ ህብረት እርምጃውን ቆጥቧል ። ሩስያም እንዲሁ ለጊዜው ብትዝትም የምታጣውን በማስላት አቋሟን ልታለሳልስ መቻል አለመቻሏ ለጊዜው ግልፅ አይደለም ። አንድ ግልጽ ነገር ቢኖር ለወራት በቀጠለው አሁንም ማብቂያ ባላገኘው ውዝግብም ምክንያት የዩክሬን ኤኮኖሚ መጎዳቱን የሃገሪቱም እጣ ፈንታውም ምን እንደሚሆን አለመታወቁ ነው። 
Source: dw.de
 
-ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነካቢኔያቸው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ የጀመረውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ለማላበስ አዲስ እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው፡፡
ከወደ ግብፅ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የግብፅ የውኃና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ይህንን አዲስ እንቅስቃሴ ያስተባብራሉ፡፡ 
ከዚህ ቀደም ግድቡን በተመለከተ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተገትቶ፣ አዲሱ ዘመቻ ፊቱን ወደ ጣሊያንና ኖርዌይ አዙሯል፡፡ ከዚያም ወደተለያዩ አገሮች ይቀጥላል፡፡ 
ባለፈው ሳምንት የውኃ ሚኒስትሩ መሐመድ አብዱል ሙታሊብና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነቢል ፋህሚ ወደ ጣሊያን ጉዞ አድርገዋል፡፡ የግብፅ መንግሥት ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ዋነኛ ሸሪክና የግድቡ ግንባታ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ባሉዋት ጣሊያን የተደረገው ጉብኝት ስኬታማ ነበር ብለዋል፡፡ 
   የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ የግድቡን ጥናትና ግንባታ የሚያካሂድ በመሆኑ፣ ጣሊያን የግብፆች የአዲሱ ዘመቻ ዓላማ መሆኗ እየተነገረ ነው፡፡ የውኃ ሚኒስትሩ ሙታሊብ ለግብፅ ሚዲያዎች እንደገለጹት፣
የጣሊያን ጉብኝት ግቡን በመምታቱ ወደ ሌሎች አገሮችም ጉዞው ይቀጥላል፡፡ ምንም እንኳ የተገኘው ስኬት ምን እንደሆነ ባይብራራም፣ ሙታሊብ ለጣሊያን መንግሥት ባለሥልጣናት በግድቡ ምክንያት ግብፅ ሊደርስባት የሚችለውን የውኃ ችግር ማስረዳታቸውን፣ የጣሊያን ባሥልጣናትም ችግሩን አሁን ገና መስማታቸውን መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡ የሚቀጥለው ጉዞም ለህዳሴው ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ታደርጋለች ባሉዋት ኖርዌይ እንደሚሆን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ኖርዌይ ለግድቡ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ መቼና የት እንደሰጠች ግን አላብራሩም፡፡ ግብፆች ለግድቡ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ ከሚያደርጉ አገሮች መካከል አንዷ ኖርዌይ ናት በማለት ሌሎችም አገሮች ዕርዳታ ይሰጣሉ የሚል አንድምታ ያለው አስተያየት መሰንዘራቸው ተሰምቷል፡፡  
የግብፅ መንግሥት የሚቀጥለው ዕርምጃ በተለያዩ አገሮች የሚደረግ ጉዞ ሲሆን፣ በየአገሮቹም የግብፅን አቋም በሰፊው ማስተዋወቅ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የዚህ ጉዞ ዓላማ ለግብፅ ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ ማስገኘት መሆኑ ተወስቷል፡፡ ከእነዚህ ጉዞዎች ለግብፅ ድጋፍ ማስገኘት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ማሳጣትም ነው ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ ግድቡ ግብፅን አይጐዳም እያለች ባለችበት ወቅት፣ ግብፆች ግን ይህ ግድብ በግብፅ ህልውና ላይ አደጋ የጋረጠ ነው በማለት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማሳወቅ መዘጋጀታው ተሰምቷል፡፡ 
ለተመድና ለአፍሪካ ኅብረት የሚቀርበው አቤቱታ ከፕሬዚዳንታዊው ምርጫ በኋላ የሚመሠረተው መንግሥት ተግባር እንዲሆን ወደጐን ተገፍቶ፣ አሁን የተያዘው በተለይ በአውሮፓ አገሮች ውስጥ ሰፊ ዘመቻ መጀመር እንደሆነ ሾልከው የወጡ ሪፖርቶች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዓባይ ወንዝ ተፋሰስ አገሮች ውስጥ ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ በግድቡ ላይ ጥያቄ ለማስነሳት ሌላ ዘመቻ መታቀዱም ይሰማል፡፡ ሰሞኑን የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋህሚ ነቢል በታንዛኒያ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ጉብኝቱንም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ጃካያ ኪክዊቴ ማንም አገር ግድብ ሲገነባ የተፋሰስ አገሮችን ማማከር አለበት ማለታቸው ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡      
የግብፅ የውኃ ሚኒስትር ሙታሊብ መንግሥታቸው በርካታ አማራጮችን በመያዝ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ ስምምነት መድረሱን በይፋ አረጋግጠዋል፡፡ በዚህም መሠረት በበርካታ አገሮች ግድቡ ግብፅን እንዴት እንደሚጐዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ይሠራሉ ብለዋል፡፡ የግብፅን ተለዋዋጭ አቋምና ዕረፍት የለሽ እንቅስቃሴ የሚከታተሉ ወገኖች ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ለአፀፋው ተዘጋጅቷል ወይ በማለት ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡ ኢትዮጵያ ግድቡ ከራሷ አልፎ ለአካባቢው አገሮች የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጐት መሟላት ወሳኝ መሆኑንና የግድቡን የጥራት ደረጃ በሚገባ ማሳየት አለባት ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እውነታውን ይዛ በግብፅ ፕሮፓጋንዳ መበለጥ የለባትም በማለት ያስረዳሉ፡፡   
ይህ በዚህ እንዳለ የግብፅ ጊዜያዊ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሐዚም አል ቤብላዊና የሚመሩት ካቢኔ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በአገሪቱ ሊካሄድ የሁለት ወራት ዕድሜ ሲቀረው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀዋል፡፡ 
ፕሬዚዳንታዊው ምርጫ እስኪከናወን ድረስ አገሪቱን እንዲያስተዳድር የተመረጠው የግብፅ ጊዜያዊ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትርና የሚመሩት ካቢኔ ባለፈው ሰኞ የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ለጊዜያዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት ማስገባታቸውን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ካቢኔያቸው የሥልጣን መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ያስገቡበት ምክንያት ምን እንደሆነ ለጊዜው የተባለ ነገር የለም፡፡ 
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገሪቱ መንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ፣ እሳቸውና ካቢኔያቸው የሥልጣን መልቀቂያ ጥያቄያቸውን ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት አሊ መንሱር እንዳስገቡ ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥልጣን መልቀቂያውን ለምን እንዳስገቡ ባይገልጹም፣ ከካቢኔያቸው ጋር የ15 ደቂቃ ውይይት አድርገው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ‹‹በግብፅ መንግሥት ውስጥ ብቻ ለውጥ ማምጣት ትርጉም የለውም፡፡ የግብፅ ሕዝብ የሚፈልገውንና የሚመኘውን ለመሆን በራሱ መጣር አለበት፤›› ሲሉ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡ 
ጠቅላይ ሚኒስትር አል ቤብላዊ፣ ‹‹ግብፅ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሆነች ሁሉ ሊጨበጡ የሚገባቸው ትልልቅ ዕድሎች እየተበላሹባት ነው፡፡ ስለዚህ ጊዜው ለአገራችን ስንል መስዋዕትነት የምንከፍልበት ነው፤›› ብለዋል፡፡ 
በሙያቸው ኢኮኖሚስት የሆኑት ቤብላዊ የግብፅ ሕዝብ አገሬ ምን አደረገችልኝ ከማለት ባለፈ፣ ለአገሬ ምን አደረግኩ ብሎ መጠየቅ እንዳለበት ገልጸው፣ የአጭር ደቂቃ መግለጫቸውን አጠናቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚመሩት ካቢኔ በአጠቃላይ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ከፍተኛ ትችት ሲጐርፍባቸው ነበር በማለት የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ይገልጻሉ፡፡ በበርካታ መገናኛ ብዙኃን ትችቶችም ሲወርዱባቸው ነበር፡፡  
የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲን አሸባሪ ብሎ ለመፈረጅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ረጅም ጊዜ አጥፍተዋል፡፡ በቅርቡ በፀደቀው የደመወዝ ስኬል የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሠራተኞች እንዳይካተቱ ማድረጋቸው፣ በአገሪቱ ውጥረትና የሽብር ጥቃቶች እንዲንሰራፉ አድርገዋል በማለት ይተቿቸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪና የጨርቃ ጨርቅ ሠራተኞች፣ ዝቅተኛ ደረጃ ያላቸው የፖሊስ አባላት፣ የፖስታ ቤት ሠራተኞች፣ እንዲሁም የሕክምና ዶክተሮች በተቃውሞ ውስጥ እየተሳተፉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡ 
ጠቅላይ ሚኒስትሩና ካቢኔያቸው ያቀረቡትን መልቀቂያ የአገሪቱ ጊዜያዊ መንግሥት ተቀብሎት፣ በአል ቤብላዊ መንግሥት የቤቶች ሚኒስትር ሆነው ያገለግሉ የነበሩት ኢብራሂም መህሊብ በጠቅላይ ሚኒስትርነት በመሾም ካቢኔያቸውን እንዲመሠርቱ ማክሰኞ ዕለት ተነግሯቸዋል፡፡ 
የአገሪቱን ትልቁን የኮንስትራክሽን ኩባንያ ከአሥር ዓመታት በላይ ሲመሩ የነበሩት መህሊብ፣ የአዲሱ ካቢኔያቸው አባላት ‹‹የቅዱስ ጦርነት ተዋጊዎች›› ይሆናሉ ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ ‹‹ፀጥታ በማስከበር ሽብርተኝነትን እንዋጋለን፤›› ያሉት መህሊብ፣ ካቢኔያቸውን በሦስት ቀን ውስጥ እንደሚያዋቅሩ ገልጸዋል፡፡  
በሆስኒ ሙባረክ ዘመን የገዥው ፓርቲ (ናሽናል ዲሞክራቲክ ፓርቲ) አባል የነበሩት መህሊብ ካቢኔውን ሲመሠርቱ፣ አብዛኞቹን ሚኒስትሮች በነበሩበት ቦታ ላይ ይመድባሉ ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል፡፡ ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸው የሚታወቁት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሹመት በግብፅ እንደገና አመፅ ሊቀሰቀስ ይችላል እየተባለ ነው፡፡       
 Source: Reporter

-የግብፅ የልዑካን ቡድን በህዳሴው ግድብ ላይ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ሊነጋገር ነው
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡
የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡

ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ
እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብና በሱዳን አቋም ላይ ተነጋግረዋል፡፡
ከውይይታቸው በኋላ አል ባዳዊ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሱዳን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላት አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው መባሉ በእውነት ላይ ያልተመሠረተ ተባራሪ ወሬ ነው ብለዋል፡፡ 
በግድቡ ላይ ሦስቱ አገሮች ጥልቅ ውይይት አካሂደው የሁሉንም ወገን ጥያቄዎች በሚመለስ ደረጃ መግባባት ይኖርባቸዋል የሚሉት አል ባዳዊ፣ ሱዳን የግብፅን የውኃ ፍላጐት በሚነካና ብሔራዊ ደኅንነቷን በሚጐዳ ጉዳይ ላይ አሉታዊ አቋም አትይዝም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡ 
የሱዳን የመገናኛ ብዙኃን ባለፈው ሰኞ ዘገባዎቻቸው የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር በዚህ ሳምንት ወደ ካይሮ በማቅናት ከግብፅ አቻቸው ከፊልድ ማርሻል አብዱልፋታህ አል ሲሲ ጋር በሁለቱ አገሮች የጋራ የደኅንነት ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ወደ ግብፅ በዚህ ሳምንት እንደሚያመሩ የሱዳን ትሪቡን ዘገባ ያመለክታል፡፡ 
የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ባለፈው ሰኞ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ማቆም እንደሚገባት ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ የኃይል ማመንጫ ግድብ መገንባት ከፈለገች መጠኑ አነስተኛ መሆን ይገባዋል፤›› ብለዋል፡፡ እንደሳቸው አባባል የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከታቀደው ስድስት ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ወደ 30 በመቶ ዝቅ ማለት አለበት፡፡ በዚህ ስሌት የታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ወደ 1,800 ሜጋ ዋት መውረድ አለበት፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ 45 አባላትን የያዘ የግብፅ የዲፕሎማሲ ቡድን ከጥር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለአምስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ግብፅ በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለአፍሪካ ኅብረት እንደሚያሳውቅና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትንም እንደሚያነጋግር ለመረዳት ተችሏል፡፡
ኢትዮጵያን የሚጐበኘው የልዑካን ቡድን በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ኃላፊ አምባሳደር ዓሊ ኣል ሃዲዴ የሚመራ መሆኑን በኢትዮጵያ የግብፅ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ከአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት ኃላፊና ከኅብረቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ጋር እንደሚመክር የተያዘው ፕሮግራም ያስረዳል፡፡ 
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ዳይሬክቶሬትና ከሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች ጋር እንደሚነጋገር ታውቋል፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመገናኘት በህዳሴው ግድብ ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በቅርቡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅአህመድ ነጋሽ፣ ሱዳን በህዳሴው ግድብ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የወገነችው ለራሷ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ በአጋጣሚ ለድርድር በካርቱም በቆዩባቸው ጊዜያት በተለያዩ መስጊዶች ውስጥ ሳይቀር የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሱዳንን እንዴት ሊጠቅም እንደሚችል ሲሰበክ በግርምት መታዘባቸውን በመግለጽ፣ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጐን ለራሷ ጥቅም ስትል መቆሟን መረዳት ይቻላል ብለዋል፡፡
የግብፅ ባለሥልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር በሚደረገው ውይይትም ሆነ ድርድር ሱዳን የግብፅን ጥቅም የሚፃረር አቋም እንድትይዝ አለመፈለጋቸው ቢነገርም፣ ሱዳን እስካሁን የግድቡን ግንባታ እንደምትደግፍ ነው የሚታወቀው፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጎን ለመሰለፍ የቻለችው በሦስቱ አገሮች ተወክሎ ሲሠራ የነበረውና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ያካተተው የኤክስፐርቶች ፓነል ሪፖርት ድምዳሜን አገናዝባ ነው፡፡ በሪፖርቱ ግድቡ በሱዳንም ሆነ በግብፅ ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት እንደማያደርስ ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ምንም እንኳ የግብፅ ባለሥልጣን የሱዳን አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ወግኗል መባሉን ተባራሪ ወሬ ነው ቢሉም፣ የሱዳን ባለሥልጣናት በአደባባይ ድጋፋቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡ 
Source: Reporter

[By Ayele Bekerie]:-

Who are the authors of the external paradigm?
New York (Tadias)- Sergew (1972) represents the Ethiopian scholars who look at the Ethiopian history from outside in, one of the most ardent proponents of the external origin of Ethiopian history and civilization is Edward Ullendorff. In the preface to his book The Ethiopians: An Introduction to Country and People, Ullendorff (1960) wrote:

This book is principally concerned with historic Abyssinia and the cultural manifestations of its Semitized inhabitants – not with all the peoples and regions now within the political boundaries of the Ethiopian Empire.
The constituent elements of the external paradigm are thus “historic Abyssinia” and “Semitized inhabitants.” Regarding the name Abyssinia, Martin Bernal (1987), in his book Black Athena: The Afroasiatic Roots of Classical Civilization, Vol 1, wrote: “It should be made clear that the name ‘Abyssynia’ was used precisely to avoid ‘Ethiopia,’ with its indelible association with Blackness. The first American edition of Samuel Johnson’s translation of the 17th-century travels of Father Lobo in Ethiopia and his novel Rasselas, published in Philadelphia in 1768, was entitled The History of Rasselas, prince of Abissinia: An Asiatic Tale! Baron Cuvier equated Ethiopian with Negro, but categorized the Abyssinians – as Arabian colonies – as Caucasians.”
On the question of “Semitized inhabitants, Bernal (1987) appears to agree with Ullendorff. Bernal stated, “The dominant Ethiopian languages are Semitic.” I must add, however, Bernal now claims the origin of what is generally accepted as Afro-Asiatic or “Semitic” languages is Ethiopia. The possible diffusion of the Afro-Asiatic languages from Ethiopia to the Near East since Late Paleolithic times have also been emphasized by Grover Hudson (1977; 1978). This claim by itself is a major challenge to the South Arabian or external paradigm. Ullendorff’s claim that “the Semitized inhabitants of historic Ethiopia” had South Arabian origin has become difficult to sustain. It is, however, exemplary to look into the writings of Ullendorff in order to bring to light the process of linking the Ethiopian history to an external paradigm.
According to Ullendorff, “no student of Ethiopia can afford to neglect the connection between that country and South Arabia. Among those who have recognized this vital link are Eugen Mitwoch, while leo Reinsch is the undisputed master of the Semitic connection with the Hamitic (Kushitic) languages of Ethiopia.” Hamitic/Semitic divide, of course, was nothing but a means to keep the Ethiopian people divided.
His divisiveness even became clearer in the following statement: “The Abyssinians proper, the carriers of the historical civilization of Semitized Ethiopia, live in the central and northern highlands. From the mountain of Eritrea in the north to the Awash valley in the south we find this clearly distinguishable Abyssinian type who for many centuries has maintained his identity against the influx of Negroid peoples of the Nile Valley, the equatorial lakes, or the Indian Ocean littoral.” What is surprising is this outdated argument of physical anthropology that remained unchallenged until very recently. It is also unfortunate that a significant portion of the Ethiopian elite would buy such erroneous assertion.
The outline of Ethiopian history constructed by Ullendorff begins with “South Arabia and Aksum.” And the outline has been duplicated and replicated by a significant number of Ethiopian historians. For instance, Sergew used similar “external” approach in his otherwise very important book entitled Ancient and medieval Ethiopian History to 1270. Sergew (1972) wrote, “Ethiopia is separated from Southern Arabia by the Red Sea. As is well known, the inhabitants of South Arabia are of Semitic stock, which most probably came from Mesopotamia long before our era and settled in this region. … For demographic and economic reasons, the people of South Arabia started to migrate to Ethiopia. It is hard to fix the date of these migrations, but it can be said that the first immigration took place before 1000 B.C.11 Sergew essentially echoed the proposition advanced by Ethiopianits, such as E. Littmann (1913), D. Nielson (1927), J Doresse (1957), H.V. Wissman (1953), C. Conti Rossini (1928), M. Hoffner (1960), A. Caquot and J. Leclant (1955), A. Jamme (1962), and Ullendorff (1960).12 The Ethiopianists almost categorically laid down the external or South Arabian paradigmatical foundation for Ethiopian history.
Challenges of the External Paradigm from Without
In Aksum: An African Civilisation of Late Antiquity, Stuart Munro-Hay (1991) writes: “The precise nature of the contacts between the two areas [South Arabia and Ethiopia], their range in commercial, linguistic or cultural terms, and their chronology, is still a major question, and discussion of this fascinating problem continues.”13 What is notable in Munro-Hay’s interpretation is the very labeling of the Aksumite civilization as an African civilization. Its impact may be equivalent to Placid Temples’ Bantu Philosophy. At a time when Africans are labeled people without history and philosophy, the Belgian missionary in the Congo inadvertently overturned the Hegelian reduction of the so-called Bantu. Temples elevated the Bantu (African) by wanting to observe him in the context of reason and logic, that is, philosophy.
By the same token, Aksum: An African Civilisation dares to place or locate Aksum in Africa. That by itself is a clear shift of paradigm, from external to internal. It is an attempt to see Ethiopians as agents of their history. It is an attempt to question the validity of the south Arabian origin of the Ethiopian history and civilization.
Jacqueline Pirenne’s proposal has also convincingly challenged the validity of the external paradigm as the source of Ethiopian history. Pirenne suggests that the influence is in reverse, i.e., the Ethiopians influenced the civilization of the South Arabians. She reached her ‘ingenious’ conclusion after “weighing up the evidence from all sides, particularly aspects of material culture and linguistic/paleographic information.” Pirenne is essentially confirming the proposal made by scholars such as DuBois and Drusilla Dungee Houston, two African American vindicationist historians, who, in the early 1900s, wrote arguing that South Arabia was a part of ancient Ethiopia.
Another landmark in the refutation of the South Arabian paradigm comes from the Italian archaeologist, Rodolofo Fattovitch, who linked the pre-Aksumite culture to Nubia, “especially to Kerma influences, and later on to Meroe.” After more than three decades of extensive research and publications, Fattovitch in 1996 made the following conclusion: “The present evidence does not support the hypothesis of migration from Arabia to Africa in late prehistoric times. On the contrary, it suggests that Afro-Arabian cultures developed in both regions as a consequence of a strong and continuous interaction among the local populations.” Recent archaeological evidence from Asmara region also appeared to support the conclusion reached by Fattovitch. “Archaeologists from Asmara University and University of Florida, based on preliminary excavations in the vicinity of the Asmara, seemed to have found an agricultural settlement dated to be 3,000 years old.”
Challenges of the External Paradigm from Within
Among the Ethiopian scholars, Hailu Habtu (1987) presents a very strong case against the external paradigm. As far as Hailu is concerned, “the formulation of Ethiopian and other African historiography by European scholars at times suffers from Afro-phobia and Eurocentrism.” Hailu utilizes linguistic and historical linguistics evidence to challenge the external paradigm. Most importantly, Hailu suggested a new approach in the reading of the Ethiopian past by declaring the absence of “Semito/Hamitic dichotomy in Ethiopian tradition.” Hailu cites the works of Murtonen (1967) to question any significant linguistic connection between Ge’ezand the languages of South Arabia. According to Murtonen, “Ancient South Arabic is more closely related to northern Arabic and north-west Semitic rather than Ethiopic.” He also cites Ethiopian sources, such as Kibra Nagast or the Glory of Kings and Anqatsa Haimanot or the Gate of Faith.
Another Ethiopian historian who challenged the external paradigm is Teshale Tibebu. Teshale (1992) poignantly summarizes the argument as follows: “That Ethiopians are Semitic, and not Negroid; civilized, and not barbaric; are all images of orientalist semiticism in Western Social Science. Ethiopia is considered as the southwestern end of the Semitic world in Africa. The Ethiopian is explained in superlative terms because the ‘Negro’ is considered sub-human. That the heavy cloud of racism had been deeply embedded in the triplicate4 intellectual division among Social Sciences, orientalism, and anthropology – corresponding to Whites, ‘orientals’ (who included, Semitic people, who in turn included Ethiopians), and Negro and native American ‘savages,’ respectively – is common knowledge nowadays. … Ethiopians have always been treated as superior to the Negro but inferior to the White in Ethiopianist Studies because of the racist nature of the classification of the intellectual disciplines. It is quite revealing to see that more is written on Ethiopia in the Journal of Semitic Studies than in the Journal of African History.”
Perhaps the most persistent critique of the external paradigm was the great Ethiopian Ge’ez scholar, Aleqa Asras Yenesaw. Aleqa Asras categorically rejected the external paradigm as follows:
The notion that a Semitic fringe from South Arabia brought the writing system to Ethiopia is a myth.
1. South Arabia as a source of Ethiopian civilization is a political invention;
2. South Arabia was Ethiopian emperors inscribed a part of Ethiopia and the inscriptions in South Arabia.
3. There is no such thing as Sabaen script; it was a political invention designed to undermine Ethiopia’s place in world history.
Paleontological Evidence Places the Origin in Africa
Of course, Ethiopia in terms of place and time emerged much earlier than the name itself. The formation of a geographical feature called the Rift Valley predates in millions of years the word Ethiopia. It was in the Rift Valley of northeast Africa, thanks to the openings and cracks, that paleontologists have been able to unearth the earliest human-like species. At least 5 million years of human evolution has taken place before the naming of Ethiopia. Dinqnesh, Italdu, Garhi, ramidus or afarensis are names assigned within the last thirty years, even if they predate Ethiopia by a much longer time periods.
Ethiopia’s beginning, in paleontological terms, was in what we now know as southern Ethiopia. The Afar region is primal, for it is the cradle of human beings. The people of this region may have experimented
with the oldest stone technology to develop our initial knowledge about plants and animals. They may have also experimented with languages and cultures so as to create groups and communities. They may have also been the first to map varying residential sites by moving from one locality to another.
In other words, the history of human beings begins in Africa, more specifically in the Rift Valley regions of northeast and southern Africa. As a result, African history is central to the early development of human beings. As the oldest continent on earth, it has been particularly valuable in the study of life. To many, Africa has made one of the most important, if not the most important contributions: the emergence of the earliest human ancestors about five million years ago. Evidence has shown that all present humans originated in Africa before migrating to other parts of the world. Paleontology is providing an incredible array of information on human origin. Furthermore, gene mapping and blood test are useful methods in the understanding of human beginnings in Africa.

Ethiopia has become one of the most important sites in the world in the unearthing and understanding of our earliest ancestors. Among the earliest human-like species found in Ethiopia are: Aridepithecus ramidus (4.4 – 4.5 myo), Australopithecus afarensis also known as Dinqnesh (3.18 myo), and Australopithecus garhi (2.5 – 2.9 myo). A. ramidus (an Afar word for root) is one of the earliest hominid species found in Aramis, Afar region by a team including Tim White and Berhane Asfaw. A. afarensis is widely considered to be the basal stalk from which other hominids evolved. Dinqnesh was found in Hadar, Afar region by Donald Johanson and his team in 1974. In addition, the oldest stone tools or the earliest stone technology, which is dated 2.5 million years old, was found in the Afar region by an Ethiopian paleontologist, Seleshi Semaw and his team in 1998.
Furthermore, Ethiopia has also provided us with a concrete fossil evidence for the emergence of modern human species, Homo sapiens, about 160, 000 years ago, again from the Afar region of Ethiopia. The fossil evidence supports the DNA evidence that traced our common ancestor to a 200,000-year-old African woman.23 “Geneticists traced her identity by analyzing DNA passed exclusively from mother to daughter in the mitochondria, energy-producing organelles in the cell.”24 Likewise, scientists from Stanford University and the University of Arizona have conducted a study to find the genetic trail leading to the earliest African man or Adam. According to this Y chromosome study, the earliest male ancestors of the modern human species include some Ethiopians, whose descendants populated the entire world.
According to Berhane Asfaw, an Ethiopian paleontologist, Edaltu, the probable immediate ancestor of anatomically modern humans and the 160,000-year-old fossilized hominid crania from Herto, Middle awash, Ethiopia, “fill the gap and provide crucial evidence on the location, timing and contextual circumstances of the emergence of Homo sapiens in Africa.”
In other words, as Lapiso Dilebo puts it, “Ethiopia is the primordial home of primal human beings and that ancient Ethiopian civilization ipso facto and by recent archaeological findings precedes chronologically and causally all civilizations of the ancients, especially that of Egyptian and Greco-Roman civilizations.”
I am also devoting more space to the paleontological aspect of Ethiopian history to show the way toward a paradigm shift in the reading of the Ethiopian past. It is very clear that humanity has gone through a set of dynamic evolutionary processes in Africa. What we now know as Ethiopia is central to part of an evolutionary transformation, which is attested by the presence of more than 87 linguistic groups that eventually emerged in it.
I think it will be fascinating to look into the historical convergence and divergence of all these linguistic/cultural groups, of course, from inside out.
Towards the People-Centered History of Ethiopia
A people-centered Ethiopian history will have at least the following foundations of material cultures. I would like to identify them as pastoral, inset and teffcivilizations. Distinct communities and ways of lives have been established and perpetuated on the bases of these three civilizations in three major ecological zones. Moreover, we observe the emergence of national traditions and identity through the interactions of these civilizations.
Pastoral civilizations tend to concentrate in the lowlands or dry or semi dry lands of Ethiopia. The civilization is also conducive to coexist with the traditions and practices of both inset and teff civilizations. The inset civilization covers a wide region in the south and southwest, in an area known as woina dega or an ecological zone between the lowland and the highlands of Ethiopia. It is a tradition that is deeply rooted among the peoples of Wolaita, Gurage Betoch, Keffaand numerous other nationalities of the south. Teff civilization is the civilization encompassing central and northern Ethiopia that is the mountainous region of Ethiopia. It is important to note that I use the term civilization to denote the social, economic and cultural institutions that are established and sustained by the people. Pastoral, inset and teff are primary occupations of the people, but the essence of their lives is not entirely dominated by them.

What are the main characteristics of these civilizations? The civilizations are home grown and deeply rooted. In other words, the people have succeeded in mastering ways of life that can be passed on from generations to generations. Furthermore, the civilizations are allowed to flourish in a pluralistic environment. In other words, they are civilizations that embrace or tolerate multilingual and multi-religious expressions. In all the three cases, we witness the presence of monotheistic or indigenous religious traditions, multiple linguistic expressions and patterns of social structures and functions under the umbrellas of these civilizations.
It is my contention that such inward approach may help us to fully understand, for instance the Gadaage-grade system of the Oromos. The Gada system is regarded as one of the most egalitarian democratic system invented by the Oromos. The system allows the entire community to fully participate in its own affairs. All age groups have roles to play, events to chronicle and responsibilities to assume. I just can’t imagine how we can achieve modernity, or for that matter post-modernity in governance and development, without seriously considering such a relevant practice.
The inset civilization tends to allow its male members to venture to other professions far from home. A case in point would be the Gurages and the Dorzes. The Gurages are active in trading and business through out the country. The Dorzes are the weavers and cloth makers from homegrown resources for the larger population. Inset does not take a lot of space. A well-fertilized acreage at the back of the residential home may have enough inset plants, which are capable of meeting the carbohydrate needs of the entire household throughout the year.
Teff is part of the plow culture of the highlands. Just like inset, teff culture is unique to Ethiopia. No traces of teff or inset cultures are found in South Arabia. It is indeed in these significant material cultures that we begin collecting data in order to construct the long and diverse history of Ethiopia.
Source: Tadias Magazine
| Copyright © 2013 Lomiy Blog